
Україна Online: Новини | Політика

Телеграмна служба новин - Україна

Резидент

Мир сегодня с "Юрий Подоляка"

Труха⚡️Україна

Николаевский Ванёк

Лачен пише

Реальний Київ | Украина

Реальна Війна

Україна Online: Новини | Політика

Телеграмна служба новин - Україна

Резидент

Мир сегодня с "Юрий Подоляка"

Труха⚡️Україна

Николаевский Ванёк

Лачен пише

Реальний Київ | Украина

Реальна Війна

Україна Online: Новини | Політика

Телеграмна служба новин - Україна

Резидент

Thoughts
ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም?
comment for the writer : @nhymn
discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk
Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1
Since: Dec-10-2022
comment for the writer : @nhymn
discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk
Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1
Since: Dec-10-2022
TGlist rating
0
0
TypePublic
Verification
Not verifiedTrust
Not trustedLocationУзбекістан
LanguageOther
Channel creation dateFeb 07, 2025
Added to TGlist
Aug 22, 2024Linked chat
TH
Thoughts
411
Records
23.04.202523:59
7.7KSubscribers05.04.202523:59
1000Citation index19.04.202513:56
3.3KAverage views per post27.02.202510:53
1.5KAverage views per ad post05.02.202523:59
266.67%ER11.09.202423:59
50.02%ERRGrowth
Subscribers
Citation index
Avg views per post
Avg views per ad post
ER
ERR
Reposted from:
Open reading 🕊⃤



30.03.202508:49
1-ድግስ ላይ አንዲት ቆንጆ ልጅ አይተ በመሄድ "ሃብታም ነኝ አግቢኝ" ብትላት፤ ይህ “Direct marketing” ቀጥታ ማርኬቲንግ ነው።
2-የሆነ ግብዣ ላይ ቆንጆ ሴት አይተህ አንዱ ጓደኛህ ወደዛች ልጅ በመሄድ ወደ አንተ እየጠቆመ ሀብታም ነው አግቢው ካለ ይህ “Advertising” ማስታወቂያ ነው።
3-አንዲት ቆንጆ ልጅ ወደ አንተ በመምጣት፡-"ሀብታም ነህ አግባኝ" ካለችህ ይህ “Brand” የምርት ስም እውቅና ነው።
4-አሁንም እቺ ልጅ ጋር ተጠግተህ "ሀብታም ነኝ አግቢኝ" ስትላት በምላሹ በጥፊ ብትመታህ ይህ “Costumer feedback” የደንበኛው አስተያየት ነው።
5-ግብዣው ጋር ወዳለችው ሴት ሄደህ ልታወራ ስትል አንድ ሌላ ቦርጫም ሰውዬ መጥቶ "ሀብታም ነኝ አግቢኝ" ቢላት ይሄ “competition” ውድድር ይባላል።
6-አንተ የፍቅር ጥያቄ አቅርበህላት እሷ ግን ከባሏ ጋር ብታስተዋውቅህ ይህ “Supply and demand gap” የአቅርቦት እና የፍላጎት ክፍተት ነው።
7-አንተ ወደ እርሷ ሄደህ ምንም ከማለትህ በፊት ሚስትህ ብትመጣ እነዚህ አዳዲስ ገበያዎች ወደ አንተ እንዳይመጡ የቀረጥና የቦታ ገደቦች ተጥሎብሃል እንደማለት ያለህ ነው።
ይህ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ውስጥ ፕሮፌሰሩ ስለማርኬቲንግ ለተማሪዎቻቸው በአሪፍ እውነታ ምሳሌዎችን በመስጠት ያስረዱት ነው!
◆━━━━━━✎✦✎━━━━━━━◆
~ @open_reading1 ~
~ @open_reading1 ~
2-የሆነ ግብዣ ላይ ቆንጆ ሴት አይተህ አንዱ ጓደኛህ ወደዛች ልጅ በመሄድ ወደ አንተ እየጠቆመ ሀብታም ነው አግቢው ካለ ይህ “Advertising” ማስታወቂያ ነው።
3-አንዲት ቆንጆ ልጅ ወደ አንተ በመምጣት፡-"ሀብታም ነህ አግባኝ" ካለችህ ይህ “Brand” የምርት ስም እውቅና ነው።
4-አሁንም እቺ ልጅ ጋር ተጠግተህ "ሀብታም ነኝ አግቢኝ" ስትላት በምላሹ በጥፊ ብትመታህ ይህ “Costumer feedback” የደንበኛው አስተያየት ነው።
5-ግብዣው ጋር ወዳለችው ሴት ሄደህ ልታወራ ስትል አንድ ሌላ ቦርጫም ሰውዬ መጥቶ "ሀብታም ነኝ አግቢኝ" ቢላት ይሄ “competition” ውድድር ይባላል።
6-አንተ የፍቅር ጥያቄ አቅርበህላት እሷ ግን ከባሏ ጋር ብታስተዋውቅህ ይህ “Supply and demand gap” የአቅርቦት እና የፍላጎት ክፍተት ነው።
7-አንተ ወደ እርሷ ሄደህ ምንም ከማለትህ በፊት ሚስትህ ብትመጣ እነዚህ አዳዲስ ገበያዎች ወደ አንተ እንዳይመጡ የቀረጥና የቦታ ገደቦች ተጥሎብሃል እንደማለት ያለህ ነው።
ይህ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ውስጥ ፕሮፌሰሩ ስለማርኬቲንግ ለተማሪዎቻቸው በአሪፍ እውነታ ምሳሌዎችን በመስጠት ያስረዱት ነው!
◆━━━━━━✎✦✎━━━━━━━◆
~ @open_reading1 ~
~ @open_reading1 ~
23.04.202517:56
የመጨረሻው ክፍል
እሷ ደንግጣ ፊቷ ሲቀላ ሮቤል ድክም ብሎ እየሳቀ ነው "ማለት ሊያስቃት እንደሚችል ሊያሳየኝ ነው?! ወይስ ምን እያደረገ ነው?!" እያልኩ ደምስሬ ሲገታተር ይሰማኛል። 'በሰላም የተኛሁትን ሰውዬ ቀስቅሶ ጠርቶ መበጥበጥ ምንድነው' ብዬ ስበሰጫጭ ቦርሳዋን ይዛ ስትወጣ አየኋት
እሱን ሳየው ግራ ገብቶት ከጓደኛዋ ጋር ስሟን ይጣራል እሷን ሳያት ስታየኝ ተገጣጠምን። በአይን ይለመናል?? በአይኔ ለመንኳት በአይኗ እምቢ አለቺኝ
ምን ብሏት ነው የሚል እልህ አነቀኝ። የከበቡኝን ሴቶች ገለል አድርጌ ሮቤል ጋር ሄድኩ። "ደሞ አንተ ምን ሆንክ" አለኝ ንዴቴን ሳልነገረው አውቆ "ምን ሆና ነው የወጣችው ምን አድርገሀት ነው የሄደችው"
"ምንም አላልኳትም ግን በሰበቡ ልታወራት ከፈለክ በእግሯ ስለሆነ የምትሄደው ብትሮጥ ትደርስባታለህ" አለኝ እየሳቀ አይ ሮቤል አሁን እኔ የእሱ ነገር ጠፍቶኝ በሱ መናደዴ እሱ እዚህ ይስቃል
"ጫማዋ ስለማያስኬዳት ባትሮጥም ትደርስባታለህ" አለች ጓደኛዋ
እውነትም እንዳሉት ብዙም ሳትርቅ ጫማዋን ለመፍታት ስትታገል አየኋት
እየሮጥኩ ሄጄ እግሯ ስር ተገኘሁ "ለመፍታት አስቸግሮሽ ከሆነ ልፍታልሽ" ብዬ እግሯ ስር ተንበረከኩ ዝም ብላ አየቺኝ እየፈታሁት
"ሮቤል ምንድነው ያለሽ" አልኳት ጫማዋን አውልቄ ባዶ እግሯን ቆማ እኔ በተንበረከኩበት
"ኧረ ቢያንስ ከተንበረከክበት ተነስ" አለች ፊቷ በደማቁ እየቀላ ድምጿም ሀምራዊ ነው
ስቆም አሁን ደግሞ ወደላይ አየቺኝ ቁመት በትንሹ እበልጣታለሁ አይኖቿ ያሳዝናሉ
"ንገሪኛ ምን ብሎሽ ነው" አልኳት
"ስምህ ኤርሚያስ መሆኑን ነግሮኝ ነው" ብላ ፊቷን ሸፈነችው
እንዳየቺኝ ሮቤል አውቆ ነበር?! ሮቤል ስላወቀባት አፍራ ነው የወጣችው?! ልቤ ደስታ ፈሰሰበት
"በቃ ይኸው ነው? የወጣሽው ለዚህ ብቻ አይደለም አይኖችሽ ሌላም ነገር ነግረውኛል እስክረዳሽ ግዜ አልሰጠሺኝም ንገሪኝ መጥቼ እስካወራሽ ለምን ቸኮልሽ ንገሪኝ" ብዬ እጆቿን ከፊቷ ላይ አነሳኋቸው
አምጣ አምጣ ቆይታ "መጎዳት ደክሞኛል"
እስካሁን ያዘነላት ልቤ አሁን እጥፉን አዘነላት
"ሰዓሊ እሱ ሲጎዳ እንጂ ሌሎችን ሲጎዳ ሰምተሽ ታውቂያለሽ?!" አልኳት መልሷን አልጠበኩም እቅፌ ውስጥ ከተትኳት እንደዚህ መቀራረብ እንድትፈራ ያደረጓትን ሰዎች እየረገምኩ ልጠብቃት ቃል ገባሁ
ቃሌንም ጠበቅኩ
ሞት እሷን ከእኔ እስኪነጥቃት መከዳትን አስረሳኋት የሚገባትን ፍቅር በምችለው ጥግ ደረስ ሰጠኋት አላሳፈረቺኝም እንደውም ህይወቴን አደመቀችው
እድሜ ለሮቤል
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
እሷ ደንግጣ ፊቷ ሲቀላ ሮቤል ድክም ብሎ እየሳቀ ነው "ማለት ሊያስቃት እንደሚችል ሊያሳየኝ ነው?! ወይስ ምን እያደረገ ነው?!" እያልኩ ደምስሬ ሲገታተር ይሰማኛል። 'በሰላም የተኛሁትን ሰውዬ ቀስቅሶ ጠርቶ መበጥበጥ ምንድነው' ብዬ ስበሰጫጭ ቦርሳዋን ይዛ ስትወጣ አየኋት
እሱን ሳየው ግራ ገብቶት ከጓደኛዋ ጋር ስሟን ይጣራል እሷን ሳያት ስታየኝ ተገጣጠምን። በአይን ይለመናል?? በአይኔ ለመንኳት በአይኗ እምቢ አለቺኝ
ምን ብሏት ነው የሚል እልህ አነቀኝ። የከበቡኝን ሴቶች ገለል አድርጌ ሮቤል ጋር ሄድኩ። "ደሞ አንተ ምን ሆንክ" አለኝ ንዴቴን ሳልነገረው አውቆ "ምን ሆና ነው የወጣችው ምን አድርገሀት ነው የሄደችው"
"ምንም አላልኳትም ግን በሰበቡ ልታወራት ከፈለክ በእግሯ ስለሆነ የምትሄደው ብትሮጥ ትደርስባታለህ" አለኝ እየሳቀ አይ ሮቤል አሁን እኔ የእሱ ነገር ጠፍቶኝ በሱ መናደዴ እሱ እዚህ ይስቃል
"ጫማዋ ስለማያስኬዳት ባትሮጥም ትደርስባታለህ" አለች ጓደኛዋ
እውነትም እንዳሉት ብዙም ሳትርቅ ጫማዋን ለመፍታት ስትታገል አየኋት
እየሮጥኩ ሄጄ እግሯ ስር ተገኘሁ "ለመፍታት አስቸግሮሽ ከሆነ ልፍታልሽ" ብዬ እግሯ ስር ተንበረከኩ ዝም ብላ አየቺኝ እየፈታሁት
"ሮቤል ምንድነው ያለሽ" አልኳት ጫማዋን አውልቄ ባዶ እግሯን ቆማ እኔ በተንበረከኩበት
"ኧረ ቢያንስ ከተንበረከክበት ተነስ" አለች ፊቷ በደማቁ እየቀላ ድምጿም ሀምራዊ ነው
ስቆም አሁን ደግሞ ወደላይ አየቺኝ ቁመት በትንሹ እበልጣታለሁ አይኖቿ ያሳዝናሉ
"ንገሪኛ ምን ብሎሽ ነው" አልኳት
"ስምህ ኤርሚያስ መሆኑን ነግሮኝ ነው" ብላ ፊቷን ሸፈነችው
እንዳየቺኝ ሮቤል አውቆ ነበር?! ሮቤል ስላወቀባት አፍራ ነው የወጣችው?! ልቤ ደስታ ፈሰሰበት
"በቃ ይኸው ነው? የወጣሽው ለዚህ ብቻ አይደለም አይኖችሽ ሌላም ነገር ነግረውኛል እስክረዳሽ ግዜ አልሰጠሺኝም ንገሪኝ መጥቼ እስካወራሽ ለምን ቸኮልሽ ንገሪኝ" ብዬ እጆቿን ከፊቷ ላይ አነሳኋቸው
አምጣ አምጣ ቆይታ "መጎዳት ደክሞኛል"
እስካሁን ያዘነላት ልቤ አሁን እጥፉን አዘነላት
"ሰዓሊ እሱ ሲጎዳ እንጂ ሌሎችን ሲጎዳ ሰምተሽ ታውቂያለሽ?!" አልኳት መልሷን አልጠበኩም እቅፌ ውስጥ ከተትኳት እንደዚህ መቀራረብ እንድትፈራ ያደረጓትን ሰዎች እየረገምኩ ልጠብቃት ቃል ገባሁ
ቃሌንም ጠበቅኩ
ሞት እሷን ከእኔ እስኪነጥቃት መከዳትን አስረሳኋት የሚገባትን ፍቅር በምችለው ጥግ ደረስ ሰጠኋት አላሳፈረቺኝም እንደውም ህይወቴን አደመቀችው
እድሜ ለሮቤል
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
Reposted from:
የሕይወት እምሻው ወጎች/ Hiwot Emishaw

22.04.202507:04
8123
<<<<<>>>>>>
ይሄኛውን ቴክስት የላከችልኝ ረቡዕ ነበር፡፡ በስራ ሰዓት ፡፡
‹‹ሄይ ቆንጂት…! እኔ የምልሽ፣ ሴቭ ዘ ችልደርን HR ውስጥ ያለ ሰው ታውቂያለሽ እንዴ? ››
ደምበኛ ሰላምታ የለ፣ ናፍቀሽኛል የለ፣ ደህና ነሽ ወይ የለ።
‹‹ሄይ ቆንጂት›› ያለችውም ለምትፈልገው ነገር ስታመቻቸኝ ነው፡፡
በረጅሙ ተነፈስኩ፡፡
ለስሙ ጓደኛሞች ነን፡፡
ለመጨረሻ ጊዜ ካወራን ግን ሁለት ወር ያልፈናል፡፡ ያኔም የሆነ ሰው ስልክ ቁጥር ፈልጋ ነው የደወለችልኝ፡፡አፍሪካ ህብረት የሚሰራ ሰው፡፡
…..ከዚያ በፊት ደግሞ የጻፈችልኝ ቴክስት፣
“ስሚማ ፍቅር፣ ያ ዩ ኤን ዲፒ የሚሰራው ሰውዬ ስልክ አለሽ እንዴ? ያ እንደውም ዶሎ አዶ ፕሮጀክት ማኔጀር የነበረው?” የሚል ነበር፡፡
ከዚያ በፊት ደግሞ አንዱን ቅዳሜ ጠዋት ምን ብላ ጽፋልኝ ነበር…?
አዎ…
“ሄይ….በናትሽ ያ የአጎትሽ ልጅ፣ ቴሌ የሚሰራው… አሁንም እዛ ነው እንዴ? ሲምካርዴ እኮ ድጋሚ ተዘጋብኝ”
እንዴት ነሽ፣ እንዴት አደርሽ እንኳን ሳትል፡፡
አንዱን ቀን ደሞ ለእኩለ ሌሊት ትንሽ ሲቀረው ደወለችና፣ በጣም ለምትፈልገው ስራ ልታስገባው የጻፈችውን ‹‹ሞቲቬሽን ሌተር›› ቶሎ ብዬ እንዳስተካክልላት ላከችልኝ፡፡
ወሊሶ ነበርኩ። ከስራ ድካም አረፍ ልበል ብዬ ቤተሰብ ጋር፡፡
ግን ጭንቀትዋን አየሁና፣ ‹‹እሺ ጠዋት አይቼ አስተካክልልሻለሁ›› ብያት ስልኩን ዘጋሁ፡፡
ማለዳ፣ ገና በቅጡ ሳይነጋ ደውላ ፣
“እ እንዴት አረግሽልኝ?” አለችኝ።
የናፈቀችኝ እናቴ ቤተክርስትያን አብሬያት እንድሄድ እየለመነችኝ ለእሷ ብዬ ቤት ቀረሁ፡፡
ይህ ከሆነ ከሶስት ሳምንት በኋላ ስትጠፋብኝ፣
‹‹እሺ፣ ያ ጉዳይ እንዴት ሆነልሽ..ተሳካ?›› ብዬ ስለስራው ስጠይቃት ሌላ ነገር ሳትለኝ፣ በብልጭልጭ መብራት ውስጥ የምትደንስ ትንሽዬ ልጅ "ጂ አይ ኤፍ "ብቻ ልካ ደግሞ እንደ ልማዷ ጥርቅም አድርጋ ዘጋችኝ፡፡
አንዴ ደግሞ ለራሴ እንኳን የምሳሳለትን ሀበሻ ቀሚሴን ለአክስቷ ልጅ ሰርግ ልትለብሰው አውሺን አለችኝ፡፡
አይሆንም ብላት
አጃቢ ነኝ ..
ደህና ነገር መልበስ አለብኝ…
ስሞትልሽ…ስከተፍልሽ
ምናምን ብላ አለቃቀሰችብኝ፡፡
ንዝንዝ ስታደርገኝ፣
‹‹ስሚ ! በእቁብ ነው የገዛሁት፡፡ አንድ ነገር ብታደርጊው የመጨረሻችን ነው፡፡ ደግሞ በስርአት ራስሽ አጥበሽ ነው የምትመልሺው›› ብዬ እያንገራገረኩ ሰጠኋት፡፡
እሺ እሺ ብላ፣ ምላ ተገዝታ ወሰደችው፡፡
በነጋታው አጥቤ አመጣለሁ እንዳላለችኝ በስንት ልመና ከአስር ቀን በኋላ የመለሰችልኝ በአሮጌ ኩርቱ ፌስታል ውስጥ ጎስጉሳው ነበር፡፡
አላጠበችውም፡፡
ላቧና ሽቶዋ ያበላሸውን ቦታ አይቼ ከንዴቴ ሳላገግም ጥለቱ ላይ አዋዜ መፍሰሱን ሳይ ጨስኩ፡፡
ያደረገችውን ነገር ስለምታውቅ ጥፍት አለች፡፡
ከብዙ ጊዜ በኋላ እንዲሁ ጉዷን ልይ እስቲ፣ ዝም ብዬ ሰላም ልበላት ብዬ ደወልኩላት።
ያው ስለማንገናኝ። ሁለቴ ጠራ፤ ስልኳን አላነሳችም።
ነገሩን ረስቼው፣ ከሶስት ቀን በኃላ ቴክስት ላከች፡፡
‹‹ ይቅርታ ብታይ አዲሱ ቦታ ስራ ብዝት ብሎብኛል። እኔ የምልሽ…የጥላ ስፓ ስልክ አለሽ አይደል? ዌብሳይታቸው ላይ ያለው አይሰራም፡፡ ካለሽ በናትሽ ቶሎ ላኪልኝ፡፡ ጀርባዬ ቆስሎልሻል፡፡ ዛሬውኑ ማሳጅ መሄድ አለብኝ።›› ይላል፡፡
እንደ ጓደኛ ለሆነ ጉዳይ ካላስፈለኳት አብረን ምሳ በልተን አናውቅም።
እሷን በሆነ መልኩ የማይጠቅማት ከሆነ ሻይ ቡና እንኳን አንባባልም።
ስንት አመት ሳባብላት ኖሬ፣ የእሷ ነገር የቆረጠልኝ ግን የሚከተለው ነገር ሲፈጠር ነው፡፡
እናቴ በጠና ታማ አዲሳባ አምጥቻት ሆስፒታል ገብታ ነበር፡፡
አንዱን ቀን ብቸኝነትና መከፋት ሲያሸንፉኝ ስለመታመሟ ፌስቡክ ላይ ፖስት አደረግኩ፡፡
ለራሴም በገረመኝ ፍጥነት ወዲያው ቴክስት አደረገችና፣
“ወይኔ የእኔ ቆንጆ ሶሪ…ማዘር ምን ሆና ነው…?እስኪ ማታ እደውልልሽና አወራሻለሁ።” አለች።
ሰው ባጣሁ ሰአት ሰው ልትሆን ነው ብዬ እንደ ሞኝ ጠበቅኳት፡፡
እሷ እቴ፡፡
አልደወለችም።
ከ አራት ወይ አምስት ቀን በኃላ ሌላ ቴክስት ላከች፡፡
“ፍቅርዬ፣ እማዬ እንዴት ሆነች? ተሻላት አይደል? በነገርሽ ላይ ባለፈው ፖስት ስታደርጊ ላንሴት ናት ብለሽ ነበር አይደል ? እስኪ ላንሴቶች ደህና neurosurgeon ካላቸው ጠይቂልኝ በናትሽ፡፡ አጎቴ ታሟል፡፡”
ስያሜ ልሰጠው ያልቻልኩት ስሜት ተሰማኝ፡፡ ዝም፣ ጭጭ አልኩ፡፡
ዝግት- ቁልፍ አደረግኳት፡፡
---
ይሄው ዛሬ፣ በረቡዕ ምድር፣ በስራ ሰአት፣ አይኗን በጨው እጥብ አድርጋ፣ ሌላ ውለታ ፈልጋ፣ የተፈጠረው ነገር ሁሉ እንዳልተፈጠረ፣ የሰራችኝን ነገር ሁሉ እንዳልሰራችኝ፣
‹‹ሄይ ቆንጂት…! እኔ የምልሽ፣ ሴቭ ዘ ቺልደርን HR ውስጥ ያለ ሰው ታውቂያለሽ እንዴ? ›› ብላ ቴክስት ላከችልኝ፡፡
ወዲያው አልመለስኩላትም፡፡
ለቡና ወጣሁ፡፡
ከባልደረቦቼ ጋር ምሳ በላሁ፡፡
እህቴ ጋር ደወልኩ፡፡ እናቴ መድሃኒቷን መውሰዷን አረጋገጥኩ፡፡
ከዚያ ግን መለስኩላት፣
‹‹አንቺ ግን በቃ ማፈር ተውሽ አይደል….?ለማንኛውም እስቲ ዛሬ እንኳን አፋላጊዎችን ጠይቂ፡፡ 8123 መሰለኝ ቁጥራቸው›› ብዬ፡፡
አልመለሰችልኝም፡፡
በዚያው ተቆራርጠን ቀረን፡፡
ለነገሩ እኔ አልቆርጥ አልኩ እንጂ እንደ ጓደኛ ከተቆራረጥን እኮ ቆየን፡፡
<<<<<>>>>>>
ይሄኛውን ቴክስት የላከችልኝ ረቡዕ ነበር፡፡ በስራ ሰዓት ፡፡
‹‹ሄይ ቆንጂት…! እኔ የምልሽ፣ ሴቭ ዘ ችልደርን HR ውስጥ ያለ ሰው ታውቂያለሽ እንዴ? ››
ደምበኛ ሰላምታ የለ፣ ናፍቀሽኛል የለ፣ ደህና ነሽ ወይ የለ።
‹‹ሄይ ቆንጂት›› ያለችውም ለምትፈልገው ነገር ስታመቻቸኝ ነው፡፡
በረጅሙ ተነፈስኩ፡፡
ለስሙ ጓደኛሞች ነን፡፡
ለመጨረሻ ጊዜ ካወራን ግን ሁለት ወር ያልፈናል፡፡ ያኔም የሆነ ሰው ስልክ ቁጥር ፈልጋ ነው የደወለችልኝ፡፡አፍሪካ ህብረት የሚሰራ ሰው፡፡
…..ከዚያ በፊት ደግሞ የጻፈችልኝ ቴክስት፣
“ስሚማ ፍቅር፣ ያ ዩ ኤን ዲፒ የሚሰራው ሰውዬ ስልክ አለሽ እንዴ? ያ እንደውም ዶሎ አዶ ፕሮጀክት ማኔጀር የነበረው?” የሚል ነበር፡፡
ከዚያ በፊት ደግሞ አንዱን ቅዳሜ ጠዋት ምን ብላ ጽፋልኝ ነበር…?
አዎ…
“ሄይ….በናትሽ ያ የአጎትሽ ልጅ፣ ቴሌ የሚሰራው… አሁንም እዛ ነው እንዴ? ሲምካርዴ እኮ ድጋሚ ተዘጋብኝ”
እንዴት ነሽ፣ እንዴት አደርሽ እንኳን ሳትል፡፡
አንዱን ቀን ደሞ ለእኩለ ሌሊት ትንሽ ሲቀረው ደወለችና፣ በጣም ለምትፈልገው ስራ ልታስገባው የጻፈችውን ‹‹ሞቲቬሽን ሌተር›› ቶሎ ብዬ እንዳስተካክልላት ላከችልኝ፡፡
ወሊሶ ነበርኩ። ከስራ ድካም አረፍ ልበል ብዬ ቤተሰብ ጋር፡፡
ግን ጭንቀትዋን አየሁና፣ ‹‹እሺ ጠዋት አይቼ አስተካክልልሻለሁ›› ብያት ስልኩን ዘጋሁ፡፡
ማለዳ፣ ገና በቅጡ ሳይነጋ ደውላ ፣
“እ እንዴት አረግሽልኝ?” አለችኝ።
የናፈቀችኝ እናቴ ቤተክርስትያን አብሬያት እንድሄድ እየለመነችኝ ለእሷ ብዬ ቤት ቀረሁ፡፡
ይህ ከሆነ ከሶስት ሳምንት በኋላ ስትጠፋብኝ፣
‹‹እሺ፣ ያ ጉዳይ እንዴት ሆነልሽ..ተሳካ?›› ብዬ ስለስራው ስጠይቃት ሌላ ነገር ሳትለኝ፣ በብልጭልጭ መብራት ውስጥ የምትደንስ ትንሽዬ ልጅ "ጂ አይ ኤፍ "ብቻ ልካ ደግሞ እንደ ልማዷ ጥርቅም አድርጋ ዘጋችኝ፡፡
አንዴ ደግሞ ለራሴ እንኳን የምሳሳለትን ሀበሻ ቀሚሴን ለአክስቷ ልጅ ሰርግ ልትለብሰው አውሺን አለችኝ፡፡
አይሆንም ብላት
አጃቢ ነኝ ..
ደህና ነገር መልበስ አለብኝ…
ስሞትልሽ…ስከተፍልሽ
ምናምን ብላ አለቃቀሰችብኝ፡፡
ንዝንዝ ስታደርገኝ፣
‹‹ስሚ ! በእቁብ ነው የገዛሁት፡፡ አንድ ነገር ብታደርጊው የመጨረሻችን ነው፡፡ ደግሞ በስርአት ራስሽ አጥበሽ ነው የምትመልሺው›› ብዬ እያንገራገረኩ ሰጠኋት፡፡
እሺ እሺ ብላ፣ ምላ ተገዝታ ወሰደችው፡፡
በነጋታው አጥቤ አመጣለሁ እንዳላለችኝ በስንት ልመና ከአስር ቀን በኋላ የመለሰችልኝ በአሮጌ ኩርቱ ፌስታል ውስጥ ጎስጉሳው ነበር፡፡
አላጠበችውም፡፡
ላቧና ሽቶዋ ያበላሸውን ቦታ አይቼ ከንዴቴ ሳላገግም ጥለቱ ላይ አዋዜ መፍሰሱን ሳይ ጨስኩ፡፡
ያደረገችውን ነገር ስለምታውቅ ጥፍት አለች፡፡
ከብዙ ጊዜ በኋላ እንዲሁ ጉዷን ልይ እስቲ፣ ዝም ብዬ ሰላም ልበላት ብዬ ደወልኩላት።
ያው ስለማንገናኝ። ሁለቴ ጠራ፤ ስልኳን አላነሳችም።
ነገሩን ረስቼው፣ ከሶስት ቀን በኃላ ቴክስት ላከች፡፡
‹‹ ይቅርታ ብታይ አዲሱ ቦታ ስራ ብዝት ብሎብኛል። እኔ የምልሽ…የጥላ ስፓ ስልክ አለሽ አይደል? ዌብሳይታቸው ላይ ያለው አይሰራም፡፡ ካለሽ በናትሽ ቶሎ ላኪልኝ፡፡ ጀርባዬ ቆስሎልሻል፡፡ ዛሬውኑ ማሳጅ መሄድ አለብኝ።›› ይላል፡፡
እንደ ጓደኛ ለሆነ ጉዳይ ካላስፈለኳት አብረን ምሳ በልተን አናውቅም።
እሷን በሆነ መልኩ የማይጠቅማት ከሆነ ሻይ ቡና እንኳን አንባባልም።
ስንት አመት ሳባብላት ኖሬ፣ የእሷ ነገር የቆረጠልኝ ግን የሚከተለው ነገር ሲፈጠር ነው፡፡
እናቴ በጠና ታማ አዲሳባ አምጥቻት ሆስፒታል ገብታ ነበር፡፡
አንዱን ቀን ብቸኝነትና መከፋት ሲያሸንፉኝ ስለመታመሟ ፌስቡክ ላይ ፖስት አደረግኩ፡፡
ለራሴም በገረመኝ ፍጥነት ወዲያው ቴክስት አደረገችና፣
“ወይኔ የእኔ ቆንጆ ሶሪ…ማዘር ምን ሆና ነው…?እስኪ ማታ እደውልልሽና አወራሻለሁ።” አለች።
ሰው ባጣሁ ሰአት ሰው ልትሆን ነው ብዬ እንደ ሞኝ ጠበቅኳት፡፡
እሷ እቴ፡፡
አልደወለችም።
ከ አራት ወይ አምስት ቀን በኃላ ሌላ ቴክስት ላከች፡፡
“ፍቅርዬ፣ እማዬ እንዴት ሆነች? ተሻላት አይደል? በነገርሽ ላይ ባለፈው ፖስት ስታደርጊ ላንሴት ናት ብለሽ ነበር አይደል ? እስኪ ላንሴቶች ደህና neurosurgeon ካላቸው ጠይቂልኝ በናትሽ፡፡ አጎቴ ታሟል፡፡”
ስያሜ ልሰጠው ያልቻልኩት ስሜት ተሰማኝ፡፡ ዝም፣ ጭጭ አልኩ፡፡
ዝግት- ቁልፍ አደረግኳት፡፡
---
ይሄው ዛሬ፣ በረቡዕ ምድር፣ በስራ ሰአት፣ አይኗን በጨው እጥብ አድርጋ፣ ሌላ ውለታ ፈልጋ፣ የተፈጠረው ነገር ሁሉ እንዳልተፈጠረ፣ የሰራችኝን ነገር ሁሉ እንዳልሰራችኝ፣
‹‹ሄይ ቆንጂት…! እኔ የምልሽ፣ ሴቭ ዘ ቺልደርን HR ውስጥ ያለ ሰው ታውቂያለሽ እንዴ? ›› ብላ ቴክስት ላከችልኝ፡፡
ወዲያው አልመለስኩላትም፡፡
ለቡና ወጣሁ፡፡
ከባልደረቦቼ ጋር ምሳ በላሁ፡፡
እህቴ ጋር ደወልኩ፡፡ እናቴ መድሃኒቷን መውሰዷን አረጋገጥኩ፡፡
ከዚያ ግን መለስኩላት፣
‹‹አንቺ ግን በቃ ማፈር ተውሽ አይደል….?ለማንኛውም እስቲ ዛሬ እንኳን አፋላጊዎችን ጠይቂ፡፡ 8123 መሰለኝ ቁጥራቸው›› ብዬ፡፡
አልመለሰችልኝም፡፡
በዚያው ተቆራርጠን ቀረን፡፡
ለነገሩ እኔ አልቆርጥ አልኩ እንጂ እንደ ጓደኛ ከተቆራረጥን እኮ ቆየን፡፡
Reposted from:
ጥበብ ፍልስፍና



14.04.202519:59
¹ አብ ልጁን ለደረው፣ ምን አስቀናት ፀሐይ?
ፊቷን ያጠቆረች፣ ዓለሙን እንዳያይ::
² ሊጠቅመው አስቦ፣ አባቱ በመላ
ላጀበው ሰው ሁሉ፣ ፅዋዉን ሳይሞላ
ልጁን ብቻ አጠጣዉ፣ የድግሱን ጠላ።
³ ደሀ አባት ደግሶ፣ ታዳሚዉን ሁሉ
በሬ ሳያዘጋጅ፣ ነው የጠራው አሉ፣
ካጀቡት ቡኋላ፣ ተጠምተው ተርበው
ከልጁ በስተቀር፣ የለም የሚያቀረበው።
⁴ ስንት ቢታረድ ነው፣ ምን ያክል ቢደገስ
ስጋዉ የሚበላዉ፣ እስከ ዛሬ ድረስ?
⁵ የተሰቀለዉን፣ ስጋዉን ሳይቀምሱ
አጃቢዎች ምነዉ፣ ተሻሙ ለልብሱ?
⁶ለሙሽራዉ ሀሞት፣ ምን ያህል ቢጥም ነው?
ለሚዜውቹ እንኳ፣ አላጠጣም ያለዉ?
@ethiosecret
ፊቷን ያጠቆረች፣ ዓለሙን እንዳያይ::
² ሊጠቅመው አስቦ፣ አባቱ በመላ
ላጀበው ሰው ሁሉ፣ ፅዋዉን ሳይሞላ
ልጁን ብቻ አጠጣዉ፣ የድግሱን ጠላ።
³ ደሀ አባት ደግሶ፣ ታዳሚዉን ሁሉ
በሬ ሳያዘጋጅ፣ ነው የጠራው አሉ፣
ካጀቡት ቡኋላ፣ ተጠምተው ተርበው
ከልጁ በስተቀር፣ የለም የሚያቀረበው።
⁴ ስንት ቢታረድ ነው፣ ምን ያክል ቢደገስ
ስጋዉ የሚበላዉ፣ እስከ ዛሬ ድረስ?
⁵ የተሰቀለዉን፣ ስጋዉን ሳይቀምሱ
አጃቢዎች ምነዉ፣ ተሻሙ ለልብሱ?
⁶ለሙሽራዉ ሀሞት፣ ምን ያህል ቢጥም ነው?
ለሚዜውቹ እንኳ፣ አላጠጣም ያለዉ?
@ethiosecret
19.04.202514:03
ሲመጣ አየሁት አረማመዱ ከራስ በተማመንም በላይ ኩራት አለበት። አልጣመኝም።
ሩትን "ማነው" አልኳት "እኔም አንቺም ካላወቅነው የሮቤል ጓደኛ ነው የሚሆነው" አለቺኝ
የሆነ አይነት ግርማ ሞገስ አለው የሚስብም የሚገፋም አይነት ነገር ሁለተኛ ያልጣመኝ ነገር
ገና ገብቶ አንዱ ጥግ ላይ ከመቀመጡ ሮቤል ካለበት ግርግር መሀል ወጥቶ ሄዶ ሰላም ብሎት ማውራት ጀመሩ። ሀሳቤን ወስዶት ሩት የምታወራውን እንኳን መስማት አቁሜያለሁ
"አንቺ ስሚኝ እንጂ ለ25 አመት ልደት የምን ግርግር ማብዛት ነው እያልኩሽ እኮ ነው አትሰሚኝም እንዴ" አለች ትከሻዬን ገፋ አድርጋ
"እህ??...አዎ... ይገርማል" አልኳት በደመ ነፍስ
ስለ ሮቤል ልደት ነው የምታወራው ልደቱን ማክበሩ ሳያንስ ጓደኞቹን በሙሉ ደግሶ መጥራቱ ገርሟታል።
እሷን ላወራ ዞሬ ስመለስ አይናችን ተገጣጠመ። የሚያስፈራ አስተያየት ውስጥ ማየት የሚችል የሚመስል የአይኑ አካባቢ አጥር እንዲሆነው ይመስል የጎደጎደ ጥልቅ አይን ቶሎ ብዬ አይኔን አሸሸሁ ሶስተኛ ያልጣመኝ ነገር
ወዲያው ሮቤል መጠጥ አምጥቶለት አብረው ተቀመጡ እኔ ላይ የሰራው መግነጢሳዊ ነገሩ ሌላውም ላይ ሰርቷል መሰል ቀስ ቀስ እያለ ሰዎች እየከበቡት መጡ
እንደውም ከዛ አቅጣጫ የሚመጣው የሴት ሳቅ ድምፅ በረከተ። በብዛት አይስቅም በሸራፋው በከንፈሩ ጠርዝ ነው ፈገግ የሚለው። በጣም ስለሚወደው ነገር እያወራ እንደሆነ ያስታውቃል እጁን ሰብስቦ በአይኑም በእጁም ነው የሚያወራው። በጣም ያልጣመኝ ከቀደሙት ሶስቱ የበለጠ ያልጣመኝ ነገር
እያየሁት ስብሰለሰል "ኤርሚያስ ነው ስሙ" አለኝ የሆነ ድምፅ ክው ብዬ ደንግጬ ስዞር ውስኪው ውስጥ በረዶውን እያሟሟ ብርጭቆውን እያሽከረከረ ሮቤል ቆሟል። ፊቱ ላይ ያ የማልወደው ፈገግታ ረብቧል።
"ማን ጠየቀህ አሁን" አልኩት ያልተበላሸውን ፀጉሬን እያስተካከልኩ
"የቀላው ጉንጭሽ" ብሎ ከት ብሎ ሳቀ
"አውቀህ ነው አይደል የጠራኸው?!" አልኩት
"አዎ ያው ምን አይነት እንደሚመችሽ ስለማውቅ ከልምድ በመነሳት ነው" አለ ፈገግታው ከፊቱ ሳይጠፋ
"ልሄድ ነው" አልኩት
"አታረጊውም" አለች ሩት የሰማችንም አልመሰለኝም ነበረ
"አትሄድም ባክሽ እንኳን ኤርሚን የመሰለ አግኝታ እንዲሁም ታቂያት የለ" አለ የድግስ ልክፍቴን ስለሚያቅ
"በሉ በሉ ቻው" ብዬ በአይኔ እንኳን ልሰናበተው ወደሱ ስዞር ድጋሜ ተገጣጠመ። አይናችን።
ይሄኔ run away በቃ ምንም የምጠብቀው ነገር የለም። ማንም ተመሳሳይ ስህተት እየደጋገመ አይሳሳትም። ያ ጊዜ አብቅቷል አይደል?! የሰዎችን ትኩረት ለማግኘት የምጋጋጥበት ለትንሽዬ ትኩረት የምዘልበት፥ ሁሉንም ጉረኛ ወንድ እንደ challenge የምቆጥርበት ወቅት አብቅቷል አይደል
ደህና ነበርኩ እኮ እስካየው ድረስ አሁንም ቢሆን አልረፈደም አሁን ተሻሽያለሁ መሄድ እችላለሁ ችግሮቼን ራሴ ላይ አልጠራም እንደውም መሄድ አይደለም እሮጣለሁ
"ኤፊ ኧረ ኤፍራታ..." ሩት ስትጣራ እየሰማሁ ጥያት በሩጫ እልም
ክፍል ሁለት ይቀጥል???
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
ሩትን "ማነው" አልኳት "እኔም አንቺም ካላወቅነው የሮቤል ጓደኛ ነው የሚሆነው" አለቺኝ
የሆነ አይነት ግርማ ሞገስ አለው የሚስብም የሚገፋም አይነት ነገር ሁለተኛ ያልጣመኝ ነገር
ገና ገብቶ አንዱ ጥግ ላይ ከመቀመጡ ሮቤል ካለበት ግርግር መሀል ወጥቶ ሄዶ ሰላም ብሎት ማውራት ጀመሩ። ሀሳቤን ወስዶት ሩት የምታወራውን እንኳን መስማት አቁሜያለሁ
"አንቺ ስሚኝ እንጂ ለ25 አመት ልደት የምን ግርግር ማብዛት ነው እያልኩሽ እኮ ነው አትሰሚኝም እንዴ" አለች ትከሻዬን ገፋ አድርጋ
"እህ??...አዎ... ይገርማል" አልኳት በደመ ነፍስ
ስለ ሮቤል ልደት ነው የምታወራው ልደቱን ማክበሩ ሳያንስ ጓደኞቹን በሙሉ ደግሶ መጥራቱ ገርሟታል።
እሷን ላወራ ዞሬ ስመለስ አይናችን ተገጣጠመ። የሚያስፈራ አስተያየት ውስጥ ማየት የሚችል የሚመስል የአይኑ አካባቢ አጥር እንዲሆነው ይመስል የጎደጎደ ጥልቅ አይን ቶሎ ብዬ አይኔን አሸሸሁ ሶስተኛ ያልጣመኝ ነገር
ወዲያው ሮቤል መጠጥ አምጥቶለት አብረው ተቀመጡ እኔ ላይ የሰራው መግነጢሳዊ ነገሩ ሌላውም ላይ ሰርቷል መሰል ቀስ ቀስ እያለ ሰዎች እየከበቡት መጡ
እንደውም ከዛ አቅጣጫ የሚመጣው የሴት ሳቅ ድምፅ በረከተ። በብዛት አይስቅም በሸራፋው በከንፈሩ ጠርዝ ነው ፈገግ የሚለው። በጣም ስለሚወደው ነገር እያወራ እንደሆነ ያስታውቃል እጁን ሰብስቦ በአይኑም በእጁም ነው የሚያወራው። በጣም ያልጣመኝ ከቀደሙት ሶስቱ የበለጠ ያልጣመኝ ነገር
እያየሁት ስብሰለሰል "ኤርሚያስ ነው ስሙ" አለኝ የሆነ ድምፅ ክው ብዬ ደንግጬ ስዞር ውስኪው ውስጥ በረዶውን እያሟሟ ብርጭቆውን እያሽከረከረ ሮቤል ቆሟል። ፊቱ ላይ ያ የማልወደው ፈገግታ ረብቧል።
"ማን ጠየቀህ አሁን" አልኩት ያልተበላሸውን ፀጉሬን እያስተካከልኩ
"የቀላው ጉንጭሽ" ብሎ ከት ብሎ ሳቀ
"አውቀህ ነው አይደል የጠራኸው?!" አልኩት
"አዎ ያው ምን አይነት እንደሚመችሽ ስለማውቅ ከልምድ በመነሳት ነው" አለ ፈገግታው ከፊቱ ሳይጠፋ
"ልሄድ ነው" አልኩት
"አታረጊውም" አለች ሩት የሰማችንም አልመሰለኝም ነበረ
"አትሄድም ባክሽ እንኳን ኤርሚን የመሰለ አግኝታ እንዲሁም ታቂያት የለ" አለ የድግስ ልክፍቴን ስለሚያቅ
"በሉ በሉ ቻው" ብዬ በአይኔ እንኳን ልሰናበተው ወደሱ ስዞር ድጋሜ ተገጣጠመ። አይናችን።
ይሄኔ run away በቃ ምንም የምጠብቀው ነገር የለም። ማንም ተመሳሳይ ስህተት እየደጋገመ አይሳሳትም። ያ ጊዜ አብቅቷል አይደል?! የሰዎችን ትኩረት ለማግኘት የምጋጋጥበት ለትንሽዬ ትኩረት የምዘልበት፥ ሁሉንም ጉረኛ ወንድ እንደ challenge የምቆጥርበት ወቅት አብቅቷል አይደል
ደህና ነበርኩ እኮ እስካየው ድረስ አሁንም ቢሆን አልረፈደም አሁን ተሻሽያለሁ መሄድ እችላለሁ ችግሮቼን ራሴ ላይ አልጠራም እንደውም መሄድ አይደለም እሮጣለሁ
"ኤፊ ኧረ ኤፍራታ..." ሩት ስትጣራ እየሰማሁ ጥያት በሩጫ እልም
ክፍል ሁለት ይቀጥል???
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
Reposted from:
ጥርኝ ጥበብ

18.04.202508:46
እኛ ያመጣናቸው እነርሱ በለጡን
እንኳን አደረሳችሁ
እየጎተንት ወደ ቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ይዘነው ገባን።የገዛንለትን ነጠላ ዘርግቶ ለመልበስ ግራ ሲጋባ ከሶስታችን መሀከል አንድኛው ተጠግቶ በአንገቱ ስል አመሳቅሎ አጣፋለትና
"እንዲህ አይሰገድም እሽ
እሽ
ምግብስ በልተሀል
ኧረ አልበላሁም
አዎ ምን ሆነሀላ ውሀ ራሱ ከጠጣህ ነገር ተበላሽቷል በቃ
አይ እንደዚያ አላደረኩም" ይቁነጠነጣል...በመሀል 1000 ሰግደን ለመውጣት የምንገፋፋው እኛ ቆመን ሳለ እርሱ ስድስት ሰባት ጊዜ ከፍ ዝቅ ብሎ ጉልበቱ እንደተብረከረከ ሰው በግንባሩ መሬቱን ተደግፎት ቀረ። እንግድህ ላለመነሳት ምክንያት እየፈጠረ መሆኑ ነው ቀና ማለት እንደከበደው ሰው ቁና ቁና ሲተነፍስ ይሰማናል።...
"ቃል እንደጓደኛ ይሄንን ልጅ ምንም መላ አናበጅለትም ማለት ነው"አለ ቢታንያ ወደ አንገቴ ተጠግቶ ... እኔ ደግሞ የአናንያን ህይወት እየሄደ ካለበት ቁልቁለት ለመመለስ መሞከር ውሀን ሽቅብ የማፍሰስ ያህል ድካሙ ብቻ ነው የሚታየኝ። ለጓደኛ በዚህ ልክ
መጠን ዝሎ መኖር ቢያሳፍርም... "ሱስ እኮ ነው እየበዛ በጣም ብሶበታል የት እናስጠምቀው በእናትህ" የየግል አስተያየታችንን ለጣጥፈን ስናበቃ ካጎነበሰበት በርከክ ብሎ አንገቱን ደፍቶ ነጠላውን አናቱ ላይ ጎዝጉዞ ተቀመጠ።
ለካ መቆም ቢያፍር ነው እንባ አርግዞ የወደቀው ድንገት ቀና ሲል ደንግጠን ተያየን በስጋው ላይ እንደተቆጣ የሚያሳብቁት የደም ስሮች ከወደግንባሩ እንድህ ተከታትለው ለመሰለፍ ምን አነቃቃቸው ከምኔው ፊቱ በእምባ ረጠበ አያስቀናም ልታፀድቁ በገሰፃችሁት ሰው ተሰብካችሁ እንደመሄድ ያለ ስብከት ወደየት ይገኛል።
የእኛ ፀፀት አርባአንድ ኪራላይሶን ብለን ከአይናችን ካልወረደ ለእርሱ በሰባት ዝቅ ማለት በዘነበለት እምባ እንዴት አይቀናም አምላኩ በልቡ አደባባይ በታተመለት ሰው ቁኑ ሀቁም ይሄው ነው።
በልምድ መመላለስ የፀና ሐዋርያም አንዳንድ ጊዜ ሊያፀድቅ ይዞ ከመጣው ወንበዴ ተምሮ ይሄዳል።...
ወዮ የሠው ስግደት ቆጥረን ለተመለስን 😢😢😢
ፀሀፊ ✍ ጌታሁን ደጉ
እንኳን አደረሳችሁ
23.04.202510:50
ወገኖቼ ትንሽ busy ሆኜ ነው ዛሬ ማታ ጠብቁ ክፍል ሁለት ይለቀቃል
17.04.202518:04
ባህላዊ date
"ከዚህ በኋላ ባንገናኝ ደስ ይለኛል አልኩት" አለች እጇን አጣምራ
"ማለት?! date ማድረግ ከጀመራችሁ ስንት ጊዜያችሁ ቢሆን ነው?!"
"ሁለት ወይ ሶስት ወር እኔንጃ" ትከሻዋን ሰበቀች
ግራ ገባኝ "ቆይ date ማድረግ ቀልድ ነው እንዴ?! እኔስ የማዝነው ለወንዶቹ ነው" አልኳት
"እዚህ ጋር እኮ ነው እኔና አንቺ የማንስማማው date ማድረግ ማለት እኮ ዘሎ ፍቅረኛሞች ሆኖ boyfriend girlfriend ለመባባል አይደለም ለመተዋወቅ ነው አሁን እኮ ነገር አለሙ ተቀላቅሎብን ነው እንጂ የድሮ date እና ትዳር ቢሆን..."
"ስለ arranged marriage ነው የምታወሪው?!" አልኳት ቅንድቤን ሰቅዬ
"አዎ በቤተሰብ ምርጫ ቤተሰብ ያለበት dating ማድረግ ማለት ነው። ለምን እንደሚጠቅም ታውቂያለሽ ዘሎ አካላዊ ነገር ውስጥ እንዳይገቡ ይጠብቋቸዋል ሌላስ አትዪም?!" አለች እጇን እየሰበሰበች
"ሌላስ"
"ከዛ ደግሞ መጠየቅ ያለባቸው ነገሮች መጠየቃቸውን ቤተሰብ check ያደርጋል 'ፍቅር ነው ታውረናል' ምናምን እንዳይሉ ማለት ነው። እንደውም የዛ ዘመን ትዳሮች ፍቺ በብዛት አይጎበኛቸውም ነበረ የዘንድሮ በእውር ድንብር እየተገባ እኮ ነው"
"ይሄ ካንቺ ጋር እንዴት ይገናኛል?!"አልኳት እየሳቅኩ
"እንዴት ይገናኛል መሰለሽ ዘመኑ አሁን የነገርኩሽን የdating መንገድ አልፎበታል ቢልም arranged marriage የፋራ ተብሎ ቢቀርም እኔ ለራሴ የቤተሰቦቼን ሀላፊነት ነው እየተወጣሁ ያለሁት date ነው ያደረግነው በይፋ የተባለ ነገር የለም"
"ስለዚህ ተጠናናን ነው የምትዪኝ እና ምኑ ነው ያልጣመሽ" አልኳት ገርማኝ
"ከአንድ መንገደኛ የተሻለ ሊያደንቀኝ አልቻለም 'አይንሽ ያምራል ቁመናሽ ቀሚስሽ' ምናምን ለራሴ ታክቶኛል" አለች በስጨት ብላ
"ማለት ወዶ አይደለም እኮ አትፍረጂበት" አልኳት የተዋጣላት ቆንጆ መሆኗን ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው
"ማድነቁ እኮ አይደለም ምን የሰፈር ተላካፊው እንኳን ያደንቅ አይደል?! ግን ጊዜ መስጠት ማለት ይሄ ከሆነ መግባባት ማውራት ጊዜ ማሳለፍ ምናምን ከአካላዊ አድናቆት ካላሳለፈን አስቸጋሪ ነው"
"በቃ?!" ለመለያየት የምታቀርባቸው መስፈርቶች እያስገረሙኝ መጥተዋል
"አልገባሽም እንዴ?! የማወራውን ካልሰማኝ የመልኬን ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰቤ ማማር ካልታየው ይሄ እኮ ፍቅር አይደለም"
"እና ምንድነው"
"ምኞት ነዋ አፍጥጦ ሰምቶሽ ያልሽውን አንዱንም ካልሰማ ወይ ሀሳቡ ሌላ ጋር ነው ወይ ደግሞ ከአካላዊ ምኞት የዘለለ አላማ የለውም ማለት ነው"
"ነገረሽዋል ግን" አልኳት ባላወቀበት እየተጨፈጨፈ ከሆነ ብዬ
"አዎ ብዙ ግዜ አውርተንበታል ያው ሁሉንም በንግግር የሚፈታ ሳይሆን ግዜ የሚፈታው ስለሆነ በሰላም ተለያየን እልሻለሁ"
"ፐ ዘመናዊነት ብዬ እንዳላደንቅሽ ይሄ ዘመናዊነት አይደለም ግን ጥሩ ነገር ስለሆነ ያወራሽው ይሁን አልኳት
እንደዚህ ስሜት ላይ ጥገኛ ሳይሆኑ ውሳኔ መወሰን ምንኛ መታደል ነው
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
"ከዚህ በኋላ ባንገናኝ ደስ ይለኛል አልኩት" አለች እጇን አጣምራ
"ማለት?! date ማድረግ ከጀመራችሁ ስንት ጊዜያችሁ ቢሆን ነው?!"
"ሁለት ወይ ሶስት ወር እኔንጃ" ትከሻዋን ሰበቀች
ግራ ገባኝ "ቆይ date ማድረግ ቀልድ ነው እንዴ?! እኔስ የማዝነው ለወንዶቹ ነው" አልኳት
"እዚህ ጋር እኮ ነው እኔና አንቺ የማንስማማው date ማድረግ ማለት እኮ ዘሎ ፍቅረኛሞች ሆኖ boyfriend girlfriend ለመባባል አይደለም ለመተዋወቅ ነው አሁን እኮ ነገር አለሙ ተቀላቅሎብን ነው እንጂ የድሮ date እና ትዳር ቢሆን..."
"ስለ arranged marriage ነው የምታወሪው?!" አልኳት ቅንድቤን ሰቅዬ
"አዎ በቤተሰብ ምርጫ ቤተሰብ ያለበት dating ማድረግ ማለት ነው። ለምን እንደሚጠቅም ታውቂያለሽ ዘሎ አካላዊ ነገር ውስጥ እንዳይገቡ ይጠብቋቸዋል ሌላስ አትዪም?!" አለች እጇን እየሰበሰበች
"ሌላስ"
"ከዛ ደግሞ መጠየቅ ያለባቸው ነገሮች መጠየቃቸውን ቤተሰብ check ያደርጋል 'ፍቅር ነው ታውረናል' ምናምን እንዳይሉ ማለት ነው። እንደውም የዛ ዘመን ትዳሮች ፍቺ በብዛት አይጎበኛቸውም ነበረ የዘንድሮ በእውር ድንብር እየተገባ እኮ ነው"
"ይሄ ካንቺ ጋር እንዴት ይገናኛል?!"አልኳት እየሳቅኩ
"እንዴት ይገናኛል መሰለሽ ዘመኑ አሁን የነገርኩሽን የdating መንገድ አልፎበታል ቢልም arranged marriage የፋራ ተብሎ ቢቀርም እኔ ለራሴ የቤተሰቦቼን ሀላፊነት ነው እየተወጣሁ ያለሁት date ነው ያደረግነው በይፋ የተባለ ነገር የለም"
"ስለዚህ ተጠናናን ነው የምትዪኝ እና ምኑ ነው ያልጣመሽ" አልኳት ገርማኝ
"ከአንድ መንገደኛ የተሻለ ሊያደንቀኝ አልቻለም 'አይንሽ ያምራል ቁመናሽ ቀሚስሽ' ምናምን ለራሴ ታክቶኛል" አለች በስጨት ብላ
"ማለት ወዶ አይደለም እኮ አትፍረጂበት" አልኳት የተዋጣላት ቆንጆ መሆኗን ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው
"ማድነቁ እኮ አይደለም ምን የሰፈር ተላካፊው እንኳን ያደንቅ አይደል?! ግን ጊዜ መስጠት ማለት ይሄ ከሆነ መግባባት ማውራት ጊዜ ማሳለፍ ምናምን ከአካላዊ አድናቆት ካላሳለፈን አስቸጋሪ ነው"
"በቃ?!" ለመለያየት የምታቀርባቸው መስፈርቶች እያስገረሙኝ መጥተዋል
"አልገባሽም እንዴ?! የማወራውን ካልሰማኝ የመልኬን ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰቤ ማማር ካልታየው ይሄ እኮ ፍቅር አይደለም"
"እና ምንድነው"
"ምኞት ነዋ አፍጥጦ ሰምቶሽ ያልሽውን አንዱንም ካልሰማ ወይ ሀሳቡ ሌላ ጋር ነው ወይ ደግሞ ከአካላዊ ምኞት የዘለለ አላማ የለውም ማለት ነው"
"ነገረሽዋል ግን" አልኳት ባላወቀበት እየተጨፈጨፈ ከሆነ ብዬ
"አዎ ብዙ ግዜ አውርተንበታል ያው ሁሉንም በንግግር የሚፈታ ሳይሆን ግዜ የሚፈታው ስለሆነ በሰላም ተለያየን እልሻለሁ"
"ፐ ዘመናዊነት ብዬ እንዳላደንቅሽ ይሄ ዘመናዊነት አይደለም ግን ጥሩ ነገር ስለሆነ ያወራሽው ይሁን አልኳት
እንደዚህ ስሜት ላይ ጥገኛ ሳይሆኑ ውሳኔ መወሰን ምንኛ መታደል ነው
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
Reposted from:
...ነጠብጣብ ✨💙



04.04.202509:54
✨
✍️👆
https://t.me/yeesua_queen
ብርጭቆ ግን እስከመቼ ነው የሰበረው እያለ ያነሳውን የሚቆርጠው...???
✍️👆
https://t.me/yeesua_queen
Reposted from:
ሚኪያስ ፈይሣ

07.04.202512:58
የኔ ልዕልት ፡ ስሚኝ አሁን
አይጠፋሽም
ውስጥሽ ያውቃል፤
ችግር አቅፈን ምናድርበት
የስካሁኑ ጊዜ ይበቃል።
ምናድግበት ሚስጥር ታየኝ
ሰውነቴን ሀሴት ዋጠው፤
ግድ የለሽም ትንሽ ቆርሰን
ፍቅራችንን እንሽጠው!።
የሚገዛ ሀገር ሞልቷል..
ነጠላ ነው ሚገጥመኝ ሰው
ብቸኛ ነው የማየውም፤
የከተማው ባለትዳር
ገንዘብ እንጂ ፍቅር የለውም።
ያሳዝናል ቀዬው ብታይ
እስቲ ይቅመሰው የኛን መገን፤
ፍቅር እንደሆን ሞልቶን ተርፏል
ትንሽ ካሽ ነው ሚያስፈልገን።
እንዳትሰጊ ፡ አንዲት እንኳን
ይሄ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
አልኳትና በረብጣ ብር
ከኛ ሰፍረን ፍቅር ሸጥን!።
ከዛን..
ተመቻቸን
ህይወት ደላን
ገርበብ አለ የአይናችን ዘብ፤
"ያለፈው ዓለም አይገባው
ፍቅር ኖሮት ያጣ ገንዘብ።"
ብለን ሳቅን
ተቃቀፍን
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ዓለም ለኛ ገነት ሆነች
ምድር ሆነች የኛ ተድላ።
የመንደሩን አይን ገዛን
ታላቅ ታናሽ አከበረን ፤
ሁሉ ሞልቶን ተደላድሎ
ትንሽ ብቻ ፡ ገንዘብ ቀረን።
ሰልችቶናል ስናገኘው
አሸዋ ላይ መልክን መሳል፤
ለታደልነው ብዙ ምኞት
የነበረን ገንዘብ ያንሳል።
ሰማዩ ላይ ስናማትር፡
መርከቡ ላይ ስናማትር፡
ስናይ ውለን የባህሩን
ግራ የገባው ፡ ውዝዋዜ ፤
ቁጭ ስንል ሀሳብ መጣ
አለን ለካ ፡ ብዙ ጊዜ!።
ተነጋገርን
ተማከርን
ካረጀ ሀብታም አንጋጠጥን፤
ሻንጣ ሙሉ ገንዘብ ወስደን
ሽርፍራፊ ጊዜ ሸጥን!።
አቤት ሀሴት
አቤት ፌሽታ
ህዝቡ ባዶ ቅኔ ያምጣል፤
ገንዘብ ደስታ ባይገዛ እንኳን
እልፍ ደስታ ይዞ ይመጣል።
የሚያቆመን ፍጥረት ጠፋ
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ግን አሁንም አልተነሳም
የህዝባችን አይነ-ጥላ!።
ምናገባን እኛ ኖርን
እኛ ኖርን ምናገባን፤
ግን አንድ ሌት በህልማችን
ስልል ያለ ሀሳብ ገባን፦
"ፍቅራችንን ከላይ አይቶ
ይህን ፀጋ እርሱ ሰጠን፤
አንድ ወንበዴ ገፍቶ ቢዘርፍ
ምንድነው ግን የሚውጠን?"
ብለን አሰብን
ተብከነከን
ያ ደላላ ፡ መጣ ዳግም፤
ያገናኘን ፅኑ መድህን
ከፍቅር ውጪ አይፈልግም።
ተመካከርን .... በቃ ይሁን!
ይህ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
ብለን ትንሽ ፡ የማትጎዳ
በድጋሚ ፡ ፍቅር ሸጥን!።
እርሱ ይክበር
ሰላም ተኛን
ህልማችንን እርሱ ረዳ፤
የሚጣፍጥ ለሊት አድረን
ደግሞ ነቃን በማለዳ።
ግና...
የትላንቱ ህመም ቢሻር
ምቾት ዛሬን ቢንሰራፋም፦
እየሳቅን ውለን አድረን
የሚያውከን ነገ አይጠፋም።
ትንሽ ብለን ፦ ስንቀንስ
ጥቂት ብለን ስናወጣ፥
እለት በለት እ.የ.ባ.ሰ
ያልታሰበ ጉድ ሲመጣ፤
ትንሽ ፍቅር ፣ ትንሽ ጊዜ
ትንሽ .. ትንሽ "ትልቅ" ሆኖ ፤
ሳናስተውል ያለን ፍቅር
በየዳናው ተበትኖ ፤
ዝም ማለት ልማድ ሆነን
መቀላለድ ወዙ ጠፋን
ደስታችንን ለማስቀጠል
አንጀት ቋጥረን ብዙ ለፋን።
ግን አልሆነም ውጥናችን
ቅዠት ገዛን ተገላብጦ፤
ህይወታችን መንቀፍ ሆነ
ያንዱን ድክመት ብቻ መርጦ።
"አንተ እኮ ነህ እንዲህ ያልከኝ"
"አንቺ እኮ ነሽ እንዲ ያረግሽው"፥
"ከዚህ ኋላ ይሄ በቃኝ"
"የስካሁኑን ፍቅር እርሺው!"።
ተቃቃርን እንደ ሩቅ ሰው
ባላንጣ ሆንን በኛው ሜዳ
እንስፍስፉን አንጀት ጥለን
በአዳር ሆንን እንደ ባዳ።
አንገርምም?
ወዳጅ ዘመድ በርቱ ሲለን
ሲቀናብን የውጪ ሰው፤
ያቀፍነውን ጥሬ ገንዘብ
አይነተን ቆጥረን ሳንጨርሰው፥
ከጓዳችን ተትረፍርፎ
ንዋይ ፣ ዝና ፣ ሀብት ፣ ስልጣን፤
ከባድ ቀንን ምናልፍበት
ቅንጥብጣቢ ፍቅር አጣን!።
@mikiyas_feyisa
አይጠፋሽም
ውስጥሽ ያውቃል፤
ችግር አቅፈን ምናድርበት
የስካሁኑ ጊዜ ይበቃል።
ምናድግበት ሚስጥር ታየኝ
ሰውነቴን ሀሴት ዋጠው፤
ግድ የለሽም ትንሽ ቆርሰን
ፍቅራችንን እንሽጠው!።
የሚገዛ ሀገር ሞልቷል..
ነጠላ ነው ሚገጥመኝ ሰው
ብቸኛ ነው የማየውም፤
የከተማው ባለትዳር
ገንዘብ እንጂ ፍቅር የለውም።
ያሳዝናል ቀዬው ብታይ
እስቲ ይቅመሰው የኛን መገን፤
ፍቅር እንደሆን ሞልቶን ተርፏል
ትንሽ ካሽ ነው ሚያስፈልገን።
እንዳትሰጊ ፡ አንዲት እንኳን
ይሄ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
አልኳትና በረብጣ ብር
ከኛ ሰፍረን ፍቅር ሸጥን!።
ከዛን..
ተመቻቸን
ህይወት ደላን
ገርበብ አለ የአይናችን ዘብ፤
"ያለፈው ዓለም አይገባው
ፍቅር ኖሮት ያጣ ገንዘብ።"
ብለን ሳቅን
ተቃቀፍን
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ዓለም ለኛ ገነት ሆነች
ምድር ሆነች የኛ ተድላ።
የመንደሩን አይን ገዛን
ታላቅ ታናሽ አከበረን ፤
ሁሉ ሞልቶን ተደላድሎ
ትንሽ ብቻ ፡ ገንዘብ ቀረን።
ሰልችቶናል ስናገኘው
አሸዋ ላይ መልክን መሳል፤
ለታደልነው ብዙ ምኞት
የነበረን ገንዘብ ያንሳል።
ሰማዩ ላይ ስናማትር፡
መርከቡ ላይ ስናማትር፡
ስናይ ውለን የባህሩን
ግራ የገባው ፡ ውዝዋዜ ፤
ቁጭ ስንል ሀሳብ መጣ
አለን ለካ ፡ ብዙ ጊዜ!።
ተነጋገርን
ተማከርን
ካረጀ ሀብታም አንጋጠጥን፤
ሻንጣ ሙሉ ገንዘብ ወስደን
ሽርፍራፊ ጊዜ ሸጥን!።
አቤት ሀሴት
አቤት ፌሽታ
ህዝቡ ባዶ ቅኔ ያምጣል፤
ገንዘብ ደስታ ባይገዛ እንኳን
እልፍ ደስታ ይዞ ይመጣል።
የሚያቆመን ፍጥረት ጠፋ
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ግን አሁንም አልተነሳም
የህዝባችን አይነ-ጥላ!።
ምናገባን እኛ ኖርን
እኛ ኖርን ምናገባን፤
ግን አንድ ሌት በህልማችን
ስልል ያለ ሀሳብ ገባን፦
"ፍቅራችንን ከላይ አይቶ
ይህን ፀጋ እርሱ ሰጠን፤
አንድ ወንበዴ ገፍቶ ቢዘርፍ
ምንድነው ግን የሚውጠን?"
ብለን አሰብን
ተብከነከን
ያ ደላላ ፡ መጣ ዳግም፤
ያገናኘን ፅኑ መድህን
ከፍቅር ውጪ አይፈልግም።
ተመካከርን .... በቃ ይሁን!
ይህ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
ብለን ትንሽ ፡ የማትጎዳ
በድጋሚ ፡ ፍቅር ሸጥን!።
እርሱ ይክበር
ሰላም ተኛን
ህልማችንን እርሱ ረዳ፤
የሚጣፍጥ ለሊት አድረን
ደግሞ ነቃን በማለዳ።
ግና...
የትላንቱ ህመም ቢሻር
ምቾት ዛሬን ቢንሰራፋም፦
እየሳቅን ውለን አድረን
የሚያውከን ነገ አይጠፋም።
ትንሽ ብለን ፦ ስንቀንስ
ጥቂት ብለን ስናወጣ፥
እለት በለት እ.የ.ባ.ሰ
ያልታሰበ ጉድ ሲመጣ፤
ትንሽ ፍቅር ፣ ትንሽ ጊዜ
ትንሽ .. ትንሽ "ትልቅ" ሆኖ ፤
ሳናስተውል ያለን ፍቅር
በየዳናው ተበትኖ ፤
ዝም ማለት ልማድ ሆነን
መቀላለድ ወዙ ጠፋን
ደስታችንን ለማስቀጠል
አንጀት ቋጥረን ብዙ ለፋን።
ግን አልሆነም ውጥናችን
ቅዠት ገዛን ተገላብጦ፤
ህይወታችን መንቀፍ ሆነ
ያንዱን ድክመት ብቻ መርጦ።
"አንተ እኮ ነህ እንዲህ ያልከኝ"
"አንቺ እኮ ነሽ እንዲ ያረግሽው"፥
"ከዚህ ኋላ ይሄ በቃኝ"
"የስካሁኑን ፍቅር እርሺው!"።
ተቃቃርን እንደ ሩቅ ሰው
ባላንጣ ሆንን በኛው ሜዳ
እንስፍስፉን አንጀት ጥለን
በአዳር ሆንን እንደ ባዳ።
አንገርምም?
ወዳጅ ዘመድ በርቱ ሲለን
ሲቀናብን የውጪ ሰው፤
ያቀፍነውን ጥሬ ገንዘብ
አይነተን ቆጥረን ሳንጨርሰው፥
ከጓዳችን ተትረፍርፎ
ንዋይ ፣ ዝና ፣ ሀብት ፣ ስልጣን፤
ከባድ ቀንን ምናልፍበት
ቅንጥብጣቢ ፍቅር አጣን!።
@mikiyas_feyisa
Reposted from:
ጥንቅሻ✍🏼🦋

13.04.202518:49
ደብዘዝ ያለ ቀይ፣ ነጫጭ ትናንሽ አበቦች ምስል ያለበት ረዘም ያለ የሚያምር ቀሚሷን ለብሳ ፀጉሯን እንዲሁ አሲዛ ከሁዋላ ለቃዋለች፣
ከፍ ያለ ጫማ ነው ያደረገችው....
ነጭ ቦርሳዋን ይዛ ወደ ቢሮ ስትገባ ሳያት ተነስተህ እቀፋት እቀፋት አለኝ....
ከውስጤ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ነው የተሰማኝ ሳላውቀው ፈገግ አልኩኝ፣
ለልብ ትግል የለውም፣ እንዲሁ ይለመዳል፣ ከአንድ ዕይታ ጀምሮ ራስን እስከመስጠት ይጠልቃል...ይሰፋል፤
ድንገት የሚወደውን አይቶ ስራው የሚጠፋበትን፣ በደስታ የሚዋኝን...እንዴት ነው ሳይማር መውደድ ያወቀን ልብ "ተው" ተብሎ አለመውደድ፤
አለማፍቀር የምናስተምረው?
ከፍ ያለ ጫማ ነው ያደረገችው....
ነጭ ቦርሳዋን ይዛ ወደ ቢሮ ስትገባ ሳያት ተነስተህ እቀፋት እቀፋት አለኝ....
ከውስጤ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ነው የተሰማኝ ሳላውቀው ፈገግ አልኩኝ፣
ለልብ ትግል የለውም፣ እንዲሁ ይለመዳል፣ ከአንድ ዕይታ ጀምሮ ራስን እስከመስጠት ይጠልቃል...ይሰፋል፤
ድንገት የሚወደውን አይቶ ስራው የሚጠፋበትን፣ በደስታ የሚዋኝን...እንዴት ነው ሳይማር መውደድ ያወቀን ልብ "ተው" ተብሎ አለመውደድ፤
አለማፍቀር የምናስተምረው?
27.03.202508:39
#13
በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት
አለም አንድ ናት ሲባል እኔ ፕላኔቶቼን የምቆጥረው ከርሷ አካል ነበር።
አለሜ ስላት ሁሉ እኔነቴን በመስጠት መሀል ስላገኘኃት ነበር....ያሳለፍነውን ሳስብ ወደ ፊት ምንም ማለፍ እንደማያቅተን በሙሉ ልብ ሳወራ እገኛለው።።።ለምን?ብባል መልሴ...የርሷ ጥንካሬና የእኔ ትግስት አብሮ መጓዙ ለዚህ አብቅቶናል......ዳሩ ነበርነት መሀል ተሰይመን ተገኘን......ቅድሚያውኑ.....
ነበርነቴ የጀመረው ያን ዕለት ..ነው...
ንዴት፤ብስጭት፤ጭንቀት፤ፍርሀት፤ራስን ማጣት ውስጤ የነበሩ ዕለት ፊቴ የነበረችው እርሷ ነበረች።የዳበስኩት እሷነቷን ሌላ ጋር ሳገኘው....በሳቀችልኝ ጥርሶቿ እርሱ ጋር ስንቴ እንደሳቀች እያሰብኩ እኔነቴ ከላዬ ሲወርድ ታወቀኝ....ዝም ብላ አይኔን መመልከቷ አበሳጨኝ ንቄሀለው...አሳፋሪ ስራ አልሰራውም አይነት አተያይ እያየችኝ አገኘኃት።
አብራት ኗሪው ላይ ትኩረቴ አልነበረም የኔ የሆነ ላይ ነው እይታዬ
የኔ የነበረ.....
ድንገት ብቻችንን ሆንን ይብረር..ይሩጥ ሳላውቅ ያ ሰው ፊቴ አልነበረም።
እኛነታችንን እንደ ቀላል በስሜት ግለት ስትጫወትበት እንደቆየች ሳስብ...ማሰቢያዬ ራሱን ሲስት ታወቀኝ
ዘልዬ አነቅኳት...የምሳሳላቸው አይኖቿ...ገና ያኔ ስታየኝ ፍስስ የሚያደርጉኝ ውብ እይታዋ ተቀየረ...ምን እያረክ ነው ?የሚል አተያይ...
እጆቿ አንገቴ ስር አድነኝ በሚል ሲቃ ሲዞሩ ይሰማኛል
ድምጷ ሲለወጥ...ደም ስሯ ለመውጣት ሲወጣጠር እያየው ነው።በዚህ ሁሉ መሀል እጆቼ ከጉሮሮዋ ስር ነበሩ....
የኔ በሆነ ልቧ ውስጥ የኖረው እሷነቷን በአንድ ቀን ይሁን በተደጋጋሚ ነው??እየኖረ አለ ብዬ ሳስብ ያፈተለከው..??መች ይሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተወችኝ??ያወራሁላት ጥንካሬ የት ተሰወረ....ማለፍ ያልቻለችውን ምንስ ህመም ብሰጣት ነው....
ሳናድዳት?ሳበሳጫት ነው??እልኃን ለመወጣት ጀምራ ማቆም ተስኗት ነው???
እንጃ መች ይሆን እያለች የጠፋችው...ቀን ከርሱ ውላ ማታ እንደ ይሁዳ አቅፋ የሸጠችኝ መች ነበር.....ያ ውብ ሳቋ ትዝ ሲለኝ አሁን እንዲያ በሲቃ መውጣት ስላቃተው ደስ አለኝ...
ስትስመኝ..ደስ ያለኝን...ስትነካኝ ልቤ ስውር ያለውን አሰዋወር...ማስመሰል መሆኑን ሳውቅ..ምን ጊዜ ነበር ህይወቴ ውሸት የሆነው....?ነገና ዛሬዬ መሀል ድልድይ ሳደርጋት ልቤን ያለ ስስት ስሰጣት ነው....ይህ ይሆን በደሌ.....
በነዚህ ሁሉ መለል በእልህ አፍጥጬ እጆቼ እርሷ ጋር ነበሩ.....
ድንገት.......
......ዝም..........አለች።የፈጠጡብኝ አይኖቿ ተከደኑ።
ሲታገለኝ የነበረው ሰውነቷ ደነዘዘ......አንገቴ ስር ሲዛወር ያላየውት ፤ያልገባኝ ፤ያልተሰማኝ የእጇ ንክኪ...እጆቿ ሲወርዱ ነቃው...
ፊቷን አዞረች...ተሸናፊ መሆኗን በዝምታዋ ነገረችኝ....
ላትመለስ በገዛ እጆቼ አይኔ እያየ መጓዟን በሰውነቷ ቅዝቃዜ አስረዳችኝ።።
ለመጀመሪያ ጊዜ ከሬሳ ጋር ተፋጠጥኩ።
ጨነቀኝ፤ትንሽ ቆይታ የምትነሳ መሰለኝ ጠበኳት.....ዝም....
ቀሰቀስኳት...ጭጭ
የማላውቀው ፍርሀት....ጭንቀት...ብቸኝነት....በቅፅበት
ወረሱኝ...ሀጢአተኝነት ተፀናወተኝ
እኔነቴን ልቤን ህይወቴን ውሸት ማረጓ ሳያንስ...ሰውነቴን ቀማችኝ...ህሊናዬን የገዛ እጆቼ ነጠቁኝ.....ምንም አላልኩም...ያደረግኩትንም አላውቅም.....
ግን......
አፈቅራት አልነበር....እወዳትስ አልነበር...
ለምን?ለምን አረግሽው አላልኳትም?
አላፈቅራትም ነው ።ባልወዳት ነው ያ ሁሉ የሆንኩላት??
እንጃ
እኔም ዝም እርሷም .... ዝም
ፍቅር እንዲህ ነው?? ገሳጭ እንጅ መላሽ የሌለበት ትግል ውስጥ ገባው።
......
ሁሉም ውሸት ነበር "አትወደኝም" ብትወደኝ አትክደኝም።
"ብወዳት"
አልገላትም.....
በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት ።ውሸት....
ኢሊ ዲያ ✍️
https://t.me/onelife21A
በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት
አለም አንድ ናት ሲባል እኔ ፕላኔቶቼን የምቆጥረው ከርሷ አካል ነበር።
አለሜ ስላት ሁሉ እኔነቴን በመስጠት መሀል ስላገኘኃት ነበር....ያሳለፍነውን ሳስብ ወደ ፊት ምንም ማለፍ እንደማያቅተን በሙሉ ልብ ሳወራ እገኛለው።።።ለምን?ብባል መልሴ...የርሷ ጥንካሬና የእኔ ትግስት አብሮ መጓዙ ለዚህ አብቅቶናል......ዳሩ ነበርነት መሀል ተሰይመን ተገኘን......ቅድሚያውኑ.....
ነበርነቴ የጀመረው ያን ዕለት ..ነው...
ንዴት፤ብስጭት፤ጭንቀት፤ፍርሀት፤ራስን ማጣት ውስጤ የነበሩ ዕለት ፊቴ የነበረችው እርሷ ነበረች።የዳበስኩት እሷነቷን ሌላ ጋር ሳገኘው....በሳቀችልኝ ጥርሶቿ እርሱ ጋር ስንቴ እንደሳቀች እያሰብኩ እኔነቴ ከላዬ ሲወርድ ታወቀኝ....ዝም ብላ አይኔን መመልከቷ አበሳጨኝ ንቄሀለው...አሳፋሪ ስራ አልሰራውም አይነት አተያይ እያየችኝ አገኘኃት።
አብራት ኗሪው ላይ ትኩረቴ አልነበረም የኔ የሆነ ላይ ነው እይታዬ
የኔ የነበረ.....
ድንገት ብቻችንን ሆንን ይብረር..ይሩጥ ሳላውቅ ያ ሰው ፊቴ አልነበረም።
እኛነታችንን እንደ ቀላል በስሜት ግለት ስትጫወትበት እንደቆየች ሳስብ...ማሰቢያዬ ራሱን ሲስት ታወቀኝ
ዘልዬ አነቅኳት...የምሳሳላቸው አይኖቿ...ገና ያኔ ስታየኝ ፍስስ የሚያደርጉኝ ውብ እይታዋ ተቀየረ...ምን እያረክ ነው ?የሚል አተያይ...
እጆቿ አንገቴ ስር አድነኝ በሚል ሲቃ ሲዞሩ ይሰማኛል
ድምጷ ሲለወጥ...ደም ስሯ ለመውጣት ሲወጣጠር እያየው ነው።በዚህ ሁሉ መሀል እጆቼ ከጉሮሮዋ ስር ነበሩ....
የኔ በሆነ ልቧ ውስጥ የኖረው እሷነቷን በአንድ ቀን ይሁን በተደጋጋሚ ነው??እየኖረ አለ ብዬ ሳስብ ያፈተለከው..??መች ይሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የተወችኝ??ያወራሁላት ጥንካሬ የት ተሰወረ....ማለፍ ያልቻለችውን ምንስ ህመም ብሰጣት ነው....
ሳናድዳት?ሳበሳጫት ነው??እልኃን ለመወጣት ጀምራ ማቆም ተስኗት ነው???
እንጃ መች ይሆን እያለች የጠፋችው...ቀን ከርሱ ውላ ማታ እንደ ይሁዳ አቅፋ የሸጠችኝ መች ነበር.....ያ ውብ ሳቋ ትዝ ሲለኝ አሁን እንዲያ በሲቃ መውጣት ስላቃተው ደስ አለኝ...
ስትስመኝ..ደስ ያለኝን...ስትነካኝ ልቤ ስውር ያለውን አሰዋወር...ማስመሰል መሆኑን ሳውቅ..ምን ጊዜ ነበር ህይወቴ ውሸት የሆነው....?ነገና ዛሬዬ መሀል ድልድይ ሳደርጋት ልቤን ያለ ስስት ስሰጣት ነው....ይህ ይሆን በደሌ.....
በነዚህ ሁሉ መለል በእልህ አፍጥጬ እጆቼ እርሷ ጋር ነበሩ.....
ድንገት.......
......ዝም..........አለች።የፈጠጡብኝ አይኖቿ ተከደኑ።
ሲታገለኝ የነበረው ሰውነቷ ደነዘዘ......አንገቴ ስር ሲዛወር ያላየውት ፤ያልገባኝ ፤ያልተሰማኝ የእጇ ንክኪ...እጆቿ ሲወርዱ ነቃው...
ፊቷን አዞረች...ተሸናፊ መሆኗን በዝምታዋ ነገረችኝ....
ላትመለስ በገዛ እጆቼ አይኔ እያየ መጓዟን በሰውነቷ ቅዝቃዜ አስረዳችኝ።።
ለመጀመሪያ ጊዜ ከሬሳ ጋር ተፋጠጥኩ።
ጨነቀኝ፤ትንሽ ቆይታ የምትነሳ መሰለኝ ጠበኳት.....ዝም....
ቀሰቀስኳት...ጭጭ
የማላውቀው ፍርሀት....ጭንቀት...ብቸኝነት....በቅፅበት
ወረሱኝ...ሀጢአተኝነት ተፀናወተኝ
እኔነቴን ልቤን ህይወቴን ውሸት ማረጓ ሳያንስ...ሰውነቴን ቀማችኝ...ህሊናዬን የገዛ እጆቼ ነጠቁኝ.....ምንም አላልኩም...ያደረግኩትንም አላውቅም.....
ግን......
አፈቅራት አልነበር....እወዳትስ አልነበር...
ለምን?ለምን አረግሽው አላልኳትም?
አላፈቅራትም ነው ።ባልወዳት ነው ያ ሁሉ የሆንኩላት??
እንጃ
እኔም ዝም እርሷም .... ዝም
ፍቅር እንዲህ ነው?? ገሳጭ እንጅ መላሽ የሌለበት ትግል ውስጥ ገባው።
......
ሁሉም ውሸት ነበር "አትወደኝም" ብትወደኝ አትክደኝም።
"ብወዳት"
አልገላትም.....
በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት ።ውሸት....
ኢሊ ዲያ ✍️
https://t.me/onelife21A
17.04.202507:18
መቼ ነው ህይወት ለዛዋ የጠፋው? መቼ ነው ለመጨረሻ ጊዜ ከልባችን የሳቅነው?! መቼ ነው በልተን የተደሰትነው? መቼ ነው ማማረር የሌለበት ወሬ ያወራነው? መቼ ነው የጨላለመብን? መቼ ነው የምንሰማው የምናየው ሁሉ የበጠበጠን? መቼ ነው
መዝናኛችን እንደ አዙሪት ከድብርታችን ያበረብን?
መቼ ነው በደንብ መኖር ያቆምነው?
በደንብ መሳቅ? በደንብ ማልቀስ? በደንብ መውደድ? በደንብ መግባባት? በደንብ መናፈቅ? በደንብ ማለም? በደንብ ለህልም መጋጋጥ? በደንብ መጎዳት? በደንብ መድመቅ?
መቼ ነው ህይወት እንደነገሩ የሆነችብን?
ከላይ ከላይ ብቻ የሆንነው መቼ ነው? ትልቋን ህይወት አጥብበን ጥቂት ሙከራ፥ ጥቂት ጥረት፥ ጥቂት ሀዘን፥ ጥቂት ተስፋ ግን ብዙ ጨለማ የከበበን መቼ ነው?! የቱ እጦት ነው ቋጥኝ ድብርት የጣለብን? የቱ እድሜ ነው ብዙ አሳይቶ ብዙ ያደከመን? የቱ እውቀታችን ነው ወደፊቱን የጋረደብን? ማነው እድሜያችን ቢበዛ ሰላሳ ብሎ በጊዜ መንፈሳችን ጡረታ ያወጣው? ምንድነው የዞረብን?!
መቼ ነው እንደዚህ የሆንነው?
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
መዝናኛችን እንደ አዙሪት ከድብርታችን ያበረብን?
መቼ ነው በደንብ መኖር ያቆምነው?
በደንብ መሳቅ? በደንብ ማልቀስ? በደንብ መውደድ? በደንብ መግባባት? በደንብ መናፈቅ? በደንብ ማለም? በደንብ ለህልም መጋጋጥ? በደንብ መጎዳት? በደንብ መድመቅ?
መቼ ነው ህይወት እንደነገሩ የሆነችብን?
ከላይ ከላይ ብቻ የሆንነው መቼ ነው? ትልቋን ህይወት አጥብበን ጥቂት ሙከራ፥ ጥቂት ጥረት፥ ጥቂት ሀዘን፥ ጥቂት ተስፋ ግን ብዙ ጨለማ የከበበን መቼ ነው?! የቱ እጦት ነው ቋጥኝ ድብርት የጣለብን? የቱ እድሜ ነው ብዙ አሳይቶ ብዙ ያደከመን? የቱ እውቀታችን ነው ወደፊቱን የጋረደብን? ማነው እድሜያችን ቢበዛ ሰላሳ ብሎ በጊዜ መንፈሳችን ጡረታ ያወጣው? ምንድነው የዞረብን?!
መቼ ነው እንደዚህ የሆንነው?
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
Log in to unlock more functionality.