
Анатолий Шарий

Реальний Київ | Украина

Лёха в Short’ах Long’ует

Труха⚡️Україна

Николаевский Ванёк

Инсайдер UA

Реальна Війна | Україна | Новини

Лачен пише

Nairaland Pulse | News

Анатолий Шарий

Реальний Київ | Украина

Лёха в Short’ах Long’ует

Труха⚡️Україна

Николаевский Ванёк

Инсайдер UA

Реальна Війна | Україна | Новини

Лачен пише

Nairaland Pulse | News

Анатолий Шарий

Реальний Київ | Украина

Лёха в Short’ах Long’ует

እንማር
名言
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯 መፅሀፎች
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
የተለያዩ PDF መፅሐፍት እንደፍላጎቶ አሉ
Ads - @Kiya988
https://youtube.com/channel/UCr7-LDddhyqtFUCH0OHhM2Q
Buy ads: https://telega.io/c/Enmare1988
🎯 መፅሀፎች
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
የተለያዩ PDF መፅሐፍት እንደፍላጎቶ አሉ
Ads - @Kiya988
https://youtube.com/channel/UCr7-LDddhyqtFUCH0OHhM2Q
Buy ads: https://telega.io/c/Enmare1988
关联群组

እንማር
3.3K


26.04.202519:49
☑️ ቆንጆ ናት... አፍላ .... 15 አመቷ ነው።
ጎረምሶች ሲያዩዋት አይናቸው ይጎለጎላል። ጎልማሶች አይተው ይመኛታል። ወንዶች ይከጅሏታል። ሴቶች በቅናት እንደ ሽንኩርት ይልጧታል።
☑️ አንድ ቀን እንዲህ ስል ጠየቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን መስፈርት እንዲያሟላ ትፈልጊያለሽ?
>>
☑️ በፍጥነት መለሰችልኝ
የተማረ መሆን አለበት፤ ማስተርስ ያለው ይመረጣል። ከተቻለ የግል ቢዝነስ የሚሰራ፤ ኢንቨስተር ቢሆን አሪፍ ነው፤ ካልሆነ ግን አሪፍ ደሞዝ ሊኖረው
ግድ.ነው። መኖሪያ ቤቱ G+2 ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ከG+1 በታች ግን
አልፈልግም።
✅ መኪና በጣም ነው የምወደው። አሪፍ መኪኖች ቢኖሩት አሪፍ ካልሆነም
ከተጋባን በኋላ እኔ እንዲገዛ አደርገዋለሁ። ሙድ የገባው ቢሆን ደስ
ይለኛል። ሁሌ ግን የሚቅም፤ የሚጨብስ እና የሚያጨስ መሆን
የለበትም። ጨዋታ የሚያውቅ ሁሌ የሚያስቀኝ!!!
✅ ቁመቱ በጣም እንዲረዝም አልፈልግም። እኔ አጠር ስለምል በጣም
እንዳይበልጠኝ። ደረቱ ሰፋ ያለ ሆኖ ቦርጭ የሚባል እንዲኖረው
አልፈልግም።
✅ጸጉሩ ፍሪዝ ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ድሬድ ቢሆን ደግሞ ነፍስ ነው። አይኑ
የሚያምር፤ መልኩ ጸይም መሆን አለበት በጣም ቀይ ወይም በጣም ጥቁር
ወንድ አልወድም። አለባበሱ ዘናጭ መሆን አለበት። የሚወደኝ፤
የሚንከባከበኝ፤ ሮማንቲክ የሆነ፤ በሳምንት ቢያንስ ሁለቴ የሻማ
እራት ያለበት ሆቴል የሚጋብዘኝ፤ ቢያንስ በወር ሁለቴ ጭፈራ ቤት
የሚወስደኝ፤.ከበዓላት እና ከልደቴ ቀን በተጨማሪ ስጦታ እያመጣ ስርፕራይዝ
የሚያደርገኝ፤ ፍቅር የሚያውቅ፤ በተለያየ ቁልምጫ ስም የሚጠራኝ እና
ታማኝ ከእኔ ውጪአንዲት ሴት የማያይ ...
☑️ >>ይበቃል አልኳት እንደማታቆም ስለገባኝ። እንዲህ አይነት ወንድ
ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ አስቴር አወቀ ዘፈን ውስጥ እንኳን አይገኝም አልኩ
በውስጤ። ለሷ ግንአልነገርኳትም።
✅ ከአስር አመት በኋላ ሳገኛት 25 አመቷ ነበር። አላገባችም። ዩኒቨርስቲ
ጨርሳ.ስራ ይዛለች። ጥቂት ቦይ ፍሬንዶች ይዛ ለቃለች። አሁንም ታምራለች
እንደድሮው ግን የሰው ሁሉ አይን ማረፊያ አይደለችም። መልሼ ያንኑ ጥያቄ
ጠየቅኳት።
✅ <<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>>
የማፈቅረው ሰው መሆን አለበት፤ ፍቅር ከሌለ ላገባው አልችልም።
ከማልወደው ሰው ጋር አንድ ቀን ላድር አልችልም። ታማኝ እንዲሆን
እፈልጋለሁ። እንዲያከብረኝ እፈልጋለሁ። ጥሩ ስራ ቢኖረው፤ ማንበብ
የሚወድና በሃሳብ የምንግባባ ቢሆን ደስ ይለኛል። ቆንጆና ሃብታም ከሆነ ጥሩ ነው፤ ካልሆነም ግን አብረን ሰርተን መለወጥ እንችላለን። ዋናው መግባባት ነው። በተረፈ ቤተሰቡን የሚወድ እና የማይዋሽ መሆን አለበት። ወንዱ ሁሉ
የማይታመን ሆነብን እኮ። ዋናው የሚታመን ከሆነ ሌላው ችግር
የለውም>>
✅ ጊዜው ይሮጣል!!! ከአስር አመት በኋላ ስንገናኝ አላገባችም። 35 አመት
እያለፋት ነበር። ደግሜ ያንኑ ጥያቄ ጠይቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>>
ትንሽ አሰብ አደረገኝና
<<የምግባባው ሰው ከሆነ ሌላው ችግር የለውም>> አለችኝ
መልኩ፤ ጸጉሩ፤ ሃብቱ፤ እውቀቱስ አልኳት።
<<ወንድ ልጅ ደግሞ መልክ ምን ያደርግለታል? ከቺምፕ (ቺምፓንዚ)
መለስ ካለ ሌላው ችግር የለውም>> አለች እየሳቀች።
☑️ ከአስር አመት በኋላ ሳገኛት አግብታ ሁለት ልጆች ወልዳ ነበር።ባሏ
አጭር፤ ጥቁር፤ መላጣ፤ የከባዳ መኪና ሾፌር አይነት ቦርጭ
ያለው፤ሱሪውን ቦርጩ መሃከል ላይ የሚታጠቅ፤ ሁልጊዜ መላጣውን
የሚያልበው ዝጋታም ነገር ነው
✅<<እንዴት ነው ትወጂዋለሽ>> አልኳት
✅<<ምን ማለትህ ነው ትዳር አይደል?>>
✅<<ማለቴ ድሮ የነገርሽኝ አይነት ሰው አይደለም ብዬ ነው?>>
✅<<ያኔማ አየር ላይ ነበርኩ፤ እድሜ መስታወት ነው፤ ብዙ ያስተምራል፤
አሁን
ተምረን ልብ ገዝተን ነው>> አለች ተከዝ ብላ።
✅ <<ሁሌ የማይቀያየር አንድ መስፈርት ነበረሽ፤ ታማኝ መሆን አለበት ትይኝ
ነበር።
ባልሽ ታማኝ ነው?>>
<<ታማኝ እግዜር ብቻ ነው፤ በቃ ግን ... ትዳር ስለሆነ ከማይታመን ሰው
ጋር መኖር ትለምዳለህ፤ አየህ አሁን የገባኝ ነገር ትዳር ማለት እንደ ፖለቲካ
ነው።
☑️ ፖለቲከኞች ውሸት እየነገሩን አብረን እንደምንኖር ትዳር ውስጥም ይሄ
ያጋጥማል>> አለች
<<በትዳርሽ ደስተኛ ነሽ?>> አልኳት እያዘንኩ
✅ <<ደስታ አንጻራዊ ነው፤ በልጆቼ ደስ ይለኛል፤ ትዳሬን አከብራለሁ። በተረፈ
ግን እየኖርኩ ነው>> አለች ፈገግ ብላ። በዛች ቅጽበታዊ ፈገግታ ውስጥ
የጊዜን ኃይለኝነት አየሁ።
ጊዜ ነው እንጂ ቁምነገራም
ባላባትነት አያኮራም እንዲሉ እመው።
አንብበው ከወደዱት 👍👍
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
ጎረምሶች ሲያዩዋት አይናቸው ይጎለጎላል። ጎልማሶች አይተው ይመኛታል። ወንዶች ይከጅሏታል። ሴቶች በቅናት እንደ ሽንኩርት ይልጧታል።
☑️ አንድ ቀን እንዲህ ስል ጠየቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን መስፈርት እንዲያሟላ ትፈልጊያለሽ?
>>
☑️ በፍጥነት መለሰችልኝ
የተማረ መሆን አለበት፤ ማስተርስ ያለው ይመረጣል። ከተቻለ የግል ቢዝነስ የሚሰራ፤ ኢንቨስተር ቢሆን አሪፍ ነው፤ ካልሆነ ግን አሪፍ ደሞዝ ሊኖረው
ግድ.ነው። መኖሪያ ቤቱ G+2 ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ከG+1 በታች ግን
አልፈልግም።
✅ መኪና በጣም ነው የምወደው። አሪፍ መኪኖች ቢኖሩት አሪፍ ካልሆነም
ከተጋባን በኋላ እኔ እንዲገዛ አደርገዋለሁ። ሙድ የገባው ቢሆን ደስ
ይለኛል። ሁሌ ግን የሚቅም፤ የሚጨብስ እና የሚያጨስ መሆን
የለበትም። ጨዋታ የሚያውቅ ሁሌ የሚያስቀኝ!!!
✅ ቁመቱ በጣም እንዲረዝም አልፈልግም። እኔ አጠር ስለምል በጣም
እንዳይበልጠኝ። ደረቱ ሰፋ ያለ ሆኖ ቦርጭ የሚባል እንዲኖረው
አልፈልግም።
✅ጸጉሩ ፍሪዝ ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ድሬድ ቢሆን ደግሞ ነፍስ ነው። አይኑ
የሚያምር፤ መልኩ ጸይም መሆን አለበት በጣም ቀይ ወይም በጣም ጥቁር
ወንድ አልወድም። አለባበሱ ዘናጭ መሆን አለበት። የሚወደኝ፤
የሚንከባከበኝ፤ ሮማንቲክ የሆነ፤ በሳምንት ቢያንስ ሁለቴ የሻማ
እራት ያለበት ሆቴል የሚጋብዘኝ፤ ቢያንስ በወር ሁለቴ ጭፈራ ቤት
የሚወስደኝ፤.ከበዓላት እና ከልደቴ ቀን በተጨማሪ ስጦታ እያመጣ ስርፕራይዝ
የሚያደርገኝ፤ ፍቅር የሚያውቅ፤ በተለያየ ቁልምጫ ስም የሚጠራኝ እና
ታማኝ ከእኔ ውጪአንዲት ሴት የማያይ ...
☑️ >>ይበቃል አልኳት እንደማታቆም ስለገባኝ። እንዲህ አይነት ወንድ
ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ አስቴር አወቀ ዘፈን ውስጥ እንኳን አይገኝም አልኩ
በውስጤ። ለሷ ግንአልነገርኳትም።
✅ ከአስር አመት በኋላ ሳገኛት 25 አመቷ ነበር። አላገባችም። ዩኒቨርስቲ
ጨርሳ.ስራ ይዛለች። ጥቂት ቦይ ፍሬንዶች ይዛ ለቃለች። አሁንም ታምራለች
እንደድሮው ግን የሰው ሁሉ አይን ማረፊያ አይደለችም። መልሼ ያንኑ ጥያቄ
ጠየቅኳት።
✅ <<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>>
የማፈቅረው ሰው መሆን አለበት፤ ፍቅር ከሌለ ላገባው አልችልም።
ከማልወደው ሰው ጋር አንድ ቀን ላድር አልችልም። ታማኝ እንዲሆን
እፈልጋለሁ። እንዲያከብረኝ እፈልጋለሁ። ጥሩ ስራ ቢኖረው፤ ማንበብ
የሚወድና በሃሳብ የምንግባባ ቢሆን ደስ ይለኛል። ቆንጆና ሃብታም ከሆነ ጥሩ ነው፤ ካልሆነም ግን አብረን ሰርተን መለወጥ እንችላለን። ዋናው መግባባት ነው። በተረፈ ቤተሰቡን የሚወድ እና የማይዋሽ መሆን አለበት። ወንዱ ሁሉ
የማይታመን ሆነብን እኮ። ዋናው የሚታመን ከሆነ ሌላው ችግር
የለውም>>
✅ ጊዜው ይሮጣል!!! ከአስር አመት በኋላ ስንገናኝ አላገባችም። 35 አመት
እያለፋት ነበር። ደግሜ ያንኑ ጥያቄ ጠይቅኳት።
<<ማግባት የምትፈልጊው ባል ምን አይነት ነገሮች ማሟላት አለበት?>>
ትንሽ አሰብ አደረገኝና
<<የምግባባው ሰው ከሆነ ሌላው ችግር የለውም>> አለችኝ
መልኩ፤ ጸጉሩ፤ ሃብቱ፤ እውቀቱስ አልኳት።
<<ወንድ ልጅ ደግሞ መልክ ምን ያደርግለታል? ከቺምፕ (ቺምፓንዚ)
መለስ ካለ ሌላው ችግር የለውም>> አለች እየሳቀች።
☑️ ከአስር አመት በኋላ ሳገኛት አግብታ ሁለት ልጆች ወልዳ ነበር።ባሏ
አጭር፤ ጥቁር፤ መላጣ፤ የከባዳ መኪና ሾፌር አይነት ቦርጭ
ያለው፤ሱሪውን ቦርጩ መሃከል ላይ የሚታጠቅ፤ ሁልጊዜ መላጣውን
የሚያልበው ዝጋታም ነገር ነው
✅<<እንዴት ነው ትወጂዋለሽ>> አልኳት
✅<<ምን ማለትህ ነው ትዳር አይደል?>>
✅<<ማለቴ ድሮ የነገርሽኝ አይነት ሰው አይደለም ብዬ ነው?>>
✅<<ያኔማ አየር ላይ ነበርኩ፤ እድሜ መስታወት ነው፤ ብዙ ያስተምራል፤
አሁን
ተምረን ልብ ገዝተን ነው>> አለች ተከዝ ብላ።
✅ <<ሁሌ የማይቀያየር አንድ መስፈርት ነበረሽ፤ ታማኝ መሆን አለበት ትይኝ
ነበር።
ባልሽ ታማኝ ነው?>>
<<ታማኝ እግዜር ብቻ ነው፤ በቃ ግን ... ትዳር ስለሆነ ከማይታመን ሰው
ጋር መኖር ትለምዳለህ፤ አየህ አሁን የገባኝ ነገር ትዳር ማለት እንደ ፖለቲካ
ነው።
☑️ ፖለቲከኞች ውሸት እየነገሩን አብረን እንደምንኖር ትዳር ውስጥም ይሄ
ያጋጥማል>> አለች
<<በትዳርሽ ደስተኛ ነሽ?>> አልኳት እያዘንኩ
✅ <<ደስታ አንጻራዊ ነው፤ በልጆቼ ደስ ይለኛል፤ ትዳሬን አከብራለሁ። በተረፈ
ግን እየኖርኩ ነው>> አለች ፈገግ ብላ። በዛች ቅጽበታዊ ፈገግታ ውስጥ
የጊዜን ኃይለኝነት አየሁ።
ጊዜ ነው እንጂ ቁምነገራም
ባላባትነት አያኮራም እንዲሉ እመው።
አንብበው ከወደዱት 👍👍
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988


02.05.202513:08
እጅግ በጣም ድሃ የሆነች አንዲት ሴት ከእግዚአብሔር እርዳታን ለመጠየቅ ወደ አንድ የሬዲዮ ጣቢያ ደወለች። ይህንን የሬዲዮ ፕሮግራም እያዳመጠ የነበረ እምነት የሌለው አንድ ሰው በሴትየዋ ላይ ሊቀልድ ወሰነ።
የሴትየዋን አድራሻ ከሬዲዮ ጣቢያው አግኝቶ፣ ፀሐፊዋ ብዙ የምግብ ነገሮችን ለሴትየዋ እንድትወስድላት አዘዛት። ነገር ግን፣ ይህንን መመሪያ ሰጣት፦ "ሴትየዋ ምግቡን ማን እንደላከው ስትጠይቅሽ፣ ከሰይጣን እንደሆነ ንገሪያት።"
ፀሐፊዋ የሴትየዋ ቤት ስትደርስ ሴትየዋ በተደረገላት እርዳታ በጣም ደስተኛና አመስጋኝ ነበረች። የምግብ እሽጎቹን ወደ ትንሿ ቤቷ ማስገባት ጀመረች። ከዚያም ፀሐፊዋ "ምግቡን ማን እንደላከው ማወቅ አትፈልጊም?" ስትል ጠየቀቻት።
ሴትየዋም እንዲህ ስትል መለሰች፦ "አይ ግድ የለኝም፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሲያዝ፣ ሰይጣን እንኳን ይታዘዛል!
የሴትየዋን አድራሻ ከሬዲዮ ጣቢያው አግኝቶ፣ ፀሐፊዋ ብዙ የምግብ ነገሮችን ለሴትየዋ እንድትወስድላት አዘዛት። ነገር ግን፣ ይህንን መመሪያ ሰጣት፦ "ሴትየዋ ምግቡን ማን እንደላከው ስትጠይቅሽ፣ ከሰይጣን እንደሆነ ንገሪያት።"
ፀሐፊዋ የሴትየዋ ቤት ስትደርስ ሴትየዋ በተደረገላት እርዳታ በጣም ደስተኛና አመስጋኝ ነበረች። የምግብ እሽጎቹን ወደ ትንሿ ቤቷ ማስገባት ጀመረች። ከዚያም ፀሐፊዋ "ምግቡን ማን እንደላከው ማወቅ አትፈልጊም?" ስትል ጠየቀቻት።
ሴትየዋም እንዲህ ስትል መለሰች፦ "አይ ግድ የለኝም፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ሲያዝ፣ ሰይጣን እንኳን ይታዘዛል!


09.05.202507:54
✅ዛሬ አንድ ሱቅ ውስጥ የቀድሞ ፍቅረኛዬ ፍቅረኛዋን ከፊት ለፊቴ እየሳመች አገኘኋቸው፣ እያየዋቸው ነበር።
አየችኝ ከዛ የበለጠ ሳመችው እና እዚህ ምን እየሰራሁ እንደሆነ ጠየቀችኝ?.
💠ባለቤቴ አርግዛ መውለዷን ነገርኳት እና እኔ እዚህ የመጣሁት የልጅ እቃዎችን ለመግዛት ነው በጣም ደስተኛ ነኝ ምናምን ብዬ አቀሳሰርኩ እና ሱቅ ውስጥ ገባሁ
✅እሷ እያየችኝ ዳይፐር ፣የህፃን ወንበር እና የህፃን አልጋ ስፖንጅ ፣ብስክሌት ፣የህጻን ልብስ እና የመሳሰሉትን ገዛሁ ከዛ Ride ደወልኩና እቃውን ጭኜ ሄድኩ።
እሷ እና የወንድ ጓደኛዋ ተመስጠው እየተመለከቱኝ ነበር እና ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነበር የሄድኩት...
💠አሁን ወደ ቁም ነገሩ ስገባ የወለደች ሴት የምታውቁ ዳይፐር፣ የልጅ መቀመጫ ወንበር፣ የአልጋ ስፖንጅ፣ ብስክሌት እና የህፃን ልብስ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጥኩ ነው ሚገዛኝ ካለ ወዲህ በሉ...😡
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
አየችኝ ከዛ የበለጠ ሳመችው እና እዚህ ምን እየሰራሁ እንደሆነ ጠየቀችኝ?.
💠ባለቤቴ አርግዛ መውለዷን ነገርኳት እና እኔ እዚህ የመጣሁት የልጅ እቃዎችን ለመግዛት ነው በጣም ደስተኛ ነኝ ምናምን ብዬ አቀሳሰርኩ እና ሱቅ ውስጥ ገባሁ
✅እሷ እያየችኝ ዳይፐር ፣የህፃን ወንበር እና የህፃን አልጋ ስፖንጅ ፣ብስክሌት ፣የህጻን ልብስ እና የመሳሰሉትን ገዛሁ ከዛ Ride ደወልኩና እቃውን ጭኜ ሄድኩ።
እሷ እና የወንድ ጓደኛዋ ተመስጠው እየተመለከቱኝ ነበር እና ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነበር የሄድኩት...
💠አሁን ወደ ቁም ነገሩ ስገባ የወለደች ሴት የምታውቁ ዳይፐር፣ የልጅ መቀመጫ ወንበር፣ የአልጋ ስፖንጅ፣ ብስክሌት እና የህፃን ልብስ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጥኩ ነው ሚገዛኝ ካለ ወዲህ በሉ...😡
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988


25.04.202516:48
አንድ ጠበቃ የውሃ ጉድጓዱን ለመምህር ሸጠለት። ከሁለት ቀን በኋላ ጠበቃው ወደ መምህሩ መጥቶ እንዲህ አለው፡ "ጌታዬ፣ ጉድጓዱን ሸጥኩልህ እንጂ በውስጡ ያለውን ውሃ አልሸጥኩልህም! ውሃውን መጠቀም ከፈለግክ ተጨማሪ መክፈል አለብህ።"
መምህሩ ፈገግ አለና እንዲህ ሲል መለሰ፡ "አዎ፣ እኔም ወደ አንተ ልመጣ ነበር። ልልህ የነበረው ውሃህን ከእኔ ጉድጓድ ውስጥ እንድታወጣ ነው፣ አለበለዚያ ከነገ ጀምሮ ኪራይ መክፈል ትጀምራለህ።"
ይህን ሲሰማ ጠበቃው ተደናግጦ "ኦ! ዝም ብዬ እየቀለድኩ ነበር!" አለዉ።
መምህሩ እየሳቀ "እንደ አንተ ያሉ ሰዎች እኮ ከእኛ ዘንድ ተምረው ነው ጠበቃ የሚሆኑት!" አለው። ይባላል።😜
ክብር ለመምህራን
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
መምህሩ ፈገግ አለና እንዲህ ሲል መለሰ፡ "አዎ፣ እኔም ወደ አንተ ልመጣ ነበር። ልልህ የነበረው ውሃህን ከእኔ ጉድጓድ ውስጥ እንድታወጣ ነው፣ አለበለዚያ ከነገ ጀምሮ ኪራይ መክፈል ትጀምራለህ።"
ይህን ሲሰማ ጠበቃው ተደናግጦ "ኦ! ዝም ብዬ እየቀለድኩ ነበር!" አለዉ።
መምህሩ እየሳቀ "እንደ አንተ ያሉ ሰዎች እኮ ከእኛ ዘንድ ተምረው ነው ጠበቃ የሚሆኑት!" አለው። ይባላል።😜
ክብር ለመምህራን
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
12.05.202518:06
✅
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
ሶስት ቦዘኔ ወንድ ልጆች ያሉት አዛውንት አባት ለልጆቹ እንዲህ አላቸው…
✔️« ልጆቼ እኔ ከሞትኩ በኋላ ይህን ቤት አፍርሱት ፤ ከቤቱ ስር ለናንተ ብዬ በብረት ሳጥን ያጠራቀምኩት አንጡራ ሀብት አለና ለቀሪ ህይወታችሁ ይሆናችኋል »
ልጆችም ወዲያው ፀሎት ይጀምራሉ...« ፈጣሪያችን ሆይ! አባታችን እንደምታየው አርጅቷልና እባክህ ወዳንተ ጥራው» ። አባትም ከ2 አመት በኋላ ሞተ ። በሞተ በማግስቱ ቤቱን ድምጥማጡን አጠፉትና የተቀበረውን ሳጥን አወጡት። ሲከፍቱት አንዲት ቁራጭ ወረቀት ብቻ አገኙ ፤ እሷ ላይ የተፃፈውን ሲያነቡት…እንዲ ይላል
« ወንድ ከሆናችሁ ያፈረሳችኋትን ቤት መልሳችሁ ገንቧት» ይላል
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988


03.05.202516:31
''...አይዞሽ ታገቢያለሽ የሆነ ጊዜ ላይ ከአንድ ቆንጆ ወጣት ጋር ትተዋወቂና በጣም ስለምትዋደዱ ልጁ ተንበርክኮ ታገቢኛለሽ የሚል ጥያቄ አቅርቦ አንቺም ትስማሚያለሽ
...ልክ እንደ ምኞትሽም አባትሽ ክንድሽን አቅፎ ለዚሁ ልጅ ያስረክብሻል....😍
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
...ልክ እንደ ምኞትሽም አባትሽ ክንድሽን አቅፎ ለዚሁ ልጅ ያስረክብሻል....😍
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
20.04.202512:09
"
አንድ በግ 45 ብር? ምን አይነት ክፉ ጊዜ ላይ ነው የደረስነው!🤭"
አያቴ በ1965 ዓ.ም ዲያሪው ላይ ካሰፈረው የተወሰደ


11.05.202518:08
የዳኛው ብልሃት
አንድ ሰው በአንድ ወቅት ለጓደኛው የተወሰነ ገንዘብ አበደረው፤ ጓደኛው ግን በኋላ ገንዘቡን እንዳልተቀበለ ካደ። ስለዚህም ሰውየው ጓደኛውን ከሰሰውና ፍርድ ቤት አቆመው።
ዳኛውም "ምስክር አለህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየውም "የለኝም፤ ገንዘቡን በድብቅ ነው የሰጠሁት።" ሲል መለሰ። ዳኛውም "እንግዲያውስ ገንዘቡን ወደሰጠህበት ቦታ ሄደህ፣ እጠይቀው ዘንድ፣ ከዚያ ቦታ አንድ እፍኝ አፈር ይዘህልኝ ና።" አሉት።
ሰውየው በዚህ ጥያቄ ቢገረምም በታዘዘው መሰረት ከዚያ ቦታ አንድ እፍኝ አፈር ሊያመጣ ሄደ።
እሱ ሄዶ ሳለ ዳኛው ወደ ተበዳሪው ዞረው፦ "አሁን ቦታው የሚደርስ ይመስልሃል?" ብለው ጠየቁት። ሰውየውም በፍጥነት "አይ፤ ቦታው ከዚህ በጣም የራቀ ነው።" ሲል መለሰ። ዳኛውም እየሳቁ "ቦታው ሩቅ መሆኑን እንዴት አወቅክ... እዛ ሄደህ ገንዘቡን ካልተቀበልክ በቀር?" አሉት።
በመሆኑም ዳኛው ሰውየው እዳውን እንዲከፍል ወሰኑ፤ በዋሸውም ሃያ ግርፋት እንዲገረፍ አዘዙ።
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
አንድ ሰው በአንድ ወቅት ለጓደኛው የተወሰነ ገንዘብ አበደረው፤ ጓደኛው ግን በኋላ ገንዘቡን እንዳልተቀበለ ካደ። ስለዚህም ሰውየው ጓደኛውን ከሰሰውና ፍርድ ቤት አቆመው።
ዳኛውም "ምስክር አለህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየውም "የለኝም፤ ገንዘቡን በድብቅ ነው የሰጠሁት።" ሲል መለሰ። ዳኛውም "እንግዲያውስ ገንዘቡን ወደሰጠህበት ቦታ ሄደህ፣ እጠይቀው ዘንድ፣ ከዚያ ቦታ አንድ እፍኝ አፈር ይዘህልኝ ና።" አሉት።
ሰውየው በዚህ ጥያቄ ቢገረምም በታዘዘው መሰረት ከዚያ ቦታ አንድ እፍኝ አፈር ሊያመጣ ሄደ።
እሱ ሄዶ ሳለ ዳኛው ወደ ተበዳሪው ዞረው፦ "አሁን ቦታው የሚደርስ ይመስልሃል?" ብለው ጠየቁት። ሰውየውም በፍጥነት "አይ፤ ቦታው ከዚህ በጣም የራቀ ነው።" ሲል መለሰ። ዳኛውም እየሳቁ "ቦታው ሩቅ መሆኑን እንዴት አወቅክ... እዛ ሄደህ ገንዘቡን ካልተቀበልክ በቀር?" አሉት።
በመሆኑም ዳኛው ሰውየው እዳውን እንዲከፍል ወሰኑ፤ በዋሸውም ሃያ ግርፋት እንዲገረፍ አዘዙ።
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988


26.04.202517:24
✅ ቀይ መስመር ይኑረን!
አንድ ከዛፍ ስር የሚኖር አደገኛ እባብ ነበረ። አቅራቢያው የሚጠጉትን ሁሉ እየነደፈ ይገድላል። ሁሉም የአከባቢው ሰው አደገኝነቱን ካወቀ በኋላ እባቡ ከለበት ዛፍ አከባቢ ድርሽ አይልም።
✅ ከለታት አንድ ቀን ለመንደርዋ እንግዳ የሆነ ጠቢብ በጠራራ ፀሀይ መንደሯን እያቋረጠ ድካም ተሰማውና ይህ አደገኛ እባብ ወዳለባት ዛፍ ስር ሊጠለል ወደዛፏ መራመድ ጀመረ። ድንገት ሰዋች ደርሰው "ሰውየው ቁም እባብ አለ… አደገኛ እባብ…"ሲሉ ተጯጩኾ ሊያስቆሙት ሞኮሩ....
ጠቢቡ ሰው ፈገግ አለና "እኔ ከጥላው እንጂ ከእባቡ ምን አለኝ" በማለት ጩኸታቸውን ከቁብ ሳይቆጥር ወደ ዛፏ ተጠጋ…ሰዋች ጤንነቱን እየተጠራጠሩ ወደ ኋላ ሸሹ።
✅ እባቡ ኮሽታ ሰማና እራሱን ለጥቃት አዘጋጀ።
ጠቢቡ ሰው በዝግታ እየተራመደ አባቡ አጠገብ እንደደረሰ በፍቅርና ፈገግታ የእባቡን አይኖች ተመለከተ። እባቡ ለአፍታ በፈገግታና ፍቅር የተሞሉ የጠቢቡ አይኖችን አስተዋለና "አንተ ሰው ከአይኖችህ በፍርሀት ፈንታ ፍቅርና ደስታ ይነበባል ወደኔ ትቀርብ ዘንድ እንዴት ደፈርክ? አለው።
"እኔ ለመኖር ምጓጓ ሞትን የምፈራ ሰው እይደለሁም። በምድር የሚያስፈራኝ ነገር የለም። ይልቅ አንተ ትፈራለህ ሰዋች ሲጠጉህ ገና ለገና ሊገድሉኝ ነው ብለ ትነድፋቸዋለህ። የቀረበህ ሁሉ አይገድልህም ስለዚህ አንተ ያገኘሁን ሁሉ አትንደፍ" አለ ጠቢቡ፡፡
እባቡ የጠቢቡና ምክር በመስማት ያገኘውን ሁሉ መንደፍ አቆመ። ከዚያ ሰዋች ቀስ በቀስ ይቀርቡት ጀመረ፡ ቀስ በቀስ ይዳብሱት ያጫውቱት ጀመረ። እባቡ ከሰዋች ጋር በጣም በተለማመደ ቁጥር መናደፍ የተው ሳይሆን መናደፍ የማይችል መሰላቸው። መፍራት መከበሩ ቀረ፡ ህፃን ትልቁ ይጥሉት፡ያነሱት፡ይወረውሩት ያንገላቱት ጀመር።
➡️ ሌላ ቀን ጠቢቡ ሰው ወደዚያች መንደር መጣና እባቡን ሊጠይቀው ወደሚኖርበት ቦታ ሄደ።
ጠቢቡ ሰው እባቡ ጎስቁሎና ቆሳስሎ ሳለ አየ። "ምን ሁነ ነው ወዳጄ ምን ገጥምሆ ነው እንዲህ የጎሰቀልከው?" ሲል ጠየቀው።
✅️"ጠቢብ ነህ ብየ ምክርህን ሰምቼ መናደፍ ብተው ይኸው እንደምታየው የትልቅ ትንሹ መጫወቻ ሆንኩ" አለ በተሰበረ ድምፅ።
"አይ ምክሬን በትክክል አልሰማሀም ማለት ነው፡ ያገኘህውን ሁሉ አትናደፍ እንጂ እራስህን አትከላከል አልኩህ"
✅ትግስተኛነት ታላቅነት ቢሆንም ገደብ ሊኖረው ይገባል!
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
አንድ ከዛፍ ስር የሚኖር አደገኛ እባብ ነበረ። አቅራቢያው የሚጠጉትን ሁሉ እየነደፈ ይገድላል። ሁሉም የአከባቢው ሰው አደገኝነቱን ካወቀ በኋላ እባቡ ከለበት ዛፍ አከባቢ ድርሽ አይልም።
✅ ከለታት አንድ ቀን ለመንደርዋ እንግዳ የሆነ ጠቢብ በጠራራ ፀሀይ መንደሯን እያቋረጠ ድካም ተሰማውና ይህ አደገኛ እባብ ወዳለባት ዛፍ ስር ሊጠለል ወደዛፏ መራመድ ጀመረ። ድንገት ሰዋች ደርሰው "ሰውየው ቁም እባብ አለ… አደገኛ እባብ…"ሲሉ ተጯጩኾ ሊያስቆሙት ሞኮሩ....
ጠቢቡ ሰው ፈገግ አለና "እኔ ከጥላው እንጂ ከእባቡ ምን አለኝ" በማለት ጩኸታቸውን ከቁብ ሳይቆጥር ወደ ዛፏ ተጠጋ…ሰዋች ጤንነቱን እየተጠራጠሩ ወደ ኋላ ሸሹ።
✅ እባቡ ኮሽታ ሰማና እራሱን ለጥቃት አዘጋጀ።
ጠቢቡ ሰው በዝግታ እየተራመደ አባቡ አጠገብ እንደደረሰ በፍቅርና ፈገግታ የእባቡን አይኖች ተመለከተ። እባቡ ለአፍታ በፈገግታና ፍቅር የተሞሉ የጠቢቡ አይኖችን አስተዋለና "አንተ ሰው ከአይኖችህ በፍርሀት ፈንታ ፍቅርና ደስታ ይነበባል ወደኔ ትቀርብ ዘንድ እንዴት ደፈርክ? አለው።
"እኔ ለመኖር ምጓጓ ሞትን የምፈራ ሰው እይደለሁም። በምድር የሚያስፈራኝ ነገር የለም። ይልቅ አንተ ትፈራለህ ሰዋች ሲጠጉህ ገና ለገና ሊገድሉኝ ነው ብለ ትነድፋቸዋለህ። የቀረበህ ሁሉ አይገድልህም ስለዚህ አንተ ያገኘሁን ሁሉ አትንደፍ" አለ ጠቢቡ፡፡
እባቡ የጠቢቡና ምክር በመስማት ያገኘውን ሁሉ መንደፍ አቆመ። ከዚያ ሰዋች ቀስ በቀስ ይቀርቡት ጀመረ፡ ቀስ በቀስ ይዳብሱት ያጫውቱት ጀመረ። እባቡ ከሰዋች ጋር በጣም በተለማመደ ቁጥር መናደፍ የተው ሳይሆን መናደፍ የማይችል መሰላቸው። መፍራት መከበሩ ቀረ፡ ህፃን ትልቁ ይጥሉት፡ያነሱት፡ይወረውሩት ያንገላቱት ጀመር።
➡️ ሌላ ቀን ጠቢቡ ሰው ወደዚያች መንደር መጣና እባቡን ሊጠይቀው ወደሚኖርበት ቦታ ሄደ።
ጠቢቡ ሰው እባቡ ጎስቁሎና ቆሳስሎ ሳለ አየ። "ምን ሁነ ነው ወዳጄ ምን ገጥምሆ ነው እንዲህ የጎሰቀልከው?" ሲል ጠየቀው።
✅️"ጠቢብ ነህ ብየ ምክርህን ሰምቼ መናደፍ ብተው ይኸው እንደምታየው የትልቅ ትንሹ መጫወቻ ሆንኩ" አለ በተሰበረ ድምፅ።
"አይ ምክሬን በትክክል አልሰማሀም ማለት ነው፡ ያገኘህውን ሁሉ አትናደፍ እንጂ እራስህን አትከላከል አልኩህ"
✅ትግስተኛነት ታላቅነት ቢሆንም ገደብ ሊኖረው ይገባል!
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988


24.04.202509:23
✅️[✔️ ሴት ልጅ ስታፈቅር ... ]✔️✅️
☑️ የሴት ልጅ ፍቅር የማይናወጥ .... ራሷን የሚያስረሳት ...
በምሳሌ እንየው ....
{ ሴት እናት ስትሆን }
☑️ እናት ፍቅሯ ንፁህ እና ምንም ነገር ላይ ያልተመሰረተ ነው። ይህችን እናት እስኪ ብቻዋን ልጆቿን ለማሳደግ የምትታገል አድርገን እንሳላት። ለልጆቿ ምግብ ለመስራት፣ ልብሳቸውን ለሟሟላት፣
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት ሚስት ስትሆን }
☑️ ሚስት ለባሏ ዘውድ ናት። ሲደክመው ረዳቱ፣ ሲሰለቸው ብርታቱ፣ ሲነሳ ምርኩዙ .... በዝቅታው ሁሉ ከጎኑ የምትሆን ናት። ወንድ ልጅ ለስብራት ቅርብ ነው .... ስራ ማጣት፣ ያሰበው ነገር አልሳካ ሲለው፣ ትንሽ ሲያመው .... እንክትክት ነው የሚለው። አለም ሁሉ በቃው፣ ተሸነፈ፣ እጅ ሰጠ፣ አይነሳም ብሎ ሲጠብቅ እና ሲደመድም ....
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት ፍቅረኛ ስትሆን }
✅ ሴት ስታፈቅር በሁሉ ነገሯ ነው። በትግሎችህ ሁሉ አጠገብህ ናት። ስሜትህ ሲረበሽ፣ አለመረጋጋት ውስጥ ስትገባ .... አለምንም ፍርድ የምትሰማህ፣ አለሁልህ የምትልህ ... በራስህ እንኳን እምነት ባጣህ ጊዜህ አምናብህ አብራህ ትቆማለች።
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት እህት ስትሆን }
✅ እህት ምንም ነገር ላይ ጠበቃህ ናት። ብታጠፋም ባታጠፋም፣ ልክ ብትሆንም ባትሆንም .... ደጋፊህ እና አብራህ ቋሚ ናት። ከምንም ነገር የምትከላከልህ ደጀንህ ናት። የደህንነት ዋሻህ እህትህ ናት። ብቻህን ስትሆን ልትቆጣህ፣ ልትናደድብህ፣ ልትጮህብህ፣ ልታኮርፍህ፣ ላታወራህ ሁላ ትችላለች። ማንም ግን ሊነካህ ከሞከረ .... እህትህ ባንተ ጉዳይ አራስ ነብር ናት።
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት የተሳሳተ ወንድ ስታፈቅር }
✅ አንዳንዴ ፍቅሯን መዘባበቻ የሚያደርግ፣ የትም አትሄድም ብሎ እንደነገሩ የሚይዛት፣ ችላ ችላ የሚላት፣ አልፎ ተርፎም የሚንቃት ወንድ ላይ ሊጥላት ይችላል። የሚደበድባትን፣ የሚሰድባትን፣ የሚያንቋሽሻትን፣ በአካልም በስሜትም የሚረማመድባትን ወንድ አፍቅራ ልትሰቃይ ትችላለች። የሁልጊዜም አሳቧ ግን .... "እቀይረዋለሁ" ብላ መታገል ነው። ጓደኞቿ ተይ ሲሏት፣ ቤተሰብ ይቅርብሽ ሲላት .... እድል በእድል ላይ መስጠቷን ትቀጥላለች፤ ነገ ጥቅሜን ተረድቶ ይስተካከላል በሚል። ይሄ የሴት ልጅ ፍቅር ውበቱ እና ህመሙ ነው። ቁስሏን አልፎ የሚገለጥ መሆኑ ንፅህናውን ያሳያል።
ሴት ልጅ ፍቅርን ከተፈጥሮ ትቀዳለች .... መልሳ አለስስት ትሰጣለች .... ምክንያት፣ ድካም፣ ጊዜም ሆነ ሌላ ፈተና ያጠነክረዋል እንጂ አይፈታውም።
~
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
☑️ የሴት ልጅ ፍቅር የማይናወጥ .... ራሷን የሚያስረሳት ...
ሁለነገሯን ሰጥታ የምትገባበት ነው። በፈተናዎች የማይናወጥ፣ አለመግባባት እና አለመረዳቶችን የሚያልፍ .... ያለመፈለግ እና ረብ የለሽ ሆኖ የመቆጠርን ሁኔታ ሁሉ የሚሸከም ነው።
በምሳሌ እንየው ....
{ ሴት እናት ስትሆን }
☑️ እናት ፍቅሯ ንፁህ እና ምንም ነገር ላይ ያልተመሰረተ ነው። ይህችን እናት እስኪ ብቻዋን ልጆቿን ለማሳደግ የምትታገል አድርገን እንሳላት። ለልጆቿ ምግብ ለመስራት፣ ልብሳቸውን ለሟሟላት፣
የትምህርት መሳሪያዎቻቸውን ለሟሟላት .... ገቢ ለማግኘት ያገኘችውን ሁሉ ስትሰራ ውላ ሰውነቷ ዝሎ እቤት ትገባለች። ልጆቹን ማጣጠብ፣ ምግብ ማብሰል፣ የቤት ስራ ካላቸው ማሰራት፣ አቅፎ ማስተኛት የእሷው ሀላፊነት ነው። ምንም ያህል ቢደክማት፣ ምንም ያህል እረፍት ቢያስፈልጋት .... ከልጆቿ በፊት መተኛት፣ ከልጆቿ ዘግይታ መነሳት የማይታሰብ ነው። አየህ የሴት ልጅ ፍቅር ታጋሽ እና ፅኑ ነው የሚባለው ለዚህ ነው።
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት ሚስት ስትሆን }
☑️ ሚስት ለባሏ ዘውድ ናት። ሲደክመው ረዳቱ፣ ሲሰለቸው ብርታቱ፣ ሲነሳ ምርኩዙ .... በዝቅታው ሁሉ ከጎኑ የምትሆን ናት። ወንድ ልጅ ለስብራት ቅርብ ነው .... ስራ ማጣት፣ ያሰበው ነገር አልሳካ ሲለው፣ ትንሽ ሲያመው .... እንክትክት ነው የሚለው። አለም ሁሉ በቃው፣ ተሸነፈ፣ እጅ ሰጠ፣ አይነሳም ብሎ ሲጠብቅ እና ሲደመድም ....
አጠገቡ ቆማ የምታበረታው እና ደግፋ የምታነሳው ሚስቱ ናት። የጉብዝና ወራቱን የምታስታውሰው፣ አቅሙን የምትነግረው፣ ተነስቶ እንዲታገል የምታበረታው .... ብቻህን አይደለህም እኔ አለሁልህ የምትለው ሚስቱ ናት። ሴት በቃል ብቻ ሳይሆን በድርጊትም አቅምህ ናት።
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት ፍቅረኛ ስትሆን }
✅ ሴት ስታፈቅር በሁሉ ነገሯ ነው። በትግሎችህ ሁሉ አጠገብህ ናት። ስሜትህ ሲረበሽ፣ አለመረጋጋት ውስጥ ስትገባ .... አለምንም ፍርድ የምትሰማህ፣ አለሁልህ የምትልህ ... በራስህ እንኳን እምነት ባጣህ ጊዜህ አምናብህ አብራህ ትቆማለች።
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት እህት ስትሆን }
✅ እህት ምንም ነገር ላይ ጠበቃህ ናት። ብታጠፋም ባታጠፋም፣ ልክ ብትሆንም ባትሆንም .... ደጋፊህ እና አብራህ ቋሚ ናት። ከምንም ነገር የምትከላከልህ ደጀንህ ናት። የደህንነት ዋሻህ እህትህ ናት። ብቻህን ስትሆን ልትቆጣህ፣ ልትናደድብህ፣ ልትጮህብህ፣ ልታኮርፍህ፣ ላታወራህ ሁላ ትችላለች። ማንም ግን ሊነካህ ከሞከረ .... እህትህ ባንተ ጉዳይ አራስ ነብር ናት።
∞∞∞∞∞∞∞∞∞∞
{ ሴት የተሳሳተ ወንድ ስታፈቅር }
✅ አንዳንዴ ፍቅሯን መዘባበቻ የሚያደርግ፣ የትም አትሄድም ብሎ እንደነገሩ የሚይዛት፣ ችላ ችላ የሚላት፣ አልፎ ተርፎም የሚንቃት ወንድ ላይ ሊጥላት ይችላል። የሚደበድባትን፣ የሚሰድባትን፣ የሚያንቋሽሻትን፣ በአካልም በስሜትም የሚረማመድባትን ወንድ አፍቅራ ልትሰቃይ ትችላለች። የሁልጊዜም አሳቧ ግን .... "እቀይረዋለሁ" ብላ መታገል ነው። ጓደኞቿ ተይ ሲሏት፣ ቤተሰብ ይቅርብሽ ሲላት .... እድል በእድል ላይ መስጠቷን ትቀጥላለች፤ ነገ ጥቅሜን ተረድቶ ይስተካከላል በሚል። ይሄ የሴት ልጅ ፍቅር ውበቱ እና ህመሙ ነው። ቁስሏን አልፎ የሚገለጥ መሆኑ ንፅህናውን ያሳያል።
ሴት ልጅ ፍቅርን ከተፈጥሮ ትቀዳለች .... መልሳ አለስስት ትሰጣለች .... ምክንያት፣ ድካም፣ ጊዜም ሆነ ሌላ ፈተና ያጠነክረዋል እንጂ አይፈታውም።
~
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988


30.04.202515:58
✅️ Date Rape Drugs" ስለሚባሉ ለወሲብ ጥቃት ስለሚውሉ መድኃኒቶች ታውቃላቹ? በብዛት GHB እና Rohypnol ናቸው የሚታወቁት ወይም ጥቅም ላይ እየዋሉት ያሉት፤ ሆኖም ብዙ መድኃኒቶች አሉ።
✅️ "እነዚህ መድኃኒቶች ለሕክምና ነው የሚውሉት፤ ሆኖም በብላክ ማርኬት እየተሸጡ ለሌሎች አገልግሎቶች ለወንጀል ይውላሉ። አንዱና ትልቁ በጣም አሳሳቢና አስጊ የሆነው ለወሲብ ጥቃት መዋላቸው ነው።
✅️እንደመድኃኒቱ አይነት የሚወስደው ሰው ላይም የሚያደርሰው ጉዳት ይለያያል። አንዳንዱ zombie ያደርጋል - እራሳችሁን አትስቱም አቅላችሁን እንጂ፤ ትንቀሳቀሳላችሁ እንደማንኛውም ጤነኛ ሰው ግን ምን እያደረጋችሁ እንደሆነ አታውቁም መድኃኒቱ ከሰውነታችሁ እስኪወጣ።
✅️ሌላው በተመሳሳይ መንገድ አቅላችሁን ያስታል - ከፍተኛ ጤናማ ያልሆነ የወሲብ ፍላጎት ያሳድርባችኋል፤ ብቻ በየትኛውም መድኃኒት ለወሲብ ጥቃት ትጋለጡበታላቹ።
"እራሳችሁን የምታውቁት መድኃኒቱ ከሰውነታችሁ ሲወጣ ነው፤ ችግሩ ምንም አታስታውሱም መድኃኒቱን ከወሰዳችሁበት ሰዓት ጀምሮ የተፈጠረውን።
መድኃኒቱ ታብሌት ፈሳሽም ሊሆን ይችላል፤ በምትበሉት በምትጠጡት ነገሮች ውስጥ ሊሰጣችሁ ይችላል።
✅️ ለህዝቦቻቸው የሚጨነቁ ሀገራት የጤና ባለሙያዎችና ፖሊስ ዲፓርትመንቶች ህዝቦቻቸው በተለይ ወጣቶች በሚዝናኑበት ወቅት የሚጠቀሟቸው ነገሮች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እየመከሩ ነው፤ ምክንያቱም በከፍተኛ ደረጃ በዚህ መንገድ ጥቃት የሚፈፀምባቸው የተለያየ ወንጀሎች በመበራከታቸው ነው። የወሲብ ጥቃት ብቻ ሳይሆን ዝርፍያ የመግደልም ወንጀል ይሆናል።
✅️ አንዳንድ መድኃኒቶች በምርመራም መወሰዳቸው ላይታወቅ በደም ላይገኙ ይችላሉ ከረጅም ሰዓታት በኋላ። እድሜ ለቴክኖሎጂ በዚህ መንገድ የወሲብ ጥቃት የተፈፀመባቸው ሰዎች መድኃኒቱ በደማቸው ባይገኝም ማስታወስ ባይችሉም እንኳን በሕክምና አንዲት ሴት ፈልጋ ነው ሳትፈልግ ወሲብ የተፈፀመው የሚለውን ማረጋገጥ ይችላል።
✔️ በጣም አስፈሪው ደግሞ አንድ ይህን መድኃኒት የተሰጠው ሰው እንደጤነኛ ሰው ስለሚንቀሳቀስ የታዘዘውን ስለሚያደርግ ይህን የተመለከተ ሌላ ሰው መድኃኒቱን መውሰዳቸውን ስለማያስተውል ፈልገው ጥቃት ከፈፀመባቸው ሰው ጋር ቤርጎ ሲይዙ እቤቱ መኪናው ላይ ሲገቡ የተለያየ ነገር በፍቃደኝነት ሲያደርጉ ስለሚታዩ ሰዎች ላያምኗቸው ይችላሉ "ተገደን ነው" ሲሉ መድኃኒቱ ከደማቸው ከወጣ ከነቁ በኋላ ፈልገው ያደረጉትን ለተለያየ ጥቅም እየዋሹ ሊመስል ይችላል።
እንዳልኳችሁ ለወሲብ ጥቃት በብዛት ቢውል እንጂ ለተለያየ ወንጀል ይውላል፤ በዚህ ወንጀል ሴቶች ብቻ ሳይሆን ወንዶችም ተጠቂ ናቸው። ብዙ በዚህ መንገድ የተገደሉ የተዘረፉ የወሲብ ጥቃት የደረሰባቸው ወንዶች አሉ፤ ስለወሲብ ጥቃት ትንኮሳ ሲወራ የዚህ ሰለባዎች አብዛኛውን ብልጫ ሴቶች ቢይዙ እንጂ ወንዶችም ሰለባ ናቸው።
በየመዝናኛ ቦታው ስትዝናኑ ፍለፊታችሁ ያልተከፈተ ነገር አትጠጡ፤ የተቀዳላችሁን መጠጥ ሳትጨርሱ አስቀምጣችሁ ሽንት ቤት የመሳሰሉት ቦታ ሄዳችሁ መጥታችሁ አትጠጡ፤ ባጠቃላይ ዞር አትበሉ ከብርጭቆአችሁ። ከማታውቁት ሰው የምግብ የመጠጥ ግብዣ ስትቀበሉ ጥንቃቄ አድርጉ፤ መዝናኛ ቦታዎች ብቻ
✔️ምን ልላችሁ ነው ፍፁም ከማትጠረጥሯቸውም ሰዎች የኔ በምትሏቸውም ሰዎች የትም ማንም ብትሆኑ ጥቃት ይፈፀምባችኋል።
በዚህ ዙርያ የተሰሩ ዶክመንተሪዎችን ሳይ በጣም ያስገረመኝ በዚህ መድኃኒት ንግድ ውስጥ በብዛት ሴቶች ናቸው የተሰማሩት፤ በብዛት ታዋቂ ሴቶች አርቲስት ፖለቲከኞች የመሳሰሉት።
✅ ለምሳሌ አርቲስቶች "
✅️ "እነዚህ መድኃኒቶች ለሕክምና ነው የሚውሉት፤ ሆኖም በብላክ ማርኬት እየተሸጡ ለሌሎች አገልግሎቶች ለወንጀል ይውላሉ። አንዱና ትልቁ በጣም አሳሳቢና አስጊ የሆነው ለወሲብ ጥቃት መዋላቸው ነው።
✅️እንደመድኃኒቱ አይነት የሚወስደው ሰው ላይም የሚያደርሰው ጉዳት ይለያያል። አንዳንዱ zombie ያደርጋል - እራሳችሁን አትስቱም አቅላችሁን እንጂ፤ ትንቀሳቀሳላችሁ እንደማንኛውም ጤነኛ ሰው ግን ምን እያደረጋችሁ እንደሆነ አታውቁም መድኃኒቱ ከሰውነታችሁ እስኪወጣ።
✅️ሌላው በተመሳሳይ መንገድ አቅላችሁን ያስታል - ከፍተኛ ጤናማ ያልሆነ የወሲብ ፍላጎት ያሳድርባችኋል፤ ብቻ በየትኛውም መድኃኒት ለወሲብ ጥቃት ትጋለጡበታላቹ።
"እራሳችሁን የምታውቁት መድኃኒቱ ከሰውነታችሁ ሲወጣ ነው፤ ችግሩ ምንም አታስታውሱም መድኃኒቱን ከወሰዳችሁበት ሰዓት ጀምሮ የተፈጠረውን።
መድኃኒቱ ታብሌት ፈሳሽም ሊሆን ይችላል፤ በምትበሉት በምትጠጡት ነገሮች ውስጥ ሊሰጣችሁ ይችላል።
✅️ ለህዝቦቻቸው የሚጨነቁ ሀገራት የጤና ባለሙያዎችና ፖሊስ ዲፓርትመንቶች ህዝቦቻቸው በተለይ ወጣቶች በሚዝናኑበት ወቅት የሚጠቀሟቸው ነገሮች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እየመከሩ ነው፤ ምክንያቱም በከፍተኛ ደረጃ በዚህ መንገድ ጥቃት የሚፈፀምባቸው የተለያየ ወንጀሎች በመበራከታቸው ነው። የወሲብ ጥቃት ብቻ ሳይሆን ዝርፍያ የመግደልም ወንጀል ይሆናል።
✅️ አንዳንድ መድኃኒቶች በምርመራም መወሰዳቸው ላይታወቅ በደም ላይገኙ ይችላሉ ከረጅም ሰዓታት በኋላ። እድሜ ለቴክኖሎጂ በዚህ መንገድ የወሲብ ጥቃት የተፈፀመባቸው ሰዎች መድኃኒቱ በደማቸው ባይገኝም ማስታወስ ባይችሉም እንኳን በሕክምና አንዲት ሴት ፈልጋ ነው ሳትፈልግ ወሲብ የተፈፀመው የሚለውን ማረጋገጥ ይችላል።
✔️ በጣም አስፈሪው ደግሞ አንድ ይህን መድኃኒት የተሰጠው ሰው እንደጤነኛ ሰው ስለሚንቀሳቀስ የታዘዘውን ስለሚያደርግ ይህን የተመለከተ ሌላ ሰው መድኃኒቱን መውሰዳቸውን ስለማያስተውል ፈልገው ጥቃት ከፈፀመባቸው ሰው ጋር ቤርጎ ሲይዙ እቤቱ መኪናው ላይ ሲገቡ የተለያየ ነገር በፍቃደኝነት ሲያደርጉ ስለሚታዩ ሰዎች ላያምኗቸው ይችላሉ "ተገደን ነው" ሲሉ መድኃኒቱ ከደማቸው ከወጣ ከነቁ በኋላ ፈልገው ያደረጉትን ለተለያየ ጥቅም እየዋሹ ሊመስል ይችላል።
እንዳልኳችሁ ለወሲብ ጥቃት በብዛት ቢውል እንጂ ለተለያየ ወንጀል ይውላል፤ በዚህ ወንጀል ሴቶች ብቻ ሳይሆን ወንዶችም ተጠቂ ናቸው። ብዙ በዚህ መንገድ የተገደሉ የተዘረፉ የወሲብ ጥቃት የደረሰባቸው ወንዶች አሉ፤ ስለወሲብ ጥቃት ትንኮሳ ሲወራ የዚህ ሰለባዎች አብዛኛውን ብልጫ ሴቶች ቢይዙ እንጂ ወንዶችም ሰለባ ናቸው።
በየመዝናኛ ቦታው ስትዝናኑ ፍለፊታችሁ ያልተከፈተ ነገር አትጠጡ፤ የተቀዳላችሁን መጠጥ ሳትጨርሱ አስቀምጣችሁ ሽንት ቤት የመሳሰሉት ቦታ ሄዳችሁ መጥታችሁ አትጠጡ፤ ባጠቃላይ ዞር አትበሉ ከብርጭቆአችሁ። ከማታውቁት ሰው የምግብ የመጠጥ ግብዣ ስትቀበሉ ጥንቃቄ አድርጉ፤ መዝናኛ ቦታዎች ብቻ
ሳይሆን በየቤቱ በተለያየ ቦታ በሚደረግላችሁ ግብዣ ላይም ጥንቃቄ ያስፈልጋል።
በቅርብ ኢራቅ ውስጥ አንድ ዶክመንተሪ ላይ አንድ ኡዝታዝ ቁርዓን የሚያስቀራ በአካባቢው ታዋቂ የሚከበር ሰው ቁርዓን እንዲቀራላቸው ቤቱ ይሄዱ የነበሩ ሴቶች እያደነዘዘ ደፍሮ በመጨረሻ አንዷ ተበቅላው ገላው ዶክመንተሪ ተሰርቶ አይቻለሁ
። ✔️ምን ልላችሁ ነው ፍፁም ከማትጠረጥሯቸውም ሰዎች የኔ በምትሏቸውም ሰዎች የትም ማንም ብትሆኑ ጥቃት ይፈፀምባችኋል።
በዚህ ዙርያ የተሰሩ ዶክመንተሪዎችን ሳይ በጣም ያስገረመኝ በዚህ መድኃኒት ንግድ ውስጥ በብዛት ሴቶች ናቸው የተሰማሩት፤ በብዛት ታዋቂ ሴቶች አርቲስት ፖለቲከኞች የመሳሰሉት።
✅ ለምሳሌ አርቲስቶች "
instagram blogger YouTuber TikToker" የመሳሰሉት "money laundry" ጨምሮ ለአደገኛ ዕፅ ዝውውር ለመሳሰሉት ወንጀል ላይ ይሳተፋሉ፤ ለዚህ ለተለያየ ወንጀል የሚመለምሏቸው አሉ በብር እያታለሉ እና ባንዴ ከበርቴ ሲሆኑ በየሀገሩ ሲዞሩ መጠርጠር አይከፋም "ብሩ ከየት መጣ?" ብሎ። ይህ ብቻ ሳይሆን እራሳቸውም ለተለያየ ወንጀል ጥቃት ሰለባ ይሆናሉ፤ ሊያጠቃቸው ለሚፈልግ እነሱን ለማግኘት ከባድ አይሆንበትም።
ስለዚህም ለማውራት ፈልጌ አልነበረም፤ እራሳችሁን ጠብቁ።


07.05.202514:56
✔️በስተርጅና እድሜው ላይ ሆኖ. . የወጣትነቱን ፎቶ እያየ በትዝታ እንደሚተክዝ ትልቅ ሰው ፡ ከሁለት አመታት በፊት የነበራትን መልክ እያየች የምትተክዘው ይህች የ12 አመት ታዳጊ Rahaf Ayyad ትባላለች ።
....
✔️...Rahaf Ayyad በዚህ እድሜዋ ይህንን መልክ እንድትይዝ የሚያደርግ ህመም የለባትም ነበር ።
ታዳጊዋ Rahaf እንዲህ ስጋዋ አልቆ በአጥንቷ ያስቀራት ረሀብ ነው ። ሰው ሰራሽ ረሀብ 😥
የአለም ህዝብ አይቶ እንዳላየ ችላ ያለው ረሀብ ። እሱ ነው እንዲህ የልጅነት መልኳን የመጠጠው ።
.....
🟢በተለይ ከባለፉት 70 ቀናት ወዲህ እስራኤል የእርዳታ ምግብ ወደ ጋዛ እንዳይገባ በማገዷ ፡ ያቺ ታምር የነበረችው ታዳጊ ችግሩ ተባብሶ ረሀብና የተመጣጠነ ምግብ እጦት እንዲህ አድርጓታል ።
...
🔵ይደክማታል ፡ አቅም ያንሳታል ፡ ትንሽ እንኳን ቀምሳው የሚያበረታት ምግብ በሀገሩ የለም ፡ እና ፡ የአሁን መልኳን ሳይሆን በወላጆቿ ስልክ ላይ የተነሳችውን የዛን የመልካም ጊዜ ምስሏን እያየች ከድካምና ከረሀቧ ጋር ስትታገል ትውላለች ።
.....
✔️ፍትህ ያለወንጀላቸው እየተቀጡ ላሉ ፍልስጤማውያን ህጻናት ❤️
Wassihun tesfaye
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
....
✔️...Rahaf Ayyad በዚህ እድሜዋ ይህንን መልክ እንድትይዝ የሚያደርግ ህመም የለባትም ነበር ።
ታዳጊዋ Rahaf እንዲህ ስጋዋ አልቆ በአጥንቷ ያስቀራት ረሀብ ነው ። ሰው ሰራሽ ረሀብ 😥
የአለም ህዝብ አይቶ እንዳላየ ችላ ያለው ረሀብ ። እሱ ነው እንዲህ የልጅነት መልኳን የመጠጠው ።
.....
🟢በተለይ ከባለፉት 70 ቀናት ወዲህ እስራኤል የእርዳታ ምግብ ወደ ጋዛ እንዳይገባ በማገዷ ፡ ያቺ ታምር የነበረችው ታዳጊ ችግሩ ተባብሶ ረሀብና የተመጣጠነ ምግብ እጦት እንዲህ አድርጓታል ።
...
🔵ይደክማታል ፡ አቅም ያንሳታል ፡ ትንሽ እንኳን ቀምሳው የሚያበረታት ምግብ በሀገሩ የለም ፡ እና ፡ የአሁን መልኳን ሳይሆን በወላጆቿ ስልክ ላይ የተነሳችውን የዛን የመልካም ጊዜ ምስሏን እያየች ከድካምና ከረሀቧ ጋር ስትታገል ትውላለች ።
.....
✔️ፍትህ ያለወንጀላቸው እየተቀጡ ላሉ ፍልስጤማውያን ህጻናት ❤️
Wassihun tesfaye
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
07.05.202519:50
✨✨ፍቅር ቅብ-17✨✨
"እድል.....".....አለኝና ወደ ወንበሩ ጠቆመኝ.....የያዘውን ትኩስ ምድጃ ለማስቀመጥ እንደሚጣደፍ ሰው ተንድርድሬ ተቀመጥኩ....
ከተቀመጥኩ በኃላ ከቫይረሱ ጋር እንዴት እንደሚኖር አጭር መግለጫ ሲሰጥ ውስጤ ሰለለ...የተቀመጥኩበት ወንበር እንዲያሰምጠኝ ተመኘሁ....መሬት አፏን ከፍታ እንድትውጠኝ ተመኘሁ....እንዳለቀ ጢስ መሰወር አሰኘኝ....መጥፋት እና "በፎቶው ላይ የምትመለከቷት ወጣት እድል ሰጠኝ በእለተ ሀሙስ ከቤት እንደወጣች አልተመለሰችም....በእለቱ የለበሰችው ልብስ....."......ምናምን የሚል የራሴን አፋልጉኝ ማስታወቂያ መንገድ ዳር ቆሞ ማንበብ አማረኝ......
"በቃ እንግዲህ እድል እራስሽን አዘጋጂ...."....."መኖር ይቻላል እኮ.....".....ሌላ ሌላም አልኩ....."ግን አባትሽ ምን ይላል..."...."ለእትሽ ምን ትያታለሽ....".....ጡዘት።
"እውነቱን ለመናገር ከበሽታው በላይ በሽታው ወደ እኔ የመጣበት መንገድ ያንገበግበኛል.... ስንት ቀን ለፍቼ ያመጣሁት በሽታ እንደሆነ ብታውቅ....".....አልኩት እና ፈገግ አልኩለት ልጅ እግር ዶክተሩን....ተረጋግቻለሁ.....መረጋጋቴ ለራሴ ራሱ አልገባኝም.....እንዴት እረጋጋለሁ....?....እንዴት አይኔ ደረቀ....?....መርበትበት አልነበረብኝም.....?....እድል ስጠኝ ያልኩትን አምላክ ላይ መጮህ አልነበረብኝም.....ተረጋግቻለሁ.....ጭንቅላቴ ነገርየውን ገና ፕሮሰስ አላደረገውም ይሆን አላውቅም....ተረጋግቻለሁ።
"ይኧውልሽ እድል.....".....ከማለቱ አቋረጥኩት....ትንሽ ትንሽ ገባኝ....ፈግታዬ ከት ወዳለ ሳቅ ተለወጠ...."እንዴት በባዶ ሆዴ ለፍቼ ያመጣሁት እንደሆነ ብታውቅ ትሸልመኝ ነበር ካካካካካ...."....ሳቄ እንባ ቀላቀለ.....አእምሮዬ ከቁጥጥሬ ውጪ ወደመሆን አዘነበለ.....
"እድል!!!......".....አለና ጠረጴዛውን አንድ ጊዜ በመዳፉ ለጠፈው....
"እድለ ቢስ ብትለኝ አይሻልም....".....አፈጠጥኩበት።
"አንድ ጊዜ ተረጋግተሽ.....".....አሁንም አቋረጥኩት.....
"ስለምን መረጋጋት ነው የምታወራኝ....የምስራች እንደሚነግር ሰው ነጭ ለብሶ መቀመጥማ ቀላል ነው.....ቀላል ነው.....ከቫይረሱ ጋር መኖር ይቻላል ማለትማ ቀላል ነው.....ቆይ መኖር ምንድን ነው.....?....መኖር ላንተ ምንድን ነው.....በየእለቱ አየር መማግና መስደድ ነው ....?......"......እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ......
ወትሮም የምኖር አይመስለኝም.....አንዳንዴ 'መኖር አስጠላኝ' እልና መልሼ 'እየኖርኩ ነው እንዴ' እላለሁ.....ለኔ መኖር እንዲህ አይደለም።
"ዶክተር ፍቅር ይዞኛል እኮ.....ልቤ የሚያርፍበት አጊኝቷል እኮ....ዶክተር አልገባህም.....አባቴ ፊቴን አያየውም ከንግዲህ....እናቴ የለችም እኮ....አታውቅም አንተ ታናሽ እህት አለኝ እኮ......"......ከዚህም ከዚያም እያማታሁ ማልቀስ ጀመርኩ....
***
መረጋጋቴን ሲጠብቅ የነበረው ዶክተር ዝምታውን ሰበረ.... ነጩን ጋውን አውልቆ ከረባቱን ፈታ.... ከተሰየመበት ወንበር ተነሳና ፊትለፊቴ ተቀመጠ.....
"እንዳትመክረኝ ዶክተር...መኖር ይቻላል እንዳትለኝ ዶክተር....አውቃለሁ....አውቃለሁ እሱን....እኔን ያንገበገበኝ......".....ከማለቴ ሰፌድ በሚያክለው መዳፉ አፌን ያዘና "ከቫይረሱ ነፃ ነሽ!!!" አለኝ።
*
ውበት አይን ይመርጣል....እንደተመልካቹ ነው.....ለኔ ነፃነትንም እንደዛው ነው..... ነፃ መሆንን ካላወቅንበት ራሱ መታሰር ሊሆን ይችላል......
ህመምን ያለ መድሀኒት አይሰጥም....መድሀኒታችን ምን አልባት እኛ እንደምናስበው አይነት መድሀኒት ላይሆን ይችላል.....ምናልባት የሚፈወሰው መንፈሳችን ይሆናል.....ምናልባት ምግባራችን .....ምናልባት ግንኙነታችን.....ምናልባት ስብእናችን....ምናልባት እኛነታችን።
ወዲያው ትናንት በቤተክርስቲያን ደጃፍ ሳልፍ ጆሮዬን የያዘው ትምህርት ትዝ አለኝ....."እረኛ በጎቹን መጀመሪያ በድምፅ ይገስፃቸዋል.....አልመለስ ካሉ በጅራፍ ከገደል አፋፍ ይመልሳቸዋል....በሽታችሁ ከገደል አፋፍ የመለሳችሁ የላችሁም.....?".....ጥያቄ።
*
እንባዬን ጠራርጌ ልጅ እግሩን ዶክተር አመሰገንኩ....ለሌላ ጊዜ ነፃነትን ለማወጅ እንዲህ የሰው ልብ ከፍ ዝቅ እስኪል ባይጠበቅ መልካም እንደሆነ አሳሰብኩ.....
" ላለፉት ሁለት አመታት በዚህ መልኩ ነው ውጤት የምንናገረው...." አለኝ እየሳቀ.....
"ያልታመመውንም ሰው....?".....በአግርሞት ጠየቅኩ።
"አዎ አለኝ በልበ ሙሉነት...."
"ለምን...."....መልሱን ለመስማት ጓጓሁ።
"ኤቲክሱ ግን ብለሽ የማትከራከሪኝ ከሆነ እነግርሻለሁ....".....አለኝና ያስቀመጠውን ጋውን ለበሰ....
"የልብ ድካም አልያም ሌላ severe case ከሌለባቸው በስተቀር ነፃነታቸውን ከማወጃችን በፊት ነፃነታቸውን ለደይቃዎች እንነጥቃቸዋለን.....አለመያዛቸውን ከመናገራችን በፊት ለደይቃዎች መያዝን አእምሯቸው ውስጥ እንከታለን...."
"እኮ ለምን....?......"
"በነፃ የተገኘ ነፃነት አይዘልቅም.....ያላየነው ስሜት አያስፈራንም....ለማናውቀውን መጥፎ ስሜት አንታገልም....ነፃነት አክባሪውን ያከብራል.....በነፃ አንሰጣቸውም".......አፌን ከፍቼ ቀረሁ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
"እድል.....".....አለኝና ወደ ወንበሩ ጠቆመኝ.....የያዘውን ትኩስ ምድጃ ለማስቀመጥ እንደሚጣደፍ ሰው ተንድርድሬ ተቀመጥኩ....
ከተቀመጥኩ በኃላ ከቫይረሱ ጋር እንዴት እንደሚኖር አጭር መግለጫ ሲሰጥ ውስጤ ሰለለ...የተቀመጥኩበት ወንበር እንዲያሰምጠኝ ተመኘሁ....መሬት አፏን ከፍታ እንድትውጠኝ ተመኘሁ....እንዳለቀ ጢስ መሰወር አሰኘኝ....መጥፋት እና "በፎቶው ላይ የምትመለከቷት ወጣት እድል ሰጠኝ በእለተ ሀሙስ ከቤት እንደወጣች አልተመለሰችም....በእለቱ የለበሰችው ልብስ....."......ምናምን የሚል የራሴን አፋልጉኝ ማስታወቂያ መንገድ ዳር ቆሞ ማንበብ አማረኝ......
"በቃ እንግዲህ እድል እራስሽን አዘጋጂ...."....."መኖር ይቻላል እኮ.....".....ሌላ ሌላም አልኩ....."ግን አባትሽ ምን ይላል..."...."ለእትሽ ምን ትያታለሽ....".....ጡዘት።
"እውነቱን ለመናገር ከበሽታው በላይ በሽታው ወደ እኔ የመጣበት መንገድ ያንገበግበኛል.... ስንት ቀን ለፍቼ ያመጣሁት በሽታ እንደሆነ ብታውቅ....".....አልኩት እና ፈገግ አልኩለት ልጅ እግር ዶክተሩን....ተረጋግቻለሁ.....መረጋጋቴ ለራሴ ራሱ አልገባኝም.....እንዴት እረጋጋለሁ....?....እንዴት አይኔ ደረቀ....?....መርበትበት አልነበረብኝም.....?....እድል ስጠኝ ያልኩትን አምላክ ላይ መጮህ አልነበረብኝም.....ተረጋግቻለሁ.....ጭንቅላቴ ነገርየውን ገና ፕሮሰስ አላደረገውም ይሆን አላውቅም....ተረጋግቻለሁ።
"ይኧውልሽ እድል.....".....ከማለቱ አቋረጥኩት....ትንሽ ትንሽ ገባኝ....ፈግታዬ ከት ወዳለ ሳቅ ተለወጠ...."እንዴት በባዶ ሆዴ ለፍቼ ያመጣሁት እንደሆነ ብታውቅ ትሸልመኝ ነበር ካካካካካ...."....ሳቄ እንባ ቀላቀለ.....አእምሮዬ ከቁጥጥሬ ውጪ ወደመሆን አዘነበለ.....
"እድል!!!......".....አለና ጠረጴዛውን አንድ ጊዜ በመዳፉ ለጠፈው....
"እድለ ቢስ ብትለኝ አይሻልም....".....አፈጠጥኩበት።
"አንድ ጊዜ ተረጋግተሽ.....".....አሁንም አቋረጥኩት.....
"ስለምን መረጋጋት ነው የምታወራኝ....የምስራች እንደሚነግር ሰው ነጭ ለብሶ መቀመጥማ ቀላል ነው.....ቀላል ነው.....ከቫይረሱ ጋር መኖር ይቻላል ማለትማ ቀላል ነው.....ቆይ መኖር ምንድን ነው.....?....መኖር ላንተ ምንድን ነው.....በየእለቱ አየር መማግና መስደድ ነው ....?......"......እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ......
ወትሮም የምኖር አይመስለኝም.....አንዳንዴ 'መኖር አስጠላኝ' እልና መልሼ 'እየኖርኩ ነው እንዴ' እላለሁ.....ለኔ መኖር እንዲህ አይደለም።
"ዶክተር ፍቅር ይዞኛል እኮ.....ልቤ የሚያርፍበት አጊኝቷል እኮ....ዶክተር አልገባህም.....አባቴ ፊቴን አያየውም ከንግዲህ....እናቴ የለችም እኮ....አታውቅም አንተ ታናሽ እህት አለኝ እኮ......"......ከዚህም ከዚያም እያማታሁ ማልቀስ ጀመርኩ....
***
መረጋጋቴን ሲጠብቅ የነበረው ዶክተር ዝምታውን ሰበረ.... ነጩን ጋውን አውልቆ ከረባቱን ፈታ.... ከተሰየመበት ወንበር ተነሳና ፊትለፊቴ ተቀመጠ.....
"እንዳትመክረኝ ዶክተር...መኖር ይቻላል እንዳትለኝ ዶክተር....አውቃለሁ....አውቃለሁ እሱን....እኔን ያንገበገበኝ......".....ከማለቴ ሰፌድ በሚያክለው መዳፉ አፌን ያዘና "ከቫይረሱ ነፃ ነሽ!!!" አለኝ።
*
ውበት አይን ይመርጣል....እንደተመልካቹ ነው.....ለኔ ነፃነትንም እንደዛው ነው..... ነፃ መሆንን ካላወቅንበት ራሱ መታሰር ሊሆን ይችላል......
ህመምን ያለ መድሀኒት አይሰጥም....መድሀኒታችን ምን አልባት እኛ እንደምናስበው አይነት መድሀኒት ላይሆን ይችላል.....ምናልባት የሚፈወሰው መንፈሳችን ይሆናል.....ምናልባት ምግባራችን .....ምናልባት ግንኙነታችን.....ምናልባት ስብእናችን....ምናልባት እኛነታችን።
ወዲያው ትናንት በቤተክርስቲያን ደጃፍ ሳልፍ ጆሮዬን የያዘው ትምህርት ትዝ አለኝ....."እረኛ በጎቹን መጀመሪያ በድምፅ ይገስፃቸዋል.....አልመለስ ካሉ በጅራፍ ከገደል አፋፍ ይመልሳቸዋል....በሽታችሁ ከገደል አፋፍ የመለሳችሁ የላችሁም.....?".....ጥያቄ።
*
እንባዬን ጠራርጌ ልጅ እግሩን ዶክተር አመሰገንኩ....ለሌላ ጊዜ ነፃነትን ለማወጅ እንዲህ የሰው ልብ ከፍ ዝቅ እስኪል ባይጠበቅ መልካም እንደሆነ አሳሰብኩ.....
" ላለፉት ሁለት አመታት በዚህ መልኩ ነው ውጤት የምንናገረው...." አለኝ እየሳቀ.....
"ያልታመመውንም ሰው....?".....በአግርሞት ጠየቅኩ።
"አዎ አለኝ በልበ ሙሉነት...."
"ለምን...."....መልሱን ለመስማት ጓጓሁ።
"ኤቲክሱ ግን ብለሽ የማትከራከሪኝ ከሆነ እነግርሻለሁ....".....አለኝና ያስቀመጠውን ጋውን ለበሰ....
"የልብ ድካም አልያም ሌላ severe case ከሌለባቸው በስተቀር ነፃነታቸውን ከማወጃችን በፊት ነፃነታቸውን ለደይቃዎች እንነጥቃቸዋለን.....አለመያዛቸውን ከመናገራችን በፊት ለደይቃዎች መያዝን አእምሯቸው ውስጥ እንከታለን...."
"እኮ ለምን....?......"
"በነፃ የተገኘ ነፃነት አይዘልቅም.....ያላየነው ስሜት አያስፈራንም....ለማናውቀውን መጥፎ ስሜት አንታገልም....ነፃነት አክባሪውን ያከብራል.....በነፃ አንሰጣቸውም".......አፌን ከፍቼ ቀረሁ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
29.04.202518:01
✨✨ፍቅር ቅብ-11✨✨
ያዘጋጀሁትን ጥቁር ልብስ ለበስኩ....ጥቁር ጫማና ጥቁር ሻርፕም አክዬበት አመሻሽ ላይ ወጣሁ....ከጨለማው ጋር ተመሳሰልኩ....ፊቴ ባይቀላ ኑረቴ እስካያስታውቅ ድረስ ድብን ብያለሁ።
ካለሁበት በጣም ርቄ መሄድ ፈለግኩኝ...."ሩቅ ውሰደኝ" የሚል ቀጭን ትዕዛዝ የሰጠሁት የራይድ ሹፌር በተባለው መሰረት ይርቃል እስካለው ድረስ እየነዳ ነው....በምፈልገው ፍጥነት ግን እየሄድን አይደለም....የኃላ ታሪኩ ዘሎ እንደሚያንቀው ሰው አስር ጊዜ "ፍጠንልኝ" እያልኩት ነው....እሱ እቴ "ልሻገር አልሻገር" ብሎ የሚወላውለውን ሰው ሳይቀር ቆም ብሎ ሊያማክር ይዳዳዋል.....ሰረቅ እያደረገ ያስጀመረውን ሰአት መቁጠሪያ እያየ አካሄዱን ይገመግማል።
"መራቅ አርቄሻለሁ....የት ነው ግን መውረድ የምትፈልጊው...?...የት ልውሰድሽ...?"
"መቃብር ቦታ ውሰደኝ"....ስለው ተንደርድሮ ፍሬኑን ያዘው።
"ከዚህ በላይ መሄድ አልችልም....መመለሻ ነዳጅ የለኝም....እባክሽ ውረጂ የእኔ እህት...."....አለኝ ፍራቻ በቀላቀለ አክብሮት...
ወደ ሰማይ ቤት ለመሄድ መሳፈሪያ ቢኖረው ልከፍለው የምችለውን ገንዘብ አስረክቤ ወረድኩ....እንደወረድኩ መኪናውን አዙሮ ቀደም ባልነበረው ፍጥነት ነዳ።
ሹፌሩ የጣለኝን ቦታ ስቃኘው አካባቢው ግርግር የማይበዛው ሰው አልፎ አልፎ ያለበት ነው...ከምሽቱ አንድ ሰአት ተኩል ይላል....መብራት አልፎ አልፎ ያለበት ቦታ ጋር ተጠግቼ ስለ አካባቢው የምጠይቀውን ሰው መረጣ ገባሁ።
አንድ ከኑሮ የሚከብድ ፊት ያላቸውን አዛውንት አስቁሜ....
"የት ነው ያለሁት" አልኳቸው.....
"አፍዝዘውሽ ነው የኔ እናት....?...አፍዝዘው እዚ ጥለውሸ ነው....?"....አሉኝ እንስፍስፍ ባለ ድምፅ።
"አይደለም አይደለም....ትንሽ የመርሳት ችግር አለብኝ...."....አልኳቸው ሚስኪን ፊት እያሳየኃቸው።
ያለሁበትን ካሳወቁኝ በኃላ ጥያቄ ደገምኩ።
"እዚህ አካባቢ የመቃብር ስፍራ የለም....?."
መልስ አልሰጡኝም.....
ሁለት እግር ሳይሆን አራት እግር እንዳለው ተሽከርካሪ ብን ብለው ከአካባቢው ጠፉ።
ለሰአታት ሲነዝረኝ የነበረው ስልኬ አሁን አደቡን ገዝቷል....በተደጋጋሚ መክብብ እየደወለልኝ እንደነበር አስታውሳለሁ....ምሳ ሰአት የተቃጠርንበት ቦታ ተሰይሞ እየጠበቀኝ እንደሆነ በፅሁፍ መልዕክት አሳውቆኛል....መልስ አልሰጠሁትም።.....ደጋግሞ ደውሎልኛል አላነሳሁትም።.....ቀርተሽ ነው ወይ ብሎ ጠይቆኛል ቀረሁም መጣሁም አላልኩትም....ደህና ነሽ ወይ ብሎኝ ነበረ....እንዲህም ነኝ እንዲያም ነኝ አላልኩትም።
"Are u okay....".....የሚል ስድስተኛ መልዕክት ገባልኝ.....
ደወልኩለት....
"ደህና ነሽ.....?...."....ነበር ያለኝ ስልኩን ከማንሳቱ.....
ድምፄ መቆራረጥ ጀመረ....አንድ ቃል መናገር ጀምሬ ልጨርስህ ስለው ሳጌ መሀል ይገባል....
ጥርሴን ከገለጥኩለት ይልቅ እምባዬን ያሳየሁትን መልቀቅ ይተናነቀኛል....በተቻለኝ አቅም ለመክብብ እምባዬን ላለማሳየት እየሞከርኩ ነበር....የሆነ ነገሬ "የሆድሽን አንድ ሳታስቀሪ ንገሪው" ይለኛል....የሆነ ነገሬ ደግሞ "ገና ትናንት ያወቅሽው ሰው እምባሽን ለማየት ብቁ አይደለም እረፊ" ይለኛል.....በዚህ ትንቅንቅ ውስጥ እያለሁ "የት ነሽ.....?....".....አለኝ....ሁለቴም ሳላስብ የቅድሟ ሴትዮ ነሽ ያሉኝን ቦታ ነገርኩት....በብርሀን ፍጥነት አጠገቤ ተገኘ።
ከመኪናው ወርዶ ፊት ለፊቴ ቆመ....ቀና ብዬ አየሁት....
"የተፈጠረ ነገር አለ....ደህና አይደለሽም.....ሀዘን ነው....ማን ሞቶብሽ ነው....?.....የምረዳሽ ነገር አለ.....?...."....አንዴ አይኔን አንዴ ጥላሸት ልብሴን እያየ በጥያቄ አጣደፈኝ።
"እሙን ታውቃታለህ....?....እናቴ ናት....በጣም ጨካኝ ናት....በ.በ..በጣም በጣም ክፉ ናት....እሙዬ ክፉ ናት...ጨከነችብን....እሙ.."....እቅፉ ውስጥ ሆኜ በእንባ እየታጠብኩኝ እናቴን አማሁለት....
ምንም ሳይለኝ በዝምታ ሰበሰበኝ።
እንደሌሎቹ ቢደናገጥም ፍላጎቴን አክብሮ እዛው አካባቢ ካለ ደብር መቃብር ስፍራ ወሰደኝ......በጤናዬ መቃብር ስፍራ እንደምፈራ ፈጣሪዬን ራሱ አልፈራም....ዛሬ ደፈርኩት....እናቴ ትኖርበታለች ብዬ ስላሰብኩ ነው መሰለኝ ፍርሀቴ በነነ።
ጭው ያለ ዝሞታ መሀል ዝም ያሉ ሟቾች ተኝተው....በቁም የሞትኩት እኔ እና እግር የጣለው መክብብ ቆመን አለን....ጨረቃ ሙሉ ነበረች....በጨረቃ ብርሀን ከሁሉም ገንጠል ብላ እንደመደበቅ ያለች መቃብር ታየችኝ...."እሙ እዛ ጋር ናት" አልኩት በስሜት.....መክብብ ፈርቷል....ወንድነቱ ይዞት ወይ አሳዝኜው እንጂ ቦታው እንዳስጨነቀው ኮፍያ ጥሶ የሚንቆረቆረው ላቡ ያሳብቅበታል።
"እናቴን ማወራት አለኝ እዚሁ ጠብቀኝ..."....አልኩት።
"ጥሩ አይደለም ብቻሽን....አብሬሽ ልምጣ...."....አለኝ በአይበሉባው የግንባሩን ላብ እየጠረገ....
"አታስብ እናቴ አለች....".....ስለው 'ያማታል እንዴ' አስተያየት አየኝ።
"የተከልሻቸውን አትክልቶች እግርሽ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወር ብሎ የሚያያቸው ጠፍቷል....ያሳደግሻት ውሻ ሞታለች....አልነገርኩሽም አይደል ቀዬው ጥላ ርቆታል....የቡናው ሽታ እንደ ድሮው አይደለም....አንቺ ያልጠመቅሽው ጠላ ደም ደም ይላል...ያለአንቺ ህይወት ከእሬት ይመራል.....".....የማላውቃት ሴትዮ መቃብር ፊት ቆሜ መለፍለፍ ጀመርኩ።
"ባለፈው ታናሽ ወንድምሽ መጥቶ ለአባዬ 'ለአስካል ለምን የቁም ተስካር አታወጡላትም....እስከመቼ ትጠብቃላችሁ.....እኛ አውጥተን ነው እርማችንን ያወጣነው....'....ሲለው ጥንብ እርኩሱን ብሎ አባረረው....አየሽ አባዬም ይጠብቅሻል።
ሞተሻል እናልቅስልሽ....?....ትመጫለሽ እንጠብቅሽ...?...."......የመቃብሩን አፈር እየዳበስኩ እጠይቃለሁ።
ተይ እሙ......የኔ ወርቅ ተይ...የኔ እናት የት ነው ያለሽው.....እዚህ ነኝ ማለት ይከብዳል....?....እዚህ ነኝ አትድረሱብኝ ብትዪን ምን አለ....ነብሴ ተጨነቀችብሽ እኮ....አባዬን ፀፀት አስረጀው እኮ....
እሙ ተይ....
ተይ እማ....
እዚህ ነኝ ሳልል ለጨዋታ ስሄድ እንዴት ነብስሽ ትጨነቅ ነበር.....?....እዚህ ነኝ ሳይሉ መሄድን ከየት አመጣሸው....
እንደወጡ መቅረትን ከየት ተማርሽው...
እህቴን ባየሻት ምን እንዳከለች....ልጅሽን ብታያት እንዴት ቆንጆ እንደሆነች....
ባንድ ጊዜ ፍቅርም ጥላቻም እየተፈራረቁ አሳሬን አበሉኝ።
መክብብ ከኃላ ትከሻዬን እስኪነካኝ ድረስ በማላውቃት ሴትዮ በድን ፊት ከእናቴ ጋር ነበርኩ።
ይበቃል እንሂድ አለኝና እጄን አጥብቆ ያዘኝ.....
**
"ግን ለምንድን ነው በጨለማ እዚህ መምጣት የፈለግሺው" አለኝ መኪናው ውስጥ ከገባን በኃላ።
"በጨለማ የወጣችውን እናቴን በጨለማ መቅበር ፈልጌ...." አልኩት።
መልስ አልሰጠኝም።
አላለቀም.......
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
ያዘጋጀሁትን ጥቁር ልብስ ለበስኩ....ጥቁር ጫማና ጥቁር ሻርፕም አክዬበት አመሻሽ ላይ ወጣሁ....ከጨለማው ጋር ተመሳሰልኩ....ፊቴ ባይቀላ ኑረቴ እስካያስታውቅ ድረስ ድብን ብያለሁ።
ካለሁበት በጣም ርቄ መሄድ ፈለግኩኝ...."ሩቅ ውሰደኝ" የሚል ቀጭን ትዕዛዝ የሰጠሁት የራይድ ሹፌር በተባለው መሰረት ይርቃል እስካለው ድረስ እየነዳ ነው....በምፈልገው ፍጥነት ግን እየሄድን አይደለም....የኃላ ታሪኩ ዘሎ እንደሚያንቀው ሰው አስር ጊዜ "ፍጠንልኝ" እያልኩት ነው....እሱ እቴ "ልሻገር አልሻገር" ብሎ የሚወላውለውን ሰው ሳይቀር ቆም ብሎ ሊያማክር ይዳዳዋል.....ሰረቅ እያደረገ ያስጀመረውን ሰአት መቁጠሪያ እያየ አካሄዱን ይገመግማል።
"መራቅ አርቄሻለሁ....የት ነው ግን መውረድ የምትፈልጊው...?...የት ልውሰድሽ...?"
"መቃብር ቦታ ውሰደኝ"....ስለው ተንደርድሮ ፍሬኑን ያዘው።
"ከዚህ በላይ መሄድ አልችልም....መመለሻ ነዳጅ የለኝም....እባክሽ ውረጂ የእኔ እህት...."....አለኝ ፍራቻ በቀላቀለ አክብሮት...
ወደ ሰማይ ቤት ለመሄድ መሳፈሪያ ቢኖረው ልከፍለው የምችለውን ገንዘብ አስረክቤ ወረድኩ....እንደወረድኩ መኪናውን አዙሮ ቀደም ባልነበረው ፍጥነት ነዳ።
ሹፌሩ የጣለኝን ቦታ ስቃኘው አካባቢው ግርግር የማይበዛው ሰው አልፎ አልፎ ያለበት ነው...ከምሽቱ አንድ ሰአት ተኩል ይላል....መብራት አልፎ አልፎ ያለበት ቦታ ጋር ተጠግቼ ስለ አካባቢው የምጠይቀውን ሰው መረጣ ገባሁ።
አንድ ከኑሮ የሚከብድ ፊት ያላቸውን አዛውንት አስቁሜ....
"የት ነው ያለሁት" አልኳቸው.....
"አፍዝዘውሽ ነው የኔ እናት....?...አፍዝዘው እዚ ጥለውሸ ነው....?"....አሉኝ እንስፍስፍ ባለ ድምፅ።
"አይደለም አይደለም....ትንሽ የመርሳት ችግር አለብኝ...."....አልኳቸው ሚስኪን ፊት እያሳየኃቸው።
ያለሁበትን ካሳወቁኝ በኃላ ጥያቄ ደገምኩ።
"እዚህ አካባቢ የመቃብር ስፍራ የለም....?."
መልስ አልሰጡኝም.....
ሁለት እግር ሳይሆን አራት እግር እንዳለው ተሽከርካሪ ብን ብለው ከአካባቢው ጠፉ።
ለሰአታት ሲነዝረኝ የነበረው ስልኬ አሁን አደቡን ገዝቷል....በተደጋጋሚ መክብብ እየደወለልኝ እንደነበር አስታውሳለሁ....ምሳ ሰአት የተቃጠርንበት ቦታ ተሰይሞ እየጠበቀኝ እንደሆነ በፅሁፍ መልዕክት አሳውቆኛል....መልስ አልሰጠሁትም።.....ደጋግሞ ደውሎልኛል አላነሳሁትም።.....ቀርተሽ ነው ወይ ብሎ ጠይቆኛል ቀረሁም መጣሁም አላልኩትም....ደህና ነሽ ወይ ብሎኝ ነበረ....እንዲህም ነኝ እንዲያም ነኝ አላልኩትም።
"Are u okay....".....የሚል ስድስተኛ መልዕክት ገባልኝ.....
ደወልኩለት....
"ደህና ነሽ.....?...."....ነበር ያለኝ ስልኩን ከማንሳቱ.....
ድምፄ መቆራረጥ ጀመረ....አንድ ቃል መናገር ጀምሬ ልጨርስህ ስለው ሳጌ መሀል ይገባል....
ጥርሴን ከገለጥኩለት ይልቅ እምባዬን ያሳየሁትን መልቀቅ ይተናነቀኛል....በተቻለኝ አቅም ለመክብብ እምባዬን ላለማሳየት እየሞከርኩ ነበር....የሆነ ነገሬ "የሆድሽን አንድ ሳታስቀሪ ንገሪው" ይለኛል....የሆነ ነገሬ ደግሞ "ገና ትናንት ያወቅሽው ሰው እምባሽን ለማየት ብቁ አይደለም እረፊ" ይለኛል.....በዚህ ትንቅንቅ ውስጥ እያለሁ "የት ነሽ.....?....".....አለኝ....ሁለቴም ሳላስብ የቅድሟ ሴትዮ ነሽ ያሉኝን ቦታ ነገርኩት....በብርሀን ፍጥነት አጠገቤ ተገኘ።
ከመኪናው ወርዶ ፊት ለፊቴ ቆመ....ቀና ብዬ አየሁት....
"የተፈጠረ ነገር አለ....ደህና አይደለሽም.....ሀዘን ነው....ማን ሞቶብሽ ነው....?.....የምረዳሽ ነገር አለ.....?...."....አንዴ አይኔን አንዴ ጥላሸት ልብሴን እያየ በጥያቄ አጣደፈኝ።
"እሙን ታውቃታለህ....?....እናቴ ናት....በጣም ጨካኝ ናት....በ.በ..በጣም በጣም ክፉ ናት....እሙዬ ክፉ ናት...ጨከነችብን....እሙ.."....እቅፉ ውስጥ ሆኜ በእንባ እየታጠብኩኝ እናቴን አማሁለት....
ምንም ሳይለኝ በዝምታ ሰበሰበኝ።
እንደሌሎቹ ቢደናገጥም ፍላጎቴን አክብሮ እዛው አካባቢ ካለ ደብር መቃብር ስፍራ ወሰደኝ......በጤናዬ መቃብር ስፍራ እንደምፈራ ፈጣሪዬን ራሱ አልፈራም....ዛሬ ደፈርኩት....እናቴ ትኖርበታለች ብዬ ስላሰብኩ ነው መሰለኝ ፍርሀቴ በነነ።
ጭው ያለ ዝሞታ መሀል ዝም ያሉ ሟቾች ተኝተው....በቁም የሞትኩት እኔ እና እግር የጣለው መክብብ ቆመን አለን....ጨረቃ ሙሉ ነበረች....በጨረቃ ብርሀን ከሁሉም ገንጠል ብላ እንደመደበቅ ያለች መቃብር ታየችኝ...."እሙ እዛ ጋር ናት" አልኩት በስሜት.....መክብብ ፈርቷል....ወንድነቱ ይዞት ወይ አሳዝኜው እንጂ ቦታው እንዳስጨነቀው ኮፍያ ጥሶ የሚንቆረቆረው ላቡ ያሳብቅበታል።
"እናቴን ማወራት አለኝ እዚሁ ጠብቀኝ..."....አልኩት።
"ጥሩ አይደለም ብቻሽን....አብሬሽ ልምጣ...."....አለኝ በአይበሉባው የግንባሩን ላብ እየጠረገ....
"አታስብ እናቴ አለች....".....ስለው 'ያማታል እንዴ' አስተያየት አየኝ።
"የተከልሻቸውን አትክልቶች እግርሽ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወር ብሎ የሚያያቸው ጠፍቷል....ያሳደግሻት ውሻ ሞታለች....አልነገርኩሽም አይደል ቀዬው ጥላ ርቆታል....የቡናው ሽታ እንደ ድሮው አይደለም....አንቺ ያልጠመቅሽው ጠላ ደም ደም ይላል...ያለአንቺ ህይወት ከእሬት ይመራል.....".....የማላውቃት ሴትዮ መቃብር ፊት ቆሜ መለፍለፍ ጀመርኩ።
"ባለፈው ታናሽ ወንድምሽ መጥቶ ለአባዬ 'ለአስካል ለምን የቁም ተስካር አታወጡላትም....እስከመቼ ትጠብቃላችሁ.....እኛ አውጥተን ነው እርማችንን ያወጣነው....'....ሲለው ጥንብ እርኩሱን ብሎ አባረረው....አየሽ አባዬም ይጠብቅሻል።
ሞተሻል እናልቅስልሽ....?....ትመጫለሽ እንጠብቅሽ...?...."......የመቃብሩን አፈር እየዳበስኩ እጠይቃለሁ።
ተይ እሙ......የኔ ወርቅ ተይ...የኔ እናት የት ነው ያለሽው.....እዚህ ነኝ ማለት ይከብዳል....?....እዚህ ነኝ አትድረሱብኝ ብትዪን ምን አለ....ነብሴ ተጨነቀችብሽ እኮ....አባዬን ፀፀት አስረጀው እኮ....
እሙ ተይ....
ተይ እማ....
እዚህ ነኝ ሳልል ለጨዋታ ስሄድ እንዴት ነብስሽ ትጨነቅ ነበር.....?....እዚህ ነኝ ሳይሉ መሄድን ከየት አመጣሸው....
እንደወጡ መቅረትን ከየት ተማርሽው...
እህቴን ባየሻት ምን እንዳከለች....ልጅሽን ብታያት እንዴት ቆንጆ እንደሆነች....
ባንድ ጊዜ ፍቅርም ጥላቻም እየተፈራረቁ አሳሬን አበሉኝ።
መክብብ ከኃላ ትከሻዬን እስኪነካኝ ድረስ በማላውቃት ሴትዮ በድን ፊት ከእናቴ ጋር ነበርኩ።
ይበቃል እንሂድ አለኝና እጄን አጥብቆ ያዘኝ.....
**
"ግን ለምንድን ነው በጨለማ እዚህ መምጣት የፈለግሺው" አለኝ መኪናው ውስጥ ከገባን በኃላ።
"በጨለማ የወጣችውን እናቴን በጨለማ መቅበር ፈልጌ...." አልኩት።
መልስ አልሰጠኝም።
አላለቀም.......
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka


27.04.202508:54
☑️ አንድ በእድሜ ገፋ ያለ ሽማግሌ ለሚስቱ ለሊት ላይ የማንኮራፏቷ ድምፅ አስቸግሮት ስሞታ ያቀርብላታል። ሚስቱም እኔ የለብኝም ብላው ትክድ ነበር። ይህ ነገር ሲደጋገምበት አንድ ለሊት ላይ ሆን ብሎ ይጠብቅና ለንግግሩ እውነታ ማስረጃ እንዲሆንለት ስታንኮራፋ ለመቅረፅ አሰበ። እንዳሰበውም ቀረፀና አስቀመጠው።
✅ ሌቱ ሲነጋ እሷ ተኝታ ነበር የቀረፀውን ሊያሳያት ይቀሰቅሳታል። እሷ ግን የመጨረሻ ለሊቷ ስለነበር መነሳት አልቻለችም። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ የማንኮራፋቷ ድምፅ ማታ ማታ ሁሌም ልክ እንደ አዝካሩን-ነውም እየደጋገመ ይሰማታል። ... 💔😪
✅ ከቅርብ ወዳጅህ
የሚመጣብህን ችግር ቻለውና እለፈው
ምናልባት ይህ ችግር አለኝታ እንዲሆንልህና
ያንን ሰው ከጎንህ እንዳታጣው የምትመኝበት
ጊዜ ሊመጣ ይችላልና። 🙏
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
✅ ሌቱ ሲነጋ እሷ ተኝታ ነበር የቀረፀውን ሊያሳያት ይቀሰቅሳታል። እሷ ግን የመጨረሻ ለሊቷ ስለነበር መነሳት አልቻለችም። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ የማንኮራፋቷ ድምፅ ማታ ማታ ሁሌም ልክ እንደ አዝካሩን-ነውም እየደጋገመ ይሰማታል። ... 💔😪
✅ ከቅርብ ወዳጅህ
የሚመጣብህን ችግር ቻለውና እለፈው
ምናልባት ይህ ችግር አለኝታ እንዲሆንልህና
ያንን ሰው ከጎንህ እንዳታጣው የምትመኝበት
ጊዜ ሊመጣ ይችላልና። 🙏
📨@Enmare1988
📨@Enmare1988
登录以解锁更多功能。