Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
TIKVAH-SPORT avatar

TIKVAH-SPORT

Sports
TGlist rating
0
0
TypePublic
Verification
Not verified
Trust
Not trusted
LocationЕфіопія
LanguageOther
Channel creation dateFeb 06, 2025
Added to TGlist
Jul 31, 2024
Linked chat

Records

21.04.202512:45
259.9KSubscribers
15.08.202423:59
100Citation index
12.08.202417:11
62KAverage views per post
13.02.202518:34
53.7KAverage views per ad post
12.09.202423:59
9.99%ER
12.08.202417:11
26.39%ERR

Popular posts TIKVAH-SPORT

“ ቀጣዩ ጨዋታ ከዚህ የተለየ ይሆናል “ ቫዝኩዌስ

የሎስ ብላንኮዎቹ ተጨዋች ሉካስ ቫዝኩዌስ አርሰናል በሪያል ማድሪድ ላይ የበላይ ሆኖ ማምሸቱን ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

“ ጥሩ አልተጫወትንም አርሰናል የተሻለ ተንቀሳቅሷል እኛ ላይ ጫና መፍጠር ችለዋል።“ ሲል ሉካስ ቫዝኩዌስ ተናግሯል።

አክሎም “ የመልሱ ጨዋታ የተለየ ይሆናል ማድረግ እንችላለን “ ሲል ውጤቱን መቀልበስ እንደሚችሉ ገልጿል።

ተከላካዩ ራውል አሴንስዮ በበኩሉ “ ከራሳችን ጋር አልነበርንም ነገርግን መቀልበስ እንችላለን ሳምንት ደጋፊው ያስፈልገናል “ ብሏል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
“ ያለ ጋርዲዮላ እዚህ አልሆንም ነበር “ አርቴታ

የአርሰናል አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ያለ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አሁን ያለሁበት አልሆንም ነበር በማለት ተናግረዋል።

“ ክብሩን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ይውሰድ “ ያሉት ሚኬል አርቴታ ያለ እሱ አሁን እዚህ ቦታ አልገኝም ነበር በማለት ገልጸዋል።

ከጋርዲዮላ ጋር ዛሬ ጠዋት በስልክ አውርተው እንደነበር ያረጋገጡት አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ “ እሱን አመስጋኝ ነኝ “ ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ምክትል አሰልጣኙ ያደረገኝ እሱ ነው ፣ እሱ አርኣያዬ ነው ፣ ዛሬ የተፈጠረው ነገር ሁሉ የተፈጠረው በእሱ ምክንያት ነው።" አርቴታ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ሳንቲያጎ በርናቦ የተለየ አይደለም “ ቶማስ ፓርቴ

" ማድረግ ያለብንን እናውቃለን "

የመድፈኞቹ አማካይ ቶማስ ፓርቴ ሳንቲያጎ በርናቦ እንግሊዝ ውስጥ ካሉ ስታዲየሞች የተለየ ነው ብሎ እንደማያስብ ገልጿል።

እንግሊዝ ውስጥ ትልቅ ጫና ባላቸው ስታዲየሞች ተጫውተው እንደሚያውቁ የገለፀው ፓርቴ “ በርናቦ ያለው ድባብ እንግሊዝ ውስጥ ካለው ጋር ብዙ የተለየ ነው ብዬ አላስብም “ ሲል ተደምጧል።

በጨዋታው ላይ እምነት ሊኖረን ይገባል ምርጥ እግርኳሳችንን መጫወት አለብን ሲል ቶማስ ፓርቴ ጨምሮ ተናግሯል።

“ ምን ማድረግ እንዳለብን ሁላችንም እናውቃለን የአሸናፊነት መንፈስ ይዘን መሄድ አለብን ፤ እያንዳንዱን ጨዋታ ማሸነፍ እንፈልጋለን ድክመታችንን በማወቅ እነሱን ማጥቃት አለብን።“ ቶማስ ፓርቴ

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
“ ያለኝ ተሰጥኦ የፈጣሪ ስጦታ ነው “ ሊዮኔል ሜሲ

አርጀንቲናዊው የስምንት ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊ ተጨዋች ሊዮኔል ሜሲ ያለው የእግርኳስ ተሰጥኦ የፈጣሪ ስጦታ ነው ብሎ እንደሚያምን ገልጿል።

ያለህ ተሰጥኦ አብሮህ የተወለደ ነው ወይስ በጥረት የተገነባ ? ተብሎ የተጠየቀው ሊዮኔል ሜሲ “ እኔ የተወለድኩት በዚህ መንገድ ነው “ ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

“ በእርግጥ ራሴን ለማሻሻል እና በደንብ ለመጎልበት ጠንክሬ እሰራ ነበር “ የሚለው ሊዮኔል ሜሲ “ ነገርግን ከልጅነቴ ጀምሮ የተቀየረ ነገር የለም እንደዚሁ ስጫወት ነበር “ ብሏል።

ሜሲ አክሎም " ተሰጥኦዬ የበለጠ ለመጠቀም የሞከርኩት ከእግዚአብሔር የተሰጠኝ ስጦታ ነው “ ሲል ተሰጥኦ ያለጥረት ብቻው በቂ አይደለም ሲል አስረድቷል።

“ ፈጣሪ ሁሉንም ነገር ስለሰጠኝ አመሰግነዋለሁ ፤ ሁሉንም ነገር አሸንፌያለሁ ተጨማሪ መጠየቅ አልችልም።“ ሊዮኔል ሜሲ

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
አርሰናል ማድሪድን ከሻምፒየንስ ሊግ አሰናበተ !

የለንደኑ ክለብ አርሰናል ሴቶች ቡድን ከሪያል ማድሪድ አቻው ጋር ያደረገውን የሴቶች የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ 3ለ0 ማሸነፍ ችለዋል።

በመጀመሪያው ጨዋታ 2ለ0 የተሸነፈው የአርሰናል ሴቶች ቡድን ሪያል ማድሪድን በድምር ውጤት 3ለ2 በመርታት ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅሏል።

አርሰናል በሴቶች አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ ታሪክ 2ለ0 ተሸንፎ ውጤቱን በመቀልበስ ግማሽ ፍፃሜ የተቀላቀለ የመጀመሪያው ክለብ ሆኗል።

የሪያል ማድሪድ ሴቶች ቡድን ከአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ውጪ ሆነዋል።

በሌላ የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ሊዮን ባየር ሙኒክን 4ለ1 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል።

የአርሰናል ሴቶች ቡድን በግማሽ ፍፃሜው ከኦሎምፒክ ሊዮን ሴቶች ቡድን ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ አርሰናል የሻምፒየንስ ሊግ ልምድ የለውም “ ቶኒ ክሩስ

የቀድሞ የሪያል ማድሪድ ተጨዋች ቶኒ ክሩስ ሪያል ማድሪድ አርሰናልን በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ማስደንገጥ አለበት በማለት ተናግሯል።

“ ሪያል ማድሪድ የሚጫወተው በሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ልምድ ከሌለው አርሰናል ጋር ነው “ ሲል ቶኒ ክሩስ አስተያየቱን ሰጥቷል።

አክሎም “ የመጀመሪያ አስራ አምስት ደቂቃዎች ጨዋታውን ይወስናሉ “ ሲል ቶኒ ክሩስ ማድሪድ ተጭኖ እንዲጫወት መክሯል።

“ ማድሪድ በመጀመሪያ ደቂቃዎች ጎል ማስቆጠር አለበት ፤ አርሰናል ጨዋታው ገና አላለቀም ብለው እንዲደነግጡ ሊደረጉ ይገባል።“ ቶኒ ክሩስ

“ አርሰናል ከዚህ በፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ተጫውቶ ጫናውን አይቶት አያውቅም “ ሲል ቶኒ ክሩስ ጨምሮ ተናግሯል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ማድሪድ የምንሄደው ስራውን ለመጨረስ ነው “ ኦዴጋርድ

የአርሰናሉ አምበል ማርቲን ኦዴጋርድ ቡድናቸው ወደ ሳንቲያጎ በርናቦ የሚያመራው የጀመረውን ስራ ለመጨረስ መሆኑን ገልጿል።

“ ወደ ሳንቲያጎ በርናቦ ሄደን በሜዳችን የጀመርነውን ሥራ እንጨርሰዋለን “ ሲል ማርቲን ኦዴጋርድ አስተያየቱን ሰጥቷል።ል።

ቡድኑ ካለፈው አመት መሻሻሉን በማድሪድ ጨዋታ እንዳሳየ ያስረዳው ኦዴጋርድ “ የሻምፒየንስ ሊጉን ንጉሥ በማሸነፍ አንድ እርምጃ ከፍ ብለናል በዚህ መኩራት አለብን “ ብሏል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
ምላሻችን በሜዳ ላይ ነበር “ ዴክላን ራይስ

የመድፈኞቹ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ዴክላን ራይስ ከድሉ በኃላ በሰጠው አስተያየት ምላሽ የሰጠነው በሜዳ ላይ ነው ሲል ተደምጧል።

“ ታሪካዊ ምሽት “ሲል የበርናቦውን ድል የገለፀው ራይስ “ ውጤቱን ስለ መቀየር ብዙ ሲያወሩ ነበር ፣ የኛ ምላሽ ግን በሜዳ ላይ ነበር “ በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
" ቡድኑ መሻሻሉን አይቻለሁ " ሩበን አሞሪም

የቀያይ ሴጣኖቹ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪሞ ቡድኑ እየተሻሻለ መሆኑን በዛሬው ጨዋታ መመልከታቸውን አስረድተዋል።

" በጨዋታው ውስጥ የቡድኑን እድገት አይቻለሁ " ያሉት አሰልጣኙ ራሴን አልዋሽም ሰው የፈለገውን ማለት ይችላል የሆነ ጥሩ ነገር አይቻለሁ ብለዋል።

አክለውም " ነገርግን ጨዋታዎችን ማሸነፍ አለብን “ ሲል ቡድናቸውን አሳስበዋል።

" አንዳንድ ጊዜ ስትሸነፍ ተጋጣሚህ የተሻለ ነበር ብለህ ታስባለህ ለመቀበል ቀላል ነው ዛሬ ግን እኛ የተሻልን ነበርን " ሩበን አሞሪም

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
25.03.202500:02
ጨዋታው ገና አላለቀም “ ሚኬል አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ካስመዘገበው ወሳኝ ድል በኃላ ቀሪ 90 ደቂቃ እንዳለ አሳስበዋል።

“ የሰራነው ግማሽ ስራ ነው “ ያሉት አሰልጣኙ “ ሪያል ማድሪድ የዚህ ውድድር ምርጦች ናቸው ፣ ምንም ያለቀ ነገር የለም “ ብለዋል።

ስለ መልሱ ጨዋታ በሰጡት ምላሽ “ ለበርናቦ ጨዋታ ተዘጋጅተን ለማሸነፍ እንጫወታለን ፣ ኤምሬትስ ላይ ያደርገነውን በመልሱ ለማድረግ አቅሙ አለን “ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የፊልም ተቋም ከፈተ !

ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከብሪታንያዊው የፊልም ባለሙያ ማቲው ቮን ጋር በመሆን የፊልም ስቱዲዮ መክፈቱን ይፋ አድርጓል።

አሁን ላይ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከአጋሩ ጋር ሁለት የ " Action " ፊልም ሰርቶ ማጠናቀቁ ሲገለፅ ፊልሞቹ በቅርቡ ለእይታ አንደሚቀርቡ ተገልጿል።

“ ይህ አዲስ የስራ ዘርፍ ለእኔ አስደሳች የህይወት ምዕራፍ ይሆናል “ ሲል ክርስቲያኖ ርናልዶ አስተያየቱን ሰጥቷል።

ፊልሞችን በመስራት የሚታወቀው ማቲው ቮን በበኩሉ “ ሮናልዶ ሜዳ ላይ እኔ መፃፍ የማልችላቸውን በርካታ ታሪኮችን ፅፏል “ ብሏል።

አክሎም “ አሁን ከእሱ ጋር ምርጥ የፊልም ታሪኮችን ለመፃፍ ጓጉቻለሁ ሮናልዶ እውነተኛ የህይወት ጀግና ነው “ ሲል ገልጿል።

@tikvahethsport        @kidusyoftahe
" ትምህርት ሰጥተናቸዋል " አልቫሬዝ

የአርጀንቲና የፊት መስመር ተጨዋች ጁሊያን አልቫሬዝ ቡድናቸው በሌሊቱ ጨዋታ ለተጋጣሚው ትምህርት መስጠቱን ገልጿል።

በጨዋታው የመጀመሪያውን ግብ ለአርጀንቲና ያስቆጠረው አልቫሬዝ " በአክብሮት ጥሩ ተጫውተን የእግርኳስ ትምህርት ሰጥተናቸዋል።“ ሲል ተደምጧል።

አልቫሬዝ አክሎም “ ሊዮኔል ሜሲ ቢኖር ደግሞ ሁለት ወይም ሶስት ጎል ይጨመር ነበር “ ሲል ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ሲቲን ማሸነፍ አለብን " ዳሎት

የማንችስተር ዩናይትዱ የመስመር ተጨዋች ዲያጎ ዳሎት ቡድናቸው እየተሻሻለ መሆኑን ከምሽቱ ጨዋታ በኋላ ተናግሯል።

" እየተሻሻልን እንደሆነ ይሰማኛል በጨዋታው እኛ ነበርን የተሻልነው ጨዋታውን ተቆጣጥረነዋል “ ሲል ዳሎት አስተያየቱን ሰጥቷል።

አክሎም " የዛሬው ጨዋታ ጥሩ ነገር ለቀጣይ ጨዋታዎች መነሳሻ ይሆነናል “ ሲል ተደምጧል።

ስለ ቀጣዩ የማንችስተር ሲቲ ጨዋታ ያነሳው ዳሎት “ ደርቢ ነው ማሸነፍ አለብን ድባቡ የተለየ ይሆናል “ ሲል ገልጿል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
ማግሀሌስ ከውድድር አመቱ ውጪ ሆነ !

ብራዚላዊው የመድፈኞቹ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጋብሬል ማግሀሌስ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከውድድር አመቱ ውጪ መሆኑ ተገልጿል።

ተጨዋቹ ከቀናት በፊት አርሰናል ፉልሀምን ባሸነፈበት ጨዋታ ጉዳት እንዳጋጠመው አይዘነጋም።

አሁን ላይ ጋብሬል ማግሀሌስ የቀዶ ጥገና ህክምና እንደሚያስፈልገው ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ አርሰናል ከሪያል ማድሪድ ጋር በሚያደርገው የሻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ የጋብሬል ማግሀሌስን ግልጋሎት የማያገኝ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Log in to unlock more functionality.