
ሚኪያስ ፈይሣ
ግጥም
ወግ
ሀሳቦች
ልቦለዶች
🤝 @mika145
ወግ
ሀሳቦች
ልቦለዶች
🤝 @mika145
关联群组
"ሚኪያስ ፈይሣ" 群组最新帖子
21.04.202518:49
ሙቅ ወንበር የተውንላቸው
ውለው አድረው መቆሚያ ነሱን
አክብረን ዝቅ ያልንላቸው
በሰው ፊት አስተናነሱን ።
በፍቅር ያጎረስናቸው
በእጅ አዙር አስቦጠቦጡን
ጠበል ውስጥ አጥበን አንፅተን
እቶን ላይ አገላበጡን።
ስንለካ እየቀነሱ
ስናቆም እያፈረሱ
ተምረው ላይለወጡ
ተዘክረው ላይለወጡ
ጭላንጭል ትዕግስታችንን
እንደ ሰም እያቀለጡ፦
ሲዘልፉን እጅ እየነሳን
ሲጥሉን እየተነሳን
ለጥፊ ፊት እየቀየርን
ብንመስል የአርብ ለት በጉን
አሻጥር የማይገባቸው
ያልነቃ ፋራ አደረጉን።
ድሮውም ወጉ እንዲያው ነው
ድሮውም ሀቁ እንዲያው ነው
እኛ ነን ቅሪል ቡቱቶ፤
ለጋ አይብ አይጠበቅም
ለህፃን ልጅ ወተት ተሰጥቶ።
@mikiyas_feyisa
ውለው አድረው መቆሚያ ነሱን
አክብረን ዝቅ ያልንላቸው
በሰው ፊት አስተናነሱን ።
በፍቅር ያጎረስናቸው
በእጅ አዙር አስቦጠቦጡን
ጠበል ውስጥ አጥበን አንፅተን
እቶን ላይ አገላበጡን።
ስንለካ እየቀነሱ
ስናቆም እያፈረሱ
ተምረው ላይለወጡ
ተዘክረው ላይለወጡ
ጭላንጭል ትዕግስታችንን
እንደ ሰም እያቀለጡ፦
ሲዘልፉን እጅ እየነሳን
ሲጥሉን እየተነሳን
ለጥፊ ፊት እየቀየርን
ብንመስል የአርብ ለት በጉን
አሻጥር የማይገባቸው
ያልነቃ ፋራ አደረጉን።
ድሮውም ወጉ እንዲያው ነው
ድሮውም ሀቁ እንዲያው ነው
እኛ ነን ቅሪል ቡቱቶ፤
ለጋ አይብ አይጠበቅም
ለህፃን ልጅ ወተት ተሰጥቶ።
@mikiyas_feyisa


19.04.202505:20
16.04.202519:19
እንደምነህ አንተ ሰው
እንደምነህ ቀያፋ
የወነጀልከው ንፁህ ሰው
መስቀሉን ይዞ ተደፋ
እንደምነህ አዛዡ
እንደምነህ ጲላጦስ
አስቀየምካቸው ህዝብህን
ፊትህ ባቆምከው
አምላክ ጦስ?
ምንተሰምቶህ ይሁን ሲንፏቀቅ
ምን ተሰማቶህ ይሁን ሲያቃስት
እጅህን ታጥበህ ከዳኸው
ወይስ አነሳኸው በስስት
ሸንጎ ላይ ስታቆመውስ
የፍትህ ሻማ ሲለኮስ
ከፊትህ ፃዲቅ የሆነው
በርባን ነው ወይስ ክርስቶስ?
እንደምነህ አንተ ሰው
እንደምንነህ በርባን
ክርስቶስን ገለን
አንተን ይዘን ገባን
ያስቃል አይደለ
የሞኝ ሰው ጩኸት
ያስቃል አይደለ
የቂል ፍትህ ምርጫ
ከወንበዴ ይብሳል
የንፁህ መቀጫ
በል አሁን ቶሎ ሂድ
የሟች ቤተሰቦች
ያንተን መውጣት ሰምተው
ሳያፈላልጉ
እሺ ወዳንተ ልምጣ
እንዴት ነህ መፃጉ?
አልጋህን የት ጣልከው
ጌታህን ምን አልከው
ባይገባው እንኳን
ያጨደውን መብላት
የዘራውን መቃም፥
እንደው ላነሳህ ሰው
ግርፋቱ አይበቃም?
የታመመ አይደል ወይ
የተጎዳ አይደል ወይ
በግፍ የሚበቀል?፥
ለምን ያዳነህ ሰው
እርቃኑን ሚሰቀል?
ተው እዘን መፃጉ
ተው እዘን ጲላጦስ
ተው እዘን ግን በርባን
ያልበደለ ሰቅለን
ወንበዴ ታቅፈን
መቅደስ እየገባን፦
ቀና አትበል ቀያፋ
ለአይሁድ አታዳርስ
ሀሰት የድል ቅጂ ፤
"ገድለኸው አይደለም
ሞቶልህ ነው እንጂ!"።
@mikiyas_feyisa
እንደምነህ ቀያፋ
የወነጀልከው ንፁህ ሰው
መስቀሉን ይዞ ተደፋ
እንደምነህ አዛዡ
እንደምነህ ጲላጦስ
አስቀየምካቸው ህዝብህን
ፊትህ ባቆምከው
አምላክ ጦስ?
ምንተሰምቶህ ይሁን ሲንፏቀቅ
ምን ተሰማቶህ ይሁን ሲያቃስት
እጅህን ታጥበህ ከዳኸው
ወይስ አነሳኸው በስስት
ሸንጎ ላይ ስታቆመውስ
የፍትህ ሻማ ሲለኮስ
ከፊትህ ፃዲቅ የሆነው
በርባን ነው ወይስ ክርስቶስ?
እንደምነህ አንተ ሰው
እንደምንነህ በርባን
ክርስቶስን ገለን
አንተን ይዘን ገባን
ያስቃል አይደለ
የሞኝ ሰው ጩኸት
ያስቃል አይደለ
የቂል ፍትህ ምርጫ
ከወንበዴ ይብሳል
የንፁህ መቀጫ
በል አሁን ቶሎ ሂድ
የሟች ቤተሰቦች
ያንተን መውጣት ሰምተው
ሳያፈላልጉ
እሺ ወዳንተ ልምጣ
እንዴት ነህ መፃጉ?
አልጋህን የት ጣልከው
ጌታህን ምን አልከው
ባይገባው እንኳን
ያጨደውን መብላት
የዘራውን መቃም፥
እንደው ላነሳህ ሰው
ግርፋቱ አይበቃም?
የታመመ አይደል ወይ
የተጎዳ አይደል ወይ
በግፍ የሚበቀል?፥
ለምን ያዳነህ ሰው
እርቃኑን ሚሰቀል?
ተው እዘን መፃጉ
ተው እዘን ጲላጦስ
ተው እዘን ግን በርባን
ያልበደለ ሰቅለን
ወንበዴ ታቅፈን
መቅደስ እየገባን፦
ቀና አትበል ቀያፋ
ለአይሁድ አታዳርስ
ሀሰት የድል ቅጂ ፤
"ገድለኸው አይደለም
ሞቶልህ ነው እንጂ!"።
@mikiyas_feyisa


16.04.202508:57
14.04.202517:19
ሰው ፍቅርን በክፉ ያነሳል
ሰው ፍቅርን በግፉ ያነሳል
ቆይ ግን ሰው ፡ ወዶ ይከሳል?
ተጓዳኝ ድውይ ተጣብቆት
ውጭ ውስጡን ካላነደደ ፥
ሰው እንዴት ወዙ ቡን ይላል
ሌላ ሰው ፡ ስለወደደ?
እንጃ ግን የኔ ረሃ ነው
በምቾት ያደነዝዛል፥
ቀን በቀን ፍቅሬ ሲጨምር
እንደ ስልብ ፊቴም ይወዛል።
እንጃልኝ ጥጋብ ነው መሰል
ሚያፋፋኝ የልቤ ላይ ጥም፥
ሰው ሳልወድ የነበረኝ ሳቅ
ሳፈቅርም አይለወጥም!።
@mikiyas_feyisa
ሰው ፍቅርን በግፉ ያነሳል
ቆይ ግን ሰው ፡ ወዶ ይከሳል?
ተጓዳኝ ድውይ ተጣብቆት
ውጭ ውስጡን ካላነደደ ፥
ሰው እንዴት ወዙ ቡን ይላል
ሌላ ሰው ፡ ስለወደደ?
እንጃ ግን የኔ ረሃ ነው
በምቾት ያደነዝዛል፥
ቀን በቀን ፍቅሬ ሲጨምር
እንደ ስልብ ፊቴም ይወዛል።
እንጃልኝ ጥጋብ ነው መሰል
ሚያፋፋኝ የልቤ ላይ ጥም፥
ሰው ሳልወድ የነበረኝ ሳቅ
ሳፈቅርም አይለወጥም!።
@mikiyas_feyisa
12.04.202518:33
መሲሁን እየጠበቀ
የሰው ዘር በሞት ሲያዘግም
ተናንሶ እታች አገኙት
ንጉሱን ታቅፎ በግርግም፥
ገረማቸው...
ለምነው የዳዊት አምላክ
መንግስቱን ክብሩን የካደ?
እንዴት ነው ሰገነት ትቶ
በበረት የተወለደ?
እያሉ ተሳለቁበት..
እርግጥ ነው እንደጠበቁት
ሰራዊት አልነበረውም
ከቀራጭ አሳ አጥማጅ ውጪ
ወታደር አልቀረበውም
እርግጥ ነው እንደገመቱት
አልያዘም ጦር እና ጋሻ
የእርሱን ህዝብ የሚያድንበት
የጠላት ጦርን ድል መንሻ፤
አልያዘም እፍኝ ውሀ እንኳን
ለጠማው ቀድቶ ሚያጠጣው
እስራኤል ግርማ ሲጠብቅ
በአህያ ነበር የመጣው።
@mikiyas_feyisa
የሰው ዘር በሞት ሲያዘግም
ተናንሶ እታች አገኙት
ንጉሱን ታቅፎ በግርግም፥
ገረማቸው...
ለምነው የዳዊት አምላክ
መንግስቱን ክብሩን የካደ?
እንዴት ነው ሰገነት ትቶ
በበረት የተወለደ?
እያሉ ተሳለቁበት..
እርግጥ ነው እንደጠበቁት
ሰራዊት አልነበረውም
ከቀራጭ አሳ አጥማጅ ውጪ
ወታደር አልቀረበውም
እርግጥ ነው እንደገመቱት
አልያዘም ጦር እና ጋሻ
የእርሱን ህዝብ የሚያድንበት
የጠላት ጦርን ድል መንሻ፤
አልያዘም እፍኝ ውሀ እንኳን
ለጠማው ቀድቶ ሚያጠጣው
እስራኤል ግርማ ሲጠብቅ
በአህያ ነበር የመጣው።
@mikiyas_feyisa
07.04.202512:51
የኔ ልዕልት ፡ ስሚኝ አሁን
አይጠፋሽም
ውስጥሽ ያውቃል፤
ችግር አቅፈን ምናድርበት
የስካሁኑ ጊዜ ይበቃል።
ምናድግበት ሚስጥር ታየኝ
ሰውነቴን ሀሴት ዋጠው፤
ግድ የለሽም ትንሽ ቆርሰን
ፍቅራችንን እንሽጠው!።
የሚገዛ ሀገር ሞልቷል..
ነጠላ ነው ሚገጥመኝ ሰው
ብቸኛ ነው የማየውም፤
የከተማው ባለትዳር
ገንዘብ እንጂ ፍቅር የለውም።
ያሳዝናል ቀዬው ብታይ
እስቲ ይቅመሰው የኛን መገን፤
ፍቅር እንደሆን ሞልቶን ተርፏል
ትንሽ ካሽ ነው ሚያስፈልገን።
እንዳትሰጊ ፡ አንዲት እንኳን
ይሄ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
አልኳትና በረብጣ ብር
ከኛ ሰፍረን ፍቅር ሸጥን!።
ከዛን..
ተመቻቸን
ህይወት ደላን
ገርበብ አለ የአይናችን ዘብ፤
"ያለፈው ዓለም አይገባው
ፍቅር ኖሮት ያጣ ገንዘብ።"
ብለን ሳቅን
ተቃቀፍን
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ዓለም ለኛ ገነት ሆነች
ምድር ሆነች የኛ ተድላ።
የመንደሩን አይን ገዛን
ታላቅ ታናሽ አከበረን ፤
ሁሉ ሞልቶን ተደላድሎ
ትንሽ ብቻ ፡ ገንዘብ ቀረን።
ሰልችቶናል ስናገኘው
አሸዋ ላይ መልክን መሳል፤
ለታደልነው ብዙ ምኞት
የነበረን ገንዘብ ያንሳል።
ሰማዩ ላይ ስናማትር፡
መርከቡ ላይ ስናማትር፡
ስናይ ውለን የባህሩን
ግራ የገባው ፡ ውዝዋዜ ፤
ቁጭ ስንል ሀሳብ መጣ
አለን ለካ ፡ ብዙ ጊዜ!።
ተነጋገርን
ተማከርን
ካረጀ ሀብታም አንጋጠጥን፤
ሻንጣ ሙሉ ገንዘብ ወስደን
ሽርፍራፊ ጊዜ ሸጥን!።
አቤት ሀሴት
አቤት ፌሽታ
ህዝቡ ባዶ ቅኔ ያምጣል፤
ገንዘብ ደስታ ባይገዛ እንኳን
እልፍ ደስታ ይዞ ይመጣል።
የሚያቆመን ፍጥረት ጠፋ
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ግን አሁንም አልተነሳም
የህዝባችን አይነ-ጥላ!።
ምናገባን እኛ ኖርን
እኛ ኖርን ምናገባን፤
ግን አንድ ሌት በህልማችን
ስልል ያለ ሀሳብ ገባን፦
"ፍቅራችንን ከላይ አይቶ
ይህን ፀጋ እርሱ ሰጠን፤
አንድ ወንበዴ ገፍቶ ቢዘርፍ
ምንድነው ግን የሚውጠን?"
ብለን አሰብን
ተብከነከን
ያ ደላላ ፡ መጣ ዳግም፤
ያገናኘን ፅኑ መድህን
ከፍቅር ውጪ አይፈልግም።
ተመካከርን .... በቃ ይሁን!
ይህ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
ብለን ትንሽ ፡ የማትጎዳ
በድጋሚ ፡ ፍቅር ሸጥን!።
እርሱ ይክበር
ሰላም ተኛን
ህልማችንን እርሱ ረዳ፤
የሚጣፍጥ ለሊት አድረን
ደግሞ ነቃን በማለዳ።
ግና...
የትላንቱ ህመም ቢሻር
ምቾት ዛሬን ቢንሰራፋም፦
እየሳቅን ውለን አድረን
የሚያውከን ነገ አይጠፋም።
ትንሽ ብለን ፦ ስንቀንስ
ጥቂት ብለን ስናወጣ፥
እለት በለት እ.የ.ባ.ሰ
ያልታሰበ ጉድ ሲመጣ፤
ትንሽ ፍቅር ፣ ትንሽ ጊዜ
ትንሽ .. ትንሽ "ትልቅ" ሆኖ ፤
ሳናስተውል ያለን ፍቅር
በየዳናው ተበትኖ ፤
ዝም ማለት ልማድ ሆነን
መቀላለድ ወዙ ጠፋን
ደስታችንን ለማስቀጠል
አንጀት ቋጥረን ብዙ ለፋን።
ግን አልሆነም ውጥናችን
ቅዠት ገዛን ተገላብጦ፤
ህይወታችን መንቀፍ ሆነ
ያንዱን ድክመት ብቻ መርጦ።
"አንተ እኮ ነህ እንዲህ ያልከኝ"
"አንቺ እኮ ነሽ እንዲ ያረግሽው"፥
"ከዚህ ኋላ ይሄ በቃኝ"
"የስካሁኑን ፍቅር እርሺው!"።
ተቃቃርን እንደ ሩቅ ሰው
ባላንጣ ሆንን በኛው ሜዳ
እንስፍስፉን አንጀት ጥለን
በአዳር ሆንን እንደ ባዳ።
አንገርምም?
ወዳጅ ዘመድ በርቱ ሲለን
ሲቀናብን የውጪ ሰው፤
ያቀፍነውን ጥሬ ገንዘብ
አይነተን ቆጥረን ሳንጨርሰው፥
ከጓዳችን ተትረፍርፎ
ንዋይ ፣ ዝና ፣ ሀብት ፣ ስልጣን፤
ከባድ ቀንን ምናልፍበት
ቅንጥብጣቢ ፍቅር አጣን!።
@mikiyas_feyisa
አይጠፋሽም
ውስጥሽ ያውቃል፤
ችግር አቅፈን ምናድርበት
የስካሁኑ ጊዜ ይበቃል።
ምናድግበት ሚስጥር ታየኝ
ሰውነቴን ሀሴት ዋጠው፤
ግድ የለሽም ትንሽ ቆርሰን
ፍቅራችንን እንሽጠው!።
የሚገዛ ሀገር ሞልቷል..
ነጠላ ነው ሚገጥመኝ ሰው
ብቸኛ ነው የማየውም፤
የከተማው ባለትዳር
ገንዘብ እንጂ ፍቅር የለውም።
ያሳዝናል ቀዬው ብታይ
እስቲ ይቅመሰው የኛን መገን፤
ፍቅር እንደሆን ሞልቶን ተርፏል
ትንሽ ካሽ ነው ሚያስፈልገን።
እንዳትሰጊ ፡ አንዲት እንኳን
ይሄ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
አልኳትና በረብጣ ብር
ከኛ ሰፍረን ፍቅር ሸጥን!።
ከዛን..
ተመቻቸን
ህይወት ደላን
ገርበብ አለ የአይናችን ዘብ፤
"ያለፈው ዓለም አይገባው
ፍቅር ኖሮት ያጣ ገንዘብ።"
ብለን ሳቅን
ተቃቀፍን
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ዓለም ለኛ ገነት ሆነች
ምድር ሆነች የኛ ተድላ።
የመንደሩን አይን ገዛን
ታላቅ ታናሽ አከበረን ፤
ሁሉ ሞልቶን ተደላድሎ
ትንሽ ብቻ ፡ ገንዘብ ቀረን።
ሰልችቶናል ስናገኘው
አሸዋ ላይ መልክን መሳል፤
ለታደልነው ብዙ ምኞት
የነበረን ገንዘብ ያንሳል።
ሰማዩ ላይ ስናማትር፡
መርከቡ ላይ ስናማትር፡
ስናይ ውለን የባህሩን
ግራ የገባው ፡ ውዝዋዜ ፤
ቁጭ ስንል ሀሳብ መጣ
አለን ለካ ፡ ብዙ ጊዜ!።
ተነጋገርን
ተማከርን
ካረጀ ሀብታም አንጋጠጥን፤
ሻንጣ ሙሉ ገንዘብ ወስደን
ሽርፍራፊ ጊዜ ሸጥን!።
አቤት ሀሴት
አቤት ፌሽታ
ህዝቡ ባዶ ቅኔ ያምጣል፤
ገንዘብ ደስታ ባይገዛ እንኳን
እልፍ ደስታ ይዞ ይመጣል።
የሚያቆመን ፍጥረት ጠፋ
ፍስሃችን ምድርን ሞላ፥
ግን አሁንም አልተነሳም
የህዝባችን አይነ-ጥላ!።
ምናገባን እኛ ኖርን
እኛ ኖርን ምናገባን፤
ግን አንድ ሌት በህልማችን
ስልል ያለ ሀሳብ ገባን፦
"ፍቅራችንን ከላይ አይቶ
ይህን ፀጋ እርሱ ሰጠን፤
አንድ ወንበዴ ገፍቶ ቢዘርፍ
ምንድነው ግን የሚውጠን?"
ብለን አሰብን
ተብከነከን
ያ ደላላ ፡ መጣ ዳግም፤
ያገናኘን ፅኑ መድህን
ከፍቅር ውጪ አይፈልግም።
ተመካከርን .... በቃ ይሁን!
ይህ ይሆናል የእግዜር ውጥን፤
ብለን ትንሽ ፡ የማትጎዳ
በድጋሚ ፡ ፍቅር ሸጥን!።
እርሱ ይክበር
ሰላም ተኛን
ህልማችንን እርሱ ረዳ፤
የሚጣፍጥ ለሊት አድረን
ደግሞ ነቃን በማለዳ።
ግና...
የትላንቱ ህመም ቢሻር
ምቾት ዛሬን ቢንሰራፋም፦
እየሳቅን ውለን አድረን
የሚያውከን ነገ አይጠፋም።
ትንሽ ብለን ፦ ስንቀንስ
ጥቂት ብለን ስናወጣ፥
እለት በለት እ.የ.ባ.ሰ
ያልታሰበ ጉድ ሲመጣ፤
ትንሽ ፍቅር ፣ ትንሽ ጊዜ
ትንሽ .. ትንሽ "ትልቅ" ሆኖ ፤
ሳናስተውል ያለን ፍቅር
በየዳናው ተበትኖ ፤
ዝም ማለት ልማድ ሆነን
መቀላለድ ወዙ ጠፋን
ደስታችንን ለማስቀጠል
አንጀት ቋጥረን ብዙ ለፋን።
ግን አልሆነም ውጥናችን
ቅዠት ገዛን ተገላብጦ፤
ህይወታችን መንቀፍ ሆነ
ያንዱን ድክመት ብቻ መርጦ።
"አንተ እኮ ነህ እንዲህ ያልከኝ"
"አንቺ እኮ ነሽ እንዲ ያረግሽው"፥
"ከዚህ ኋላ ይሄ በቃኝ"
"የስካሁኑን ፍቅር እርሺው!"።
ተቃቃርን እንደ ሩቅ ሰው
ባላንጣ ሆንን በኛው ሜዳ
እንስፍስፉን አንጀት ጥለን
በአዳር ሆንን እንደ ባዳ።
አንገርምም?
ወዳጅ ዘመድ በርቱ ሲለን
ሲቀናብን የውጪ ሰው፤
ያቀፍነውን ጥሬ ገንዘብ
አይነተን ቆጥረን ሳንጨርሰው፥
ከጓዳችን ተትረፍርፎ
ንዋይ ፣ ዝና ፣ ሀብት ፣ ስልጣን፤
ከባድ ቀንን ምናልፍበት
ቅንጥብጣቢ ፍቅር አጣን!።
@mikiyas_feyisa
06.04.202503:04
እንዳትረሺኝ!
'ከመሬት ሰው ቢትረፈረፍ
ደም ቢለብስም ሳር ቅጠሉ፥
ካለፈው ጣር ለማገገም
መርሳት ቢሆን ስኬት ድሉ
ማርትሬዛ ሀብል ሆኜ
ከአንገትሽ ላይ ባታስሪኝም
ጡትሽ መሃል ሸሽገሺኝ፤
እንዳትረሺኝ
ቢቋደሱት የአለምን ጣ'ም
ቢነቃቀል እሾህ አጋም
ጭፍግግ ያለው ሌሊት ገፎ
ተስፋ ያለው ጧት ቢነጋም፥
እኩለ ሌት ባደርንበት
ግርግዳ ላይ ለጥፈሺኝ
እንዳትረሺኝ!
እንዳረጀ ሸማ ፈትል
ቢደበዝዝ ትዝታዬ
ፀአዳ አለም ተሸፍኖኝ
እልም ቢሆን ገፅታዬ
ከልብሽ ላይ ባታንዣብብ
የመንፈሴ ልዝብ ልኳ
ሁሉም እዳው ገፈት ቢሆን
ጥጥ ሰማዩ ቢጠቁር እንኳ፤
ያደፈውን ሰማይ ቀደሽ
ከርሰ ምድር ሰነጣጥቀሽ
በሽንቁሩ እያየሺኝ
እንዳትረሺኝ!
ከሰው መንጋ ባይነጥለኝ
አመል ማይለቅ ያይንሽ ቀሽም
እንደ ራቁት የሰው ጠረን
ያሳለፍነው ቢጠፋሽም፥
እንዳልነበር
እንዳልኖረ ፦
እርሺኝና ፡ አለቅሽም!
@mikiyas_feyisa
'ከመሬት ሰው ቢትረፈረፍ
ደም ቢለብስም ሳር ቅጠሉ፥
ካለፈው ጣር ለማገገም
መርሳት ቢሆን ስኬት ድሉ
ማርትሬዛ ሀብል ሆኜ
ከአንገትሽ ላይ ባታስሪኝም
ጡትሽ መሃል ሸሽገሺኝ፤
እንዳትረሺኝ
ቢቋደሱት የአለምን ጣ'ም
ቢነቃቀል እሾህ አጋም
ጭፍግግ ያለው ሌሊት ገፎ
ተስፋ ያለው ጧት ቢነጋም፥
እኩለ ሌት ባደርንበት
ግርግዳ ላይ ለጥፈሺኝ
እንዳትረሺኝ!
እንዳረጀ ሸማ ፈትል
ቢደበዝዝ ትዝታዬ
ፀአዳ አለም ተሸፍኖኝ
እልም ቢሆን ገፅታዬ
ከልብሽ ላይ ባታንዣብብ
የመንፈሴ ልዝብ ልኳ
ሁሉም እዳው ገፈት ቢሆን
ጥጥ ሰማዩ ቢጠቁር እንኳ፤
ያደፈውን ሰማይ ቀደሽ
ከርሰ ምድር ሰነጣጥቀሽ
በሽንቁሩ እያየሺኝ
እንዳትረሺኝ!
ከሰው መንጋ ባይነጥለኝ
አመል ማይለቅ ያይንሽ ቀሽም
እንደ ራቁት የሰው ጠረን
ያሳለፍነው ቢጠፋሽም፥
እንዳልነበር
እንዳልኖረ ፦
እርሺኝና ፡ አለቅሽም!
@mikiyas_feyisa
04.04.202519:15
፨
ልሻር እንጂ ላንዴ
ከሚለበልበኝ ፡ ስውር የጣር ስቃይ፥
ይክሰምልኝ እንጂ
ስራስሩ ያነቀኝ
የመከዳት ብቃይ ፤
ብሞትም ጨክኜ
በምሬት ተግቼው ሀቁን እንደ ኮሶ፤
አንደው ልዳን እንጂ
እህህ ያስባለኝን
ህመሜን ጨርሶ ፦
..
ብቻ ልትረፍ እንጂ
ቤትም ተፍጨርጭሬ
ባለኝ ቁንፅል አቅም ፤
"ሴት" የሚባል ፍጡር
በጥርሴም ፡ አለቅም!።
@mikiyas_feyisa
ልሻር እንጂ ላንዴ
ከሚለበልበኝ ፡ ስውር የጣር ስቃይ፥
ይክሰምልኝ እንጂ
ስራስሩ ያነቀኝ
የመከዳት ብቃይ ፤
ብሞትም ጨክኜ
በምሬት ተግቼው ሀቁን እንደ ኮሶ፤
አንደው ልዳን እንጂ
እህህ ያስባለኝን
ህመሜን ጨርሶ ፦
..
ብቻ ልትረፍ እንጂ
ቤትም ተፍጨርጭሬ
ባለኝ ቁንፅል አቅም ፤
"ሴት" የሚባል ፍጡር
በጥርሴም ፡ አለቅም!።
@mikiyas_feyisa
28.03.202519:26
*
አድምቄ አድሬ ሲነጋልኝ
የያዝኩት ሁሉ ከእጄ እልም ፤
ምንድነው የነካኝ እመቤቴ
እለፋለው ግን ፈቀቅ አይልም።
ድጥ ና ማጥ ነው ፡ ደጄ ሁሉ
ግራ ይቀናኛል ፡ ልያዝ ካልኩም
የዝናብ ፍሳሽ ፡ የሚያስገባው
የእናቴን ጓዳም አላደስኩም።
ምንድነው ሰልፉ የሚያውከኝ?
አላልፍም አለኝ የእለት መርዶ፥
ምንም ሳልፈጥር ፡ ስንፈራገጥ
ባከንኩኝ እኮ ፡ ልቀር ባዶ።
ቀን ያቀናሁት በሌት ሲፈርስ
በሌት ያቆምኩት ቀን ሲከዳኝ ፤
ማለቅስበት ሰው አንድም ሳይኖር
ቅን በሌለበት ፍትህ ሚዳኝ፦
ለምን ኳተንኩኝ ፡ እናት ዓለም?
ግልገል ሆንኩ እኮ ፡ የተረሳ ፤
ወኔዬን እንኳን ቀን ቢከዳው
እነዛ ሁሉ ፡ ህልሞቼሳ?
ምን አጥፍቼ ነው በልጅሽ ፊት?
ምን ረግጦ ነው ፡ የእግሬ ዳናው?
የምሻው እሺ ፡ ይሁን.. ይራቅ
የያዝኩት ለምን ፡ የማይፀናው?
ምስቅልቅል ብሏል
ተስፋ ፣ ህልሜ፡
ፊት የነበረኝ ፡ ፋና ወጊው ፤
አሁን ላንዴ እንኳን አየር ልውሰድ
እስቲ መንፈሴን ፡ አረጋጊው።
ብዬ ጠረኩኝ
የአይኔን እምባ ፦
ከመደፋቴ ፡ ቀና አልኩኝ ፤
ቁጢጥ ብዬ ስዕሏ ስር
ከሬት የባሰ ሀቄን ዋጥኩኝ።
ከሩቅ የመጣ የስብከት ድምፅ
ከሽውታ ጋር ነክቶኝ ያልፋል፦
"በእግዜር እንመን ወንድሞቼ
እርሱ ጥላ ነው ፡ ያሳርፋል።
እዮብ ምን ነበር ፡ ከእጁ የቀረው
ቸር እግዚአብሄርን ፡ ሲያመሰግን?
ውጪው መልካችን አማኝ መስሎ
በዙር ይጮሃል ፡ ውስጣችን ግን!
ሀቁ ይሄ ነው ፡ ህይወት ህጓ
እሱን ሚያከብር ያልፈለታል፤
ወድቆ ከማያውቅ ሰው በላቀ
ወድቆ የተነሳ ፤ ይበረታል።
እንኳን ሰው ቀርቶ
የእግዜር አምሳል
ኤሎሄ ጌታ ማረኝ የሚል፤
ብረትም እንኳን ሀቁን አውቆ
በ'ሳት አልፎ ነው ሚሆን አክሊል።
አንጠራጠር እረኛችን፦
እኛን ሲጠብቅ ፡ ከቶ አይሰንፍም፤
ማንቸለው ችግር አሸክሞ
እንደ ግብዝ ሰው ፡ ጥሎ አያልፍም።"
....
ሰባኪው ፍቅርን ይተርካል
የድምፁ ቃና ሀይል አለው፥
እኔ ግን ስ'ሏን እያስተዋልኩ
የምትለኝን ፡ እሰማለው።
ለሚያይ ካህኑ ቢያስተምርም
አሜን እያለ ፡ ሲያደምቅ አማኝ፤
እኔ ግን ፡ ከዚህ ተነጥሎ
የእርሷ ቃላት ነው ፡ የሚሰማኝ!።
ምን አልሺኝ ድንግል?
@mikiyas_feyisa
አድምቄ አድሬ ሲነጋልኝ
የያዝኩት ሁሉ ከእጄ እልም ፤
ምንድነው የነካኝ እመቤቴ
እለፋለው ግን ፈቀቅ አይልም።
ድጥ ና ማጥ ነው ፡ ደጄ ሁሉ
ግራ ይቀናኛል ፡ ልያዝ ካልኩም
የዝናብ ፍሳሽ ፡ የሚያስገባው
የእናቴን ጓዳም አላደስኩም።
ምንድነው ሰልፉ የሚያውከኝ?
አላልፍም አለኝ የእለት መርዶ፥
ምንም ሳልፈጥር ፡ ስንፈራገጥ
ባከንኩኝ እኮ ፡ ልቀር ባዶ።
ቀን ያቀናሁት በሌት ሲፈርስ
በሌት ያቆምኩት ቀን ሲከዳኝ ፤
ማለቅስበት ሰው አንድም ሳይኖር
ቅን በሌለበት ፍትህ ሚዳኝ፦
ለምን ኳተንኩኝ ፡ እናት ዓለም?
ግልገል ሆንኩ እኮ ፡ የተረሳ ፤
ወኔዬን እንኳን ቀን ቢከዳው
እነዛ ሁሉ ፡ ህልሞቼሳ?
ምን አጥፍቼ ነው በልጅሽ ፊት?
ምን ረግጦ ነው ፡ የእግሬ ዳናው?
የምሻው እሺ ፡ ይሁን.. ይራቅ
የያዝኩት ለምን ፡ የማይፀናው?
ምስቅልቅል ብሏል
ተስፋ ፣ ህልሜ፡
ፊት የነበረኝ ፡ ፋና ወጊው ፤
አሁን ላንዴ እንኳን አየር ልውሰድ
እስቲ መንፈሴን ፡ አረጋጊው።
ብዬ ጠረኩኝ
የአይኔን እምባ ፦
ከመደፋቴ ፡ ቀና አልኩኝ ፤
ቁጢጥ ብዬ ስዕሏ ስር
ከሬት የባሰ ሀቄን ዋጥኩኝ።
ከሩቅ የመጣ የስብከት ድምፅ
ከሽውታ ጋር ነክቶኝ ያልፋል፦
"በእግዜር እንመን ወንድሞቼ
እርሱ ጥላ ነው ፡ ያሳርፋል።
እዮብ ምን ነበር ፡ ከእጁ የቀረው
ቸር እግዚአብሄርን ፡ ሲያመሰግን?
ውጪው መልካችን አማኝ መስሎ
በዙር ይጮሃል ፡ ውስጣችን ግን!
ሀቁ ይሄ ነው ፡ ህይወት ህጓ
እሱን ሚያከብር ያልፈለታል፤
ወድቆ ከማያውቅ ሰው በላቀ
ወድቆ የተነሳ ፤ ይበረታል።
እንኳን ሰው ቀርቶ
የእግዜር አምሳል
ኤሎሄ ጌታ ማረኝ የሚል፤
ብረትም እንኳን ሀቁን አውቆ
በ'ሳት አልፎ ነው ሚሆን አክሊል።
አንጠራጠር እረኛችን፦
እኛን ሲጠብቅ ፡ ከቶ አይሰንፍም፤
ማንቸለው ችግር አሸክሞ
እንደ ግብዝ ሰው ፡ ጥሎ አያልፍም።"
....
ሰባኪው ፍቅርን ይተርካል
የድምፁ ቃና ሀይል አለው፥
እኔ ግን ስ'ሏን እያስተዋልኩ
የምትለኝን ፡ እሰማለው።
ለሚያይ ካህኑ ቢያስተምርም
አሜን እያለ ፡ ሲያደምቅ አማኝ፤
እኔ ግን ፡ ከዚህ ተነጥሎ
የእርሷ ቃላት ነው ፡ የሚሰማኝ!።
ምን አልሺኝ ድንግል?
@mikiyas_feyisa
26.03.202513:12
ቀሽም አይደለሽ
እምላለው፡
በጉብዝናሽ ነው
ሽሬ የዳንኩት ፤
በጥንካሬ አይበልጡሽም
ለስላሳ ነበር የፈለኩት።
@mikiyas_feyisa
እምላለው፡
በጉብዝናሽ ነው
ሽሬ የዳንኩት ፤
በጥንካሬ አይበልጡሽም
ለስላሳ ነበር የፈለኩት።
@mikiyas_feyisa
23.03.202506:31
ቱ!
እኔን ብሎ ደግሞ
የሲግማ ህግ አውጪ
አሁን ልቤን አምጪ
ይኸው እጅና እግሬ
ከጠቀመሽ እንደው
ልቤ ነው ሚከብደው
ሚሆንብሽ ሸክም
ቀኔን በምን ላክም?
እኔን በምን ላክም?
ወይኔ ሲግማነቴ
ወይኔ ሲግማነቴ
ባልበሰለ ጀብዱ
ሰው ያጣውን ነፍሱን
በዲስኩር ሚያረካ
ቆንጆ ያጣ ወንድ እንጂ
ሲግማ የለም ለካ
ወይ ሲግማ : ተግማማ
ወይ ሲግማው : ተግማማው
አንድሪው ቴት በቃኝ
አንቺን ነው ምሰማው።
ከአለም ጥበብ ያልፋል
የተፈጥሮሽ ግጥም ፤
ቀነኒሳም ቢሆን
አንቺን ካየ አይሮጥም።
ሀይሌም በተአምር
ለሰው ብር ያድላል
ላርሰናል ዋንጫ ምን?
ዱባ ወጥ ይበላል።
ወይ መፈቀር እቴ
ድንቄም ቀልብን መጣል ፤
አንቺን ያየ ለታ
እንኳንስ ጃል መሮ
ጅብ ከጫካ ይወጣል።
ሳቂ ምናለብሽ
የኔ ነው ጥፋቱ
መንጌ ምናባቱ
መሌ ምናባቱ
ቀይ ሽብር ለመልክሽ
ኮማንዶ ለክብርሽ
ያውጅልሽ አድማ
የታባቱን ሲግማ!
ተይ አትሳቂብኝ
ተይ አትመሪብኝ
ፊትሽን እያየው
ያመልጠኛል ሳቄ ፤
ካንቺ ጋር ከሆነ
እንኳንና ህይወት ፡ ይረዝማል በውቄ።
ውይይ ተረዱኝ በቃ
ዓለም ሀቁን ይስማ፤
ፍፁም አለነበረም
ከኔ በላይ ሲግማ።
ግግር አለት ነበርኩ
ከስራ እና ከጂም
ውጪ የማልገኝ፤
እርሾ ውበቷ ነው
እንዲህ ሊጥ ያረገኝ።
ወይኔ ሲግማነቴ
ማርና ወተቴ
ወይኔ ሲግማነቴ
ማርና ወተቴ
"ጀንታላው ወንዳወንድ
የተሽቀረቀረ
እንደ ፖለቲካ
ተልከስክሶ ቀረ"
ይሉኛል ሰማለው
ያሙኛል ሰማለው
ሆኖም ተደፍቼ
አንቺን አልማለው
ምናገባኝ ግና
ምንያደርጉልኛል?
አንቺን ይሰጡኛል?
ሲያሻቸው ያምፁ
ያረጀ ሲግማነት
ማዕረጌን ይቀሙት፤
ብቻ ላንድ ጊዜ
ሳሚኝና ልሙት።
@mikiyas_feyisa
እኔን ብሎ ደግሞ
የሲግማ ህግ አውጪ
አሁን ልቤን አምጪ
ይኸው እጅና እግሬ
ከጠቀመሽ እንደው
ልቤ ነው ሚከብደው
ሚሆንብሽ ሸክም
ቀኔን በምን ላክም?
እኔን በምን ላክም?
ወይኔ ሲግማነቴ
ወይኔ ሲግማነቴ
ባልበሰለ ጀብዱ
ሰው ያጣውን ነፍሱን
በዲስኩር ሚያረካ
ቆንጆ ያጣ ወንድ እንጂ
ሲግማ የለም ለካ
ወይ ሲግማ : ተግማማ
ወይ ሲግማው : ተግማማው
አንድሪው ቴት በቃኝ
አንቺን ነው ምሰማው።
ከአለም ጥበብ ያልፋል
የተፈጥሮሽ ግጥም ፤
ቀነኒሳም ቢሆን
አንቺን ካየ አይሮጥም።
ሀይሌም በተአምር
ለሰው ብር ያድላል
ላርሰናል ዋንጫ ምን?
ዱባ ወጥ ይበላል።
ወይ መፈቀር እቴ
ድንቄም ቀልብን መጣል ፤
አንቺን ያየ ለታ
እንኳንስ ጃል መሮ
ጅብ ከጫካ ይወጣል።
ሳቂ ምናለብሽ
የኔ ነው ጥፋቱ
መንጌ ምናባቱ
መሌ ምናባቱ
ቀይ ሽብር ለመልክሽ
ኮማንዶ ለክብርሽ
ያውጅልሽ አድማ
የታባቱን ሲግማ!
ተይ አትሳቂብኝ
ተይ አትመሪብኝ
ፊትሽን እያየው
ያመልጠኛል ሳቄ ፤
ካንቺ ጋር ከሆነ
እንኳንና ህይወት ፡ ይረዝማል በውቄ።
ውይይ ተረዱኝ በቃ
ዓለም ሀቁን ይስማ፤
ፍፁም አለነበረም
ከኔ በላይ ሲግማ።
ግግር አለት ነበርኩ
ከስራ እና ከጂም
ውጪ የማልገኝ፤
እርሾ ውበቷ ነው
እንዲህ ሊጥ ያረገኝ።
ወይኔ ሲግማነቴ
ማርና ወተቴ
ወይኔ ሲግማነቴ
ማርና ወተቴ
"ጀንታላው ወንዳወንድ
የተሽቀረቀረ
እንደ ፖለቲካ
ተልከስክሶ ቀረ"
ይሉኛል ሰማለው
ያሙኛል ሰማለው
ሆኖም ተደፍቼ
አንቺን አልማለው
ምናገባኝ ግና
ምንያደርጉልኛል?
አንቺን ይሰጡኛል?
ሲያሻቸው ያምፁ
ያረጀ ሲግማነት
ማዕረጌን ይቀሙት፤
ብቻ ላንድ ጊዜ
ሳሚኝና ልሙት።
@mikiyas_feyisa
20.03.202512:36
አፈቅርሻለሁኝ
አልወድሽም ግና
ፀሀይ ቪዛ አወጣች
ጨፈረች ደመና
ሰው ነበርኩኝ ድመት
በደረቱ ሚሳብ እንዳሳነባሪ
ሞተሻል አውቃለው
የሰርግሽን ለቅሶ
ነገረኝ ፈጣሪ
አምሮብሻል ደግሞ
ወዝሽም ገርጥቷል፤
አጎትሽ ጋሽ ዳምጤ
ወንድ ልጅ ሞቶበት
መታወቂያ አውጥቷል።
ምናገባኝ እኔ ..
እራሴን መች ላጥፋ?
መቼም ተስፋ አልቆርጥም ፤
ይቅር በዪኝ በቃ
አለቀብኝ ግጥም።😂
@mikiyas_feyisa
አልወድሽም ግና
ፀሀይ ቪዛ አወጣች
ጨፈረች ደመና
ሰው ነበርኩኝ ድመት
በደረቱ ሚሳብ እንዳሳነባሪ
ሞተሻል አውቃለው
የሰርግሽን ለቅሶ
ነገረኝ ፈጣሪ
አምሮብሻል ደግሞ
ወዝሽም ገርጥቷል፤
አጎትሽ ጋሽ ዳምጤ
ወንድ ልጅ ሞቶበት
መታወቂያ አውጥቷል።
ምናገባኝ እኔ ..
እራሴን መች ላጥፋ?
መቼም ተስፋ አልቆርጥም ፤
ይቅር በዪኝ በቃ
አለቀብኝ ግጥም።😂
@mikiyas_feyisa
18.03.202520:23
ስሚኝ
ምናለፋሽ
ላጠፊኝ ላልጠፋሽ
እንደነ እነሱ
ማድነቅ ካልቻልኩበት
ባይሽ ምናለበት?
ቁምነገር ካጠረን
ባንስቅ ባንጫወት
ምናችን ይጎላል?
ዝምታም ደስ ይላል!
ማይደበዝዝ መልክሽ
በአይኔ ተንሰራፍቶ
ምን ያረጋል ፎቶ?
እንደነ እዩልኝ
እንደነ እወቁልኝ
ታይታን ባንኮርጅም
አብረን አናረጅም?
ተዪው
ምን አለፋሽ
ላጠፊኝ ላልጠፋሽ
የምታስመስዪው
ፍቅር እንዳነደደው ፤
ምናለበት ብኖር
እንደተለመደው?
@mikiyas_feyisa
ምናለፋሽ
ላጠፊኝ ላልጠፋሽ
እንደነ እነሱ
ማድነቅ ካልቻልኩበት
ባይሽ ምናለበት?
ቁምነገር ካጠረን
ባንስቅ ባንጫወት
ምናችን ይጎላል?
ዝምታም ደስ ይላል!
ማይደበዝዝ መልክሽ
በአይኔ ተንሰራፍቶ
ምን ያረጋል ፎቶ?
እንደነ እዩልኝ
እንደነ እወቁልኝ
ታይታን ባንኮርጅም
አብረን አናረጅም?
ተዪው
ምን አለፋሽ
ላጠፊኝ ላልጠፋሽ
የምታስመስዪው
ፍቅር እንዳነደደው ፤
ምናለበት ብኖር
እንደተለመደው?
@mikiyas_feyisa
18.03.202503:36
እኔ እና አንቺን ያጣመረን
ልባችንን ሊከፍል ወዷል፤
አብረን ሆነን ምንድንበት
የተሰጠን ጊዜ ሄዷል።
እንለያይ ሳይፈርድብን
ሳያነደን የሲዖል ፍም፤
መሳሙን ተይ ብቻ እንሩጥ
ካልፈጠንን አንደርስም።
ብያት ስሮጥ..
እሷም ስትሮጥ..
ሳያት ዞሬ
ስታይ ዞራ
ፍዝዝ አርጋው
የአይኗን ብሌን
የፍቅሯን ዳር ሙሾ እንዲዳኝ፤
እያየሁኋት እግሬ እምቢ አለ
ተመለስኩኝ አምላክ ይርዳኝ!።
በቃ አልፈራም
ከዚህ ኋላ
እንኳን እቶን ቢዘራ ደም፤
ደልቶኝ ይሁን እያየኋት
ከረፈደም .. ከፈረደም!
@mikiyas_feyisa
ልባችንን ሊከፍል ወዷል፤
አብረን ሆነን ምንድንበት
የተሰጠን ጊዜ ሄዷል።
እንለያይ ሳይፈርድብን
ሳያነደን የሲዖል ፍም፤
መሳሙን ተይ ብቻ እንሩጥ
ካልፈጠንን አንደርስም።
ብያት ስሮጥ..
እሷም ስትሮጥ..
ሳያት ዞሬ
ስታይ ዞራ
ፍዝዝ አርጋው
የአይኗን ብሌን
የፍቅሯን ዳር ሙሾ እንዲዳኝ፤
እያየሁኋት እግሬ እምቢ አለ
ተመለስኩኝ አምላክ ይርዳኝ!።
በቃ አልፈራም
ከዚህ ኋላ
እንኳን እቶን ቢዘራ ደም፤
ደልቶኝ ይሁን እያየኋት
ከረፈደም .. ከፈረደም!
@mikiyas_feyisa
记录
20.04.202523:59
1.8K订阅者31.03.202523:59
300引用指数07.04.202520:04
1.2K每帖平均覆盖率07.04.202520:04
1.2K广告帖子的平均覆盖率04.01.202523:59
19.54%ER07.04.202520:04
69.06%ERR登录以解锁更多功能。