

07.05.202505:37
ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል፡- ፍልሚያን የመምረጥ ምስጢር
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
ወቅቱ ግሪክና ሮም የጦርነት ፍጥጫ ላይ የነበሩበት ዘመን ነው፡፡ በሁለቱም ወገን 40 ሺህ የሚያክል ጽኑ የጦር ሰራዊት ተሰልፏል፡፡ የግሪኩ ንጉስ ፓይረስ (King Pyrrus) አይኖቹን ሮም ላይ ተክሏል፡፡ “ሮምን ካላሸነፍኩ አላርፍም” ያለ ይመስላል፤ ማንም ሰው ከዚህ አቋሙ ሊመልሰው እስከማይችል ድረስ ቆርጦ ነበር፡፡ የጦር መሳሪያ አይነት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸውን ዝሆኖች ሁሉ ሳይቀር ሰብስቧል፡፡
ከዚህ በፊት የተፋለመውን ፍልሚያ ሁሉ በማሸነፍ የታወቀ ንጉስ ነው፡፡ የሮም አገዛዝ ያበቃለት ይመስላል፡፡ ውጊያው ጀምሮ ብዙ መራራ ቀናትን ካስቆጠረ በኋላ ማንም የማያሸንፍበት የእልቂት ፍጥጫ ሆነ፡፡ ሆኖም፣ በድንገት ግሪኮች ድልን ተቀዳጁ፡፡ ግዙፍ ዝሆኖቻቸው በብዙ ቁጥር ሆነው ወደ ሮማውያን ክልል ጥሰው በመግባታቸው ከሞት የተረፉት ሮማውያን ወደ ኋላ መሸሽ ግድ ሆነባቸው፡፡
የንጉስ ፓይረስ ሰራዊት ግን እጅግ ደክሟል፡፡ ጉልበትን ለመሰብሰብ ባለበት ስፍራ ከሰራዊቱ ጋር ተከማችቶ እንዳለ አንድ ወዳጁ ስላገኘው ድል “እንኳን ደስ ያለህ” አለው፡፡ ንጉስ ፓይረስ የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር፣ “ከአሁን ወዲያ አንድ ፍልሚያ ተፋልሜ ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል”፡፡
አንዳንድ ጊዜ በፊታችን የመጣውን ፍልሚያ ሁሉ መዋጋትና ማሸነፍ ያለብን ይመስለናል፡፡ የተጫረ ጸብ ውስጥ ሁሉ ራሳችንን እንጨምራለን፣ ለተናገረን ሰው ሁሉ መልስ ለመስጠት ጊዜ አይፈጅብንም፣ ለነካን ሰው አጸፋ ሳንመልስ እንቅልፍ አይወስደንም፡፡ በዚህ “ብርታታችን” ከዚህ በፊት ብዙዎችን አንበርክከን ሊሆን ይችላል፡፡
መለስ ብለን ሕይወታችንን ስናጤነው ግን አንድ ሺህ ፍልሚያዎችን አሸንፈን፣ ነገር ግን አንድን ነገር ለመገንባት ጊዜ ያጣን ሰዎች ሆነን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ ብዙ የተዋጋናቸው ሁኔታዎችና ሰዎች በታሪካችን ተመዝግበው አንድም የገነባነው ቁም ነገር ከሌለ ትኩረት የተነጠቀ ሰው የመሆናችን እውነታ አከራካሪ አይደለም፡፡
የሕይወትን ውጣ ውረድ በሚገባ ስንቃኘውና ስንጨምቀው እውነተኛ ፍልሚያን ልንፋለምባቸው የሚገቡን ነገሮች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡
ብዙ ሰዎች በሞት አልጋቸው ላይ ሆነው ሲጠየቁ ወይም የመናገር እድል ሲያገኙ በሕይወት ዘመናቸው በወሰዷቸው አንዳንድ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ላይ የሚናገሩት ነገር አላቸው፡፡
አንዳንዶች፣ “እገሌን ጥሩልኝና ይቅርታ ልጠይቀው” በማለት በዘመናቸው ሲጋፉት የኖሩትን ሰው በመጨረሻ ትንፋሻቸው ሊያቅፉት ይሞክራሉ፡፡ ሌሎች፣ “ለእገሌ የወሰድኩበትን ይህንና ያንን ነገር እባካችሁ መልሱልኝ” በማለት በውጊያ የወሰዱትን በልመና ሊመልሱ ይመኛሉ፡፡
“ይህንን ንብረቴን ለእገሌ አውርሱልኝ” በማለትም በብዙ ፍልሚያ የሰበሰቡትን ንብረት መልቀቅ ምርጫ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አይተውና አሳይተው የሚያልፉም ብዙ ናቸው፡፡
ሕይወት ምንድን ነች? ሕይወት ሁለተኛ እድል የማትሰጥና ከራሳችን አልፈን ለሌላው የሚጠቅም ነገር አድርገን አጣጥመናት ልናልፋት የምትገባ ትእይንት ናት እንጂ ሕይወት በጠላት የተከበበችና ለፍልሚያ የተወሰነች የጦርነት ሜዳ አይደለችም፡፡
ለአንዳንዶች ግን ይህ የሕይወት ስእል በፍጹም ተቀባይነት የማያገኝ ጉዳይ ነው፡፡ የሚያውቁት ሌላ ነውና፡፡ በእርግጥ ነው በዚህች ምድር ላይ ስንኖር የማንፈልጋቸው ሙግቶችና ትግሎች አልፈው ወደ እኛ ይመጣሉ፡፡ ስለሆነም፣ ሕይወት ከምንም ችግር ነጻ የሆነች ጎዳና ነች ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡
ለማለት የተፈለገው የመጣውን ግፊያ ሁሉ መጋፋት፣ የተነሳውን ውድድር ሁሉ መወዳደር፣ የተከሰተውን ፍትጊያ ሁሉ የመፋተግ ግዴታ የለብንም፡፡ የምንፋለማቸውን ፍልሚያዎች የመምረጥ እድሉም ሆነ ብቃቱ አለን፡፡
የሕይወታችን ጥራት የሚለካው ባሸነፍናቸው ፍልሚያዎች ሳይሆን በመረጥናቸው የፍልሚያ አይነቶች ነው፡፡ የምትሰለፍለት ዓላማና የምትከራከርለት ነጥብ የውስጥህን አመለካከት ጠቋሚ ነውና፡፡ ተራ ሰው ለተራ ነገር ይጋፋል፣ የከበረው ሰው ደግሞ ፍልሚያዎቹን መዝኖ ለከበረውና ለዘላቂው ነገር ራሱን ያቀርባል፡፡ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
ወቅቱ ግሪክና ሮም የጦርነት ፍጥጫ ላይ የነበሩበት ዘመን ነው፡፡ በሁለቱም ወገን 40 ሺህ የሚያክል ጽኑ የጦር ሰራዊት ተሰልፏል፡፡ የግሪኩ ንጉስ ፓይረስ (King Pyrrus) አይኖቹን ሮም ላይ ተክሏል፡፡ “ሮምን ካላሸነፍኩ አላርፍም” ያለ ይመስላል፤ ማንም ሰው ከዚህ አቋሙ ሊመልሰው እስከማይችል ድረስ ቆርጦ ነበር፡፡ የጦር መሳሪያ አይነት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸውን ዝሆኖች ሁሉ ሳይቀር ሰብስቧል፡፡
ከዚህ በፊት የተፋለመውን ፍልሚያ ሁሉ በማሸነፍ የታወቀ ንጉስ ነው፡፡ የሮም አገዛዝ ያበቃለት ይመስላል፡፡ ውጊያው ጀምሮ ብዙ መራራ ቀናትን ካስቆጠረ በኋላ ማንም የማያሸንፍበት የእልቂት ፍጥጫ ሆነ፡፡ ሆኖም፣ በድንገት ግሪኮች ድልን ተቀዳጁ፡፡ ግዙፍ ዝሆኖቻቸው በብዙ ቁጥር ሆነው ወደ ሮማውያን ክልል ጥሰው በመግባታቸው ከሞት የተረፉት ሮማውያን ወደ ኋላ መሸሽ ግድ ሆነባቸው፡፡
የንጉስ ፓይረስ ሰራዊት ግን እጅግ ደክሟል፡፡ ጉልበትን ለመሰብሰብ ባለበት ስፍራ ከሰራዊቱ ጋር ተከማችቶ እንዳለ አንድ ወዳጁ ስላገኘው ድል “እንኳን ደስ ያለህ” አለው፡፡ ንጉስ ፓይረስ የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር፣ “ከአሁን ወዲያ አንድ ፍልሚያ ተፋልሜ ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል”፡፡
አንዳንድ ጊዜ በፊታችን የመጣውን ፍልሚያ ሁሉ መዋጋትና ማሸነፍ ያለብን ይመስለናል፡፡ የተጫረ ጸብ ውስጥ ሁሉ ራሳችንን እንጨምራለን፣ ለተናገረን ሰው ሁሉ መልስ ለመስጠት ጊዜ አይፈጅብንም፣ ለነካን ሰው አጸፋ ሳንመልስ እንቅልፍ አይወስደንም፡፡ በዚህ “ብርታታችን” ከዚህ በፊት ብዙዎችን አንበርክከን ሊሆን ይችላል፡፡
መለስ ብለን ሕይወታችንን ስናጤነው ግን አንድ ሺህ ፍልሚያዎችን አሸንፈን፣ ነገር ግን አንድን ነገር ለመገንባት ጊዜ ያጣን ሰዎች ሆነን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ ብዙ የተዋጋናቸው ሁኔታዎችና ሰዎች በታሪካችን ተመዝግበው አንድም የገነባነው ቁም ነገር ከሌለ ትኩረት የተነጠቀ ሰው የመሆናችን እውነታ አከራካሪ አይደለም፡፡
የሕይወትን ውጣ ውረድ በሚገባ ስንቃኘውና ስንጨምቀው እውነተኛ ፍልሚያን ልንፋለምባቸው የሚገቡን ነገሮች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡
ብዙ ሰዎች በሞት አልጋቸው ላይ ሆነው ሲጠየቁ ወይም የመናገር እድል ሲያገኙ በሕይወት ዘመናቸው በወሰዷቸው አንዳንድ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ላይ የሚናገሩት ነገር አላቸው፡፡
አንዳንዶች፣ “እገሌን ጥሩልኝና ይቅርታ ልጠይቀው” በማለት በዘመናቸው ሲጋፉት የኖሩትን ሰው በመጨረሻ ትንፋሻቸው ሊያቅፉት ይሞክራሉ፡፡ ሌሎች፣ “ለእገሌ የወሰድኩበትን ይህንና ያንን ነገር እባካችሁ መልሱልኝ” በማለት በውጊያ የወሰዱትን በልመና ሊመልሱ ይመኛሉ፡፡
“ይህንን ንብረቴን ለእገሌ አውርሱልኝ” በማለትም በብዙ ፍልሚያ የሰበሰቡትን ንብረት መልቀቅ ምርጫ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አይተውና አሳይተው የሚያልፉም ብዙ ናቸው፡፡
ሕይወት ምንድን ነች? ሕይወት ሁለተኛ እድል የማትሰጥና ከራሳችን አልፈን ለሌላው የሚጠቅም ነገር አድርገን አጣጥመናት ልናልፋት የምትገባ ትእይንት ናት እንጂ ሕይወት በጠላት የተከበበችና ለፍልሚያ የተወሰነች የጦርነት ሜዳ አይደለችም፡፡
ለአንዳንዶች ግን ይህ የሕይወት ስእል በፍጹም ተቀባይነት የማያገኝ ጉዳይ ነው፡፡ የሚያውቁት ሌላ ነውና፡፡ በእርግጥ ነው በዚህች ምድር ላይ ስንኖር የማንፈልጋቸው ሙግቶችና ትግሎች አልፈው ወደ እኛ ይመጣሉ፡፡ ስለሆነም፣ ሕይወት ከምንም ችግር ነጻ የሆነች ጎዳና ነች ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡
ለማለት የተፈለገው የመጣውን ግፊያ ሁሉ መጋፋት፣ የተነሳውን ውድድር ሁሉ መወዳደር፣ የተከሰተውን ፍትጊያ ሁሉ የመፋተግ ግዴታ የለብንም፡፡ የምንፋለማቸውን ፍልሚያዎች የመምረጥ እድሉም ሆነ ብቃቱ አለን፡፡
የሕይወታችን ጥራት የሚለካው ባሸነፍናቸው ፍልሚያዎች ሳይሆን በመረጥናቸው የፍልሚያ አይነቶች ነው፡፡ የምትሰለፍለት ዓላማና የምትከራከርለት ነጥብ የውስጥህን አመለካከት ጠቋሚ ነውና፡፡ ተራ ሰው ለተራ ነገር ይጋፋል፣ የከበረው ሰው ደግሞ ፍልሚያዎቹን መዝኖ ለከበረውና ለዘላቂው ነገር ራሱን ያቀርባል፡፡ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988


06.05.202514:01
✅ እጀግ በሚገርም ሁኔታ የዓለምን የበላይነት ማለትም በእኮኖሚ በጦር ሚዛን እና በመሳሰሉት የበላይነትን ለመቀዳጀት ሲባል የሩሲያ KGB እና የአሜሪካነ CIA በሰው ሃገር ላይ ያገባኛል በማለት ተፋጠዋል ( ማን ይሳካለት ይሆን?
✅ የ KGBው የስለላ መረብ ሃላፊ ላቀደው ታላቅ ሴራ ማስፈፀሚያ የሰውን ልጅ እንደ እንስሳ ከመጠቀሙም በላይ እንደ ቀልድ እያደባ ይህን ታላቅ ሚስጢር የሚፈፅምበት ቀን ተቃርቧል ይፈፅመው ይሆን?
✅ የ CIA ዋ ሰላይ አንድ አስደንጋጭ የ KGBን ሚስጥር ከመስማትም አልፋ ትደርስበታለች ግን አለቆቿ ሚስጢሩን በማጣጣል ሰማ በማጣቷ ራሷ ሕይወቷን አደጋ ላይ በመጣል ትጋፈጠዋለች::ታጋልጠው ይሆን?
✅ KGB ያጠመደው የኒውክለር ቦንብ CIA ሳይደርስበት የመፈንጃው ጊዜ ደግሞ ተቃርቧል ይህ ጓረቤት ሀገርንም ሆነ አካባቢውን የሚያጠድም ታላቅ > የቦንቡ ሚስጢር ከተሰማ በኃላ ሃገሮችን ሽብር ውስጥ ከመክተቱም --- በላይ እልህ አስጨራሽ እርብርብ ይደረጋል :: ይከሽፋ ይሆን?
✅ እሷ ከደረሰባት የእንሰሳዊ ድርጊት እና እሱ ክደረሰበት በደል የተነሳ የመበቀያ ጊዜና ሁኔታ በመድረሱ እንዳረሩት የልባቸውን የበቀል መልስ ለመመለስ ተቃርበዋል ይፈዕሙት ይሆን፡፡
✅ ይህ መፅሐፍ ለፍቅር ሲባል ከአላማ ውጪ የሚደረግ ጉቦን ፤ለገንዘብ ሲባል የጣምራ ሰላይነት ሚናን ፣ ክደረሰባቸው በደል የተነሳ የበቀል ዕዋን የመጐንጨት እና የተጠበቀው እንዳልተጠበቀ የሆኑና ያልሆነ ድርጊቶች እየተፈፀሙ የአንባቢን ቀልብ በመግዛት ከመጀመሪያ ገፅ እንስቶ ሚስጢሩ አስከሚፈታ የመጨረሻው ገፅ ድረስ በጉጉት የሚነበብ መፅሐፍ ነው።
✅✅መፅሐፍ በ Pdf ማታ 3 ሰአት ይለቀቃል
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
✅ የ KGBው የስለላ መረብ ሃላፊ ላቀደው ታላቅ ሴራ ማስፈፀሚያ የሰውን ልጅ እንደ እንስሳ ከመጠቀሙም በላይ እንደ ቀልድ እያደባ ይህን ታላቅ ሚስጢር የሚፈፅምበት ቀን ተቃርቧል ይፈፅመው ይሆን?
✅ የ CIA ዋ ሰላይ አንድ አስደንጋጭ የ KGBን ሚስጥር ከመስማትም አልፋ ትደርስበታለች ግን አለቆቿ ሚስጢሩን በማጣጣል ሰማ በማጣቷ ራሷ ሕይወቷን አደጋ ላይ በመጣል ትጋፈጠዋለች::ታጋልጠው ይሆን?
✅ KGB ያጠመደው የኒውክለር ቦንብ CIA ሳይደርስበት የመፈንጃው ጊዜ ደግሞ ተቃርቧል ይህ ጓረቤት ሀገርንም ሆነ አካባቢውን የሚያጠድም ታላቅ > የቦንቡ ሚስጢር ከተሰማ በኃላ ሃገሮችን ሽብር ውስጥ ከመክተቱም --- በላይ እልህ አስጨራሽ እርብርብ ይደረጋል :: ይከሽፋ ይሆን?
✅ እሷ ከደረሰባት የእንሰሳዊ ድርጊት እና እሱ ክደረሰበት በደል የተነሳ የመበቀያ ጊዜና ሁኔታ በመድረሱ እንዳረሩት የልባቸውን የበቀል መልስ ለመመለስ ተቃርበዋል ይፈዕሙት ይሆን፡፡
✅ ይህ መፅሐፍ ለፍቅር ሲባል ከአላማ ውጪ የሚደረግ ጉቦን ፤ለገንዘብ ሲባል የጣምራ ሰላይነት ሚናን ፣ ክደረሰባቸው በደል የተነሳ የበቀል ዕዋን የመጐንጨት እና የተጠበቀው እንዳልተጠበቀ የሆኑና ያልሆነ ድርጊቶች እየተፈፀሙ የአንባቢን ቀልብ በመግዛት ከመጀመሪያ ገፅ እንስቶ ሚስጢሩ አስከሚፈታ የመጨረሻው ገፅ ድረስ በጉጉት የሚነበብ መፅሐፍ ነው።
✅✅መፅሐፍ በ Pdf ማታ 3 ሰአት ይለቀቃል
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988


06.05.202507:25
🕯ፎሬክስ በአማርኛ መሉ ትምህርት
📈ለጀማሪ
📈ለመካከለኛ
📊ለ ትሬደር
📉ለሁሉም
ቻናሉን በመቀላቀል ይማሩ
⚡️⚡️⚡️
https://t.me/EthioLearning19/3749
https://t.me/EthioLearning19/3749
https://t.me/EthioLearning19/3749
📈ለጀማሪ
📈ለመካከለኛ
📊ለ ትሬደር
📉ለሁሉም
ቻናሉን በመቀላቀል ይማሩ
⚡️⚡️⚡️
https://t.me/EthioLearning19/3749
https://t.me/EthioLearning19/3749
https://t.me/EthioLearning19/3749


05.05.202519:34
05.05.202508:50
04.05.202517:23
ፍቅር እና ቁጥር
ስንግባባ ሰሞን እኔ መላመድን ለማምለጥ የምባትል ባተሌ ነበርኩ። የተጣመርኩት ባይኖርም ራሴን ብቻዬን እወደዋለሁ።
የማልደራደርበት ማንነት ነበረኝ። ሌሎችን የማደንቅበትና የማከብርበት የማንነት መለኪያያዎችም ነበሩኝ።
እሱ ---- አላውቅም የሱን ፍላጎት........ ብቻ አላጣደፈኝም። የተለየ ፍላጎት እንዳለውም ሊያሳየኝ አልተፍጨረጨረም። የሰው ፍላጎት እና ሀሳብ ሲጫንብኝ እንደማልወድ ገብቶታል።
ማባበሉ አጥንቶ የቀመረበት ነበር። ጆሮዬ ከአንዴም ሁለቴ ከድቶኛል እና በተቆለጳጰሰ የፍቅር ዓረፍተ ነገር የሚደነግጥ ልብ እንደሌለኝ አውቋል። ቀስ በቀስ ለፍፅምና የተጠጋ እሱነቱን ነው የጋተኝ።
በገንዘብ ተተምነው ውድ የሆኑ ስጦታዎች እየገዛ አይደለም ያቀበጠኝ፤ በአንድ አንጎል የምናስብ እስኪመስለኝ ድረስ የሚያስፈልገኝን እና ለልቤ የቀረቡ ስጦታዎችን ነበር የሰጠኝ። ውደጂኝ አላለኝም። እንድወደው ምንም አስተዋፅኦ እንዳላደረገ ዓይነት፣ .....የቀን ተቀን እሱነቱን እየኖረ እንደሆነ ዓይነት
፣....... እኔን ለመማረክ የጨመረው ምናምኒት ትጋት እንደሌለ ፣.......... ለሃጬ እስኪዝረበረብ በሱሱ ለመተብተቤ ያበረከተው ምንም እንደሌለ ሁላ ......ከደሙ ነፃ ነኝ...... እኔ የእለት ተእለት እኔነቴን ነው የኖርኩት ዓይነት እጁን ተለቀለቀ።
የሰው ልጅ አዘቦታዊ ማንነት እንዴት እንዲህ እንከን አልባ ይሆናል ብዬ አልጠየቅኩም። በየእለቱ እየገለጠ ያስነበበኝን የማንነቱን ምሰሶዎች ሰብስቤ እሱ ነው ያልኩትን እሱን በልቤ ገነባሁ ፣ በአዕምሮዬ ሳልኩ። ለዚህ ማንነት እጅ ሰጠሁ።
እዚህ ጊዜ ላይ
ፍቅሩን ፣ ጊዜውን ፣ ጆሮውን ፣ ልቡን ፣ ገላውን ፣ትኩረቱን ያልሰጠኝ የለም። 100% እሱነቱን ያለስስት ነበር የሰጠኝ። እስክበስል ማገዶ እንደምፈጅ ገብቶታል። አልተጣደፈም። ከሞከኩኝ ኋላ እስክበሰብስ እንደምታሽ ገብቶታል።
ሱሴ የሆነ ጊዜ ላይ ....... ያለእርሱ ትንፋሽ እንደሚያጥረኝ የገባው ሰዓት ላይ .......
የሂሳብ ቀመሩን ይጫወት ጀመረ። ቀስ በቀስ ከመቶ እሱነቱ ይገምሰው ገባ። ፍቅሩንም ጊዜውንም ጆሮውኑም ልቡንም ገላውንም ትኩረቱንም በግማሽ ቦደሰው። 50% !! ልቤ የምትደገፈው ምርኩዝ ስታስስ የነጠቀኝን ትንሽ ይጨምርበታል። 75%!! ........ ጨዋታው ይሄ ነው። 100 እንደነበር ይጠፋኛል።
ካጣሁት ግማሽ ይልቅ የተጨመረልኝ እሩብ ያስቦርቀኛል። ልቤ መልሳ እሱን ማምለኳን ትቀጥላለች። መልሶ ከ75% ወደ 25% ሲወርድብኝ የአየር ቧንቧዬ የጠበበ ያህል ደረቴን ያፍነኛል። መልሶ 25% እሱን ይጨምርልኛል። ግማሽ እሱነቱን እንደነሳኝ አላላዝንም። የጨመረልኝ ያስደንሰኛል።
አንድ ቀን ገላውን ለሌላ ሴት አዋሰብኝ። እዚህ ጊዜ ላይ ከሙሉ እሱነቱ 5% ፐርሰንቱን እንኳን አልሰጠኝም።
በብዙ ትዕግስት እና ጥበብ ውስጤ የገነባው እሱነቱ ግን አሁንም አልተገመሰም። ወይም በቀላሉ እንዳይፈርስ አድርጎ ከዓለት ገንብቶታል። ወይም ማመን አልፈልግም። ፍንክች አይልም።
አልካደኝም። በእንባ ታጅቦ ይቅርታ ጠየቀኝ። ይቅርታውን በአግቢኝ ጥያቄ እና ቀለበት አጀበው። የምለው ገባችሁ? ከአምስት 25% ነዳው አይደል? ያደረገውን ሳይሆን ያደረገልኝን እያሰብኩ ተፍለቀለቅኩ። ስለሚወደኝ አይደል አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ጠርቶ ፕሮፖዝ ያደረገኝ?
ሶስት ቀን የት እንዳለ እንኳን ሳይነግረኝ ዘግቶኝ ይከርምና በአራተኛው ቀን ለእናቴ ከክርስታል የተሰራ የአበባ ማስቀመጫ ገዝቶ ከች ይላል። ሶስቱን ቀን ረስቼ ለእናቴ ላሳያት ፍቅር እሸነፋለሁ።
እሱ ከሚያሳየኝ የዘቀጠ ማንነት ይልቅ በልቤ ያነገስኩት ማነነት ላይ ሙጭጭ አልኩ። በሂሳብ ቀመሩ ተወናበድኩ።
የእሱን ስዕል ከልቤ ከማፍረሴ ብዙ ቀን ቀድሞ እኔ ፈረስኩ። የእሱን እውነተኛ ማንነት አምኜ ከመቀበሌ ከብዙ ቀናት ቀድሞ የራሴ ማንነት ጠፋኝ።
መላመድን ላመልጠው የምሸመጥጥ አትሌት አልነበርኩ? እሱ ከልቤም ከህይወቴም ሲወጣ ለመሮጥም ለማምለጥም ለማሰብም የተረፈ አቅም አልነበረኝም።
*
ውብ ምሽት አምሹልኝ!!♥️❤️♥️❤️
ሜሪ ፈለቀ
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
ስንግባባ ሰሞን እኔ መላመድን ለማምለጥ የምባትል ባተሌ ነበርኩ። የተጣመርኩት ባይኖርም ራሴን ብቻዬን እወደዋለሁ።
የማልደራደርበት ማንነት ነበረኝ። ሌሎችን የማደንቅበትና የማከብርበት የማንነት መለኪያያዎችም ነበሩኝ።
እሱ ---- አላውቅም የሱን ፍላጎት........ ብቻ አላጣደፈኝም። የተለየ ፍላጎት እንዳለውም ሊያሳየኝ አልተፍጨረጨረም። የሰው ፍላጎት እና ሀሳብ ሲጫንብኝ እንደማልወድ ገብቶታል።
ማባበሉ አጥንቶ የቀመረበት ነበር። ጆሮዬ ከአንዴም ሁለቴ ከድቶኛል እና በተቆለጳጰሰ የፍቅር ዓረፍተ ነገር የሚደነግጥ ልብ እንደሌለኝ አውቋል። ቀስ በቀስ ለፍፅምና የተጠጋ እሱነቱን ነው የጋተኝ።
በገንዘብ ተተምነው ውድ የሆኑ ስጦታዎች እየገዛ አይደለም ያቀበጠኝ፤ በአንድ አንጎል የምናስብ እስኪመስለኝ ድረስ የሚያስፈልገኝን እና ለልቤ የቀረቡ ስጦታዎችን ነበር የሰጠኝ። ውደጂኝ አላለኝም። እንድወደው ምንም አስተዋፅኦ እንዳላደረገ ዓይነት፣ .....የቀን ተቀን እሱነቱን እየኖረ እንደሆነ ዓይነት
፣....... እኔን ለመማረክ የጨመረው ምናምኒት ትጋት እንደሌለ ፣.......... ለሃጬ እስኪዝረበረብ በሱሱ ለመተብተቤ ያበረከተው ምንም እንደሌለ ሁላ ......ከደሙ ነፃ ነኝ...... እኔ የእለት ተእለት እኔነቴን ነው የኖርኩት ዓይነት እጁን ተለቀለቀ።
የሰው ልጅ አዘቦታዊ ማንነት እንዴት እንዲህ እንከን አልባ ይሆናል ብዬ አልጠየቅኩም። በየእለቱ እየገለጠ ያስነበበኝን የማንነቱን ምሰሶዎች ሰብስቤ እሱ ነው ያልኩትን እሱን በልቤ ገነባሁ ፣ በአዕምሮዬ ሳልኩ። ለዚህ ማንነት እጅ ሰጠሁ።
እዚህ ጊዜ ላይ
ፍቅሩን ፣ ጊዜውን ፣ ጆሮውን ፣ ልቡን ፣ ገላውን ፣ትኩረቱን ያልሰጠኝ የለም። 100% እሱነቱን ያለስስት ነበር የሰጠኝ። እስክበስል ማገዶ እንደምፈጅ ገብቶታል። አልተጣደፈም። ከሞከኩኝ ኋላ እስክበሰብስ እንደምታሽ ገብቶታል።
ሱሴ የሆነ ጊዜ ላይ ....... ያለእርሱ ትንፋሽ እንደሚያጥረኝ የገባው ሰዓት ላይ .......
የሂሳብ ቀመሩን ይጫወት ጀመረ። ቀስ በቀስ ከመቶ እሱነቱ ይገምሰው ገባ። ፍቅሩንም ጊዜውንም ጆሮውኑም ልቡንም ገላውንም ትኩረቱንም በግማሽ ቦደሰው። 50% !! ልቤ የምትደገፈው ምርኩዝ ስታስስ የነጠቀኝን ትንሽ ይጨምርበታል። 75%!! ........ ጨዋታው ይሄ ነው። 100 እንደነበር ይጠፋኛል።
ካጣሁት ግማሽ ይልቅ የተጨመረልኝ እሩብ ያስቦርቀኛል። ልቤ መልሳ እሱን ማምለኳን ትቀጥላለች። መልሶ ከ75% ወደ 25% ሲወርድብኝ የአየር ቧንቧዬ የጠበበ ያህል ደረቴን ያፍነኛል። መልሶ 25% እሱን ይጨምርልኛል። ግማሽ እሱነቱን እንደነሳኝ አላላዝንም። የጨመረልኝ ያስደንሰኛል።
አንድ ቀን ገላውን ለሌላ ሴት አዋሰብኝ። እዚህ ጊዜ ላይ ከሙሉ እሱነቱ 5% ፐርሰንቱን እንኳን አልሰጠኝም።
በብዙ ትዕግስት እና ጥበብ ውስጤ የገነባው እሱነቱ ግን አሁንም አልተገመሰም። ወይም በቀላሉ እንዳይፈርስ አድርጎ ከዓለት ገንብቶታል። ወይም ማመን አልፈልግም። ፍንክች አይልም።
አልካደኝም። በእንባ ታጅቦ ይቅርታ ጠየቀኝ። ይቅርታውን በአግቢኝ ጥያቄ እና ቀለበት አጀበው። የምለው ገባችሁ? ከአምስት 25% ነዳው አይደል? ያደረገውን ሳይሆን ያደረገልኝን እያሰብኩ ተፍለቀለቅኩ። ስለሚወደኝ አይደል አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ጠርቶ ፕሮፖዝ ያደረገኝ?
ሶስት ቀን የት እንዳለ እንኳን ሳይነግረኝ ዘግቶኝ ይከርምና በአራተኛው ቀን ለእናቴ ከክርስታል የተሰራ የአበባ ማስቀመጫ ገዝቶ ከች ይላል። ሶስቱን ቀን ረስቼ ለእናቴ ላሳያት ፍቅር እሸነፋለሁ።
እሱ ከሚያሳየኝ የዘቀጠ ማንነት ይልቅ በልቤ ያነገስኩት ማነነት ላይ ሙጭጭ አልኩ። በሂሳብ ቀመሩ ተወናበድኩ።
የእሱን ስዕል ከልቤ ከማፍረሴ ብዙ ቀን ቀድሞ እኔ ፈረስኩ። የእሱን እውነተኛ ማንነት አምኜ ከመቀበሌ ከብዙ ቀናት ቀድሞ የራሴ ማንነት ጠፋኝ።
መላመድን ላመልጠው የምሸመጥጥ አትሌት አልነበርኩ? እሱ ከልቤም ከህይወቴም ሲወጣ ለመሮጥም ለማምለጥም ለማሰብም የተረፈ አቅም አልነበረኝም።
*
ውብ ምሽት አምሹልኝ!!♥️❤️♥️❤️
ሜሪ ፈለቀ
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
06.05.202517:47
📗📗#የመፅሀፉ_ርዕስ ➠በቀለኛው ሰላይ
( Deep lie )
📝ትርጉም ፦
👨💼 ሙሉጌታ ይፍሩ
🤵♂ ሚሊዬን ግዛው
✅ይህ መፅሀፍ .. ለፍቅር ሲባል ከአላማ ውጪ የሚደረግ ጉዞን፣ ለገንዘብ ሲባል የጣምራ ሰላይነት ሚናን፣ ከደረሰባቸው በደል የተነሳ የበቀል ፅዋን የመጎንጨት እና የተጠበቀው እንዳልተጠበቀ የሆኑና ያልሆኑ ድርጊቶች እየተፈፀሙ፣ የአከባቢን ቀልብ በመግዛት
ከመጀመርያ ገፅ አንስቶ ሚስጥሩ እስከሚፈታ የመጨረሻው ገፅ ድረስ በጉጉት የሚነበብ መፅሀፍ ነው።
#መልካም_ንባብ_ጓደኞቼ 😊
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare198
( Deep lie )
📝ትርጉም ፦
👨💼 ሙሉጌታ ይፍሩ
🤵♂ ሚሊዬን ግዛው
✅ይህ መፅሀፍ .. ለፍቅር ሲባል ከአላማ ውጪ የሚደረግ ጉዞን፣ ለገንዘብ ሲባል የጣምራ ሰላይነት ሚናን፣ ከደረሰባቸው በደል የተነሳ የበቀል ፅዋን የመጎንጨት እና የተጠበቀው እንዳልተጠበቀ የሆኑና ያልሆኑ ድርጊቶች እየተፈፀሙ፣ የአከባቢን ቀልብ በመግዛት
ከመጀመርያ ገፅ አንስቶ ሚስጥሩ እስከሚፈታ የመጨረሻው ገፅ ድረስ በጉጉት የሚነበብ መፅሀፍ ነው።
#መልካም_ንባብ_ጓደኞቼ 😊
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare198
06.05.202511:22
⇲⇲ 📖 ✘ የተራቡ ጭኖች ✘ ⇲ ⇲
❏ ❐ ✅️✅️✅️❒ ❏ ❐ ❏ ❐ ❑ ❒✅️
❈ ደራሲ ፦ ንጋቱ ክፍሌ
➠➠➠➠ ሼር ያድርጉ!! ➠➠➠➠
💠ይህ መጽሐፍ ሽብርና አክራሪነት ከኢራን ተነስቶ ያቆጠቆጠባት የሲኦል ሞት የበረታባት፣ የሴቶች ጭቆና ጣራ የነካበት፣ የፍትወተ ስጋ የእንስሳት አይነት የሚፈጸምባት፣ የስለላ መረብ የተዘረጋባት፣ ሐሺሽና ጫት በገፍ የሚወሰዱባት፣ የጎሳ ጦርነት ስለሚያምሳት ሲኦላዊት አገር ነው፡፡
💠በሚያስደንቅ ሁኔታ ሰላዮቹ መረጃን ለማግኘት ሲሉ በእምነታቸው ክልክል የሆነውን የወሲብ አይነት በባለስልጣኖች ሚስቶች ላይ በመፈጸምና በማባበል የሚፈልጉትን ከማግኘታቸውም በላይ በሌላ እቅዳቸው ማስፈጸሚያነት ይገፏፏቸዋል፡፡ ያሳኩት ይሆን?
✅️መጽሐፉ የሶማሌ፣ የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ፣ የየመንና የሌሎች አረብ ሀገሮች ሰላዮች የሚራኮቱበት፡፡ ሁሉም : አላማቸውን ለማስፈጸም የሚጥሩበት፤ አሸባሪነትንና _ የአክራሪነት ጥንስስ ተወልዶ አድጎ ሕዝቦቹን _ የሚገርፍበት፤ ነፍስ መጠፋፋት፤ መከዳዳት፣ ፍቅርን ፍለጋ የሴቶች የስሜት ጥማት መዋተትን በቀል ሴራ ጭፍጨፋ የሚካሄድባት ከመጀመሪያው ገጽ አንስቶ ልብን በማንጠልጠል መጨረሻውን _ ለማወቅ ትንፋሽን ይዞ የሚጓዝ ሁሉን ያካተተመጽሐፍ
✅️@Enmare1988
✅️✅️@Enmare1988
❏ ❐ ✅️✅️✅️❒ ❏ ❐ ❏ ❐ ❑ ❒✅️
❈ ደራሲ ፦ ንጋቱ ክፍሌ
➠➠➠➠ ሼር ያድርጉ!! ➠➠➠➠
💠ይህ መጽሐፍ ሽብርና አክራሪነት ከኢራን ተነስቶ ያቆጠቆጠባት የሲኦል ሞት የበረታባት፣ የሴቶች ጭቆና ጣራ የነካበት፣ የፍትወተ ስጋ የእንስሳት አይነት የሚፈጸምባት፣ የስለላ መረብ የተዘረጋባት፣ ሐሺሽና ጫት በገፍ የሚወሰዱባት፣ የጎሳ ጦርነት ስለሚያምሳት ሲኦላዊት አገር ነው፡፡
💠በሚያስደንቅ ሁኔታ ሰላዮቹ መረጃን ለማግኘት ሲሉ በእምነታቸው ክልክል የሆነውን የወሲብ አይነት በባለስልጣኖች ሚስቶች ላይ በመፈጸምና በማባበል የሚፈልጉትን ከማግኘታቸውም በላይ በሌላ እቅዳቸው ማስፈጸሚያነት ይገፏፏቸዋል፡፡ ያሳኩት ይሆን?
✅️መጽሐፉ የሶማሌ፣ የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ፣ የየመንና የሌሎች አረብ ሀገሮች ሰላዮች የሚራኮቱበት፡፡ ሁሉም : አላማቸውን ለማስፈጸም የሚጥሩበት፤ አሸባሪነትንና _ የአክራሪነት ጥንስስ ተወልዶ አድጎ ሕዝቦቹን _ የሚገርፍበት፤ ነፍስ መጠፋፋት፤ መከዳዳት፣ ፍቅርን ፍለጋ የሴቶች የስሜት ጥማት መዋተትን በቀል ሴራ ጭፍጨፋ የሚካሄድባት ከመጀመሪያው ገጽ አንስቶ ልብን በማንጠልጠል መጨረሻውን _ ለማወቅ ትንፋሽን ይዞ የሚጓዝ ሁሉን ያካተተመጽሐፍ
✅️@Enmare1988
✅️✅️@Enmare1988


06.05.202504:27
" ያኔ ፡ አሳ እያጠመድኩ በምሸጥበት ጊዜ ይህች ሴት ከኔ ጋር ነበረች
አንዳንዴ በመረቤ ውስጥ አንድም አሳ ሳይገባ ቀርቶ ባዶ ኪሴን ወደቤት ስመጣ ፡ በፍቅር አይን እያየችኝ ፡ አይዞህ ይሄ ሁሉ ነገር አንድ ቀን ይለወጣል አታስብ እያለች ፡ የቤት ወጭ ከምሰጣት ላይ የተረፋትን ብር ጥቅልል አድርጋ በእጄ አስጨብጣኝ ፡ ሻይ ቡና ብለህ ና ትለኛለች ።
......
አምላክ ብቻዬን እንዳልተወኝ አውቅ ዘንድ ከኔ ጋር እንድትሆን የላካት ይህች ሴት አብራኝ ባትሆን ኖሮ ፡ ዛሬ የደረስኩበት ደረጃ አልደርስም ነበር " ይላል ካርሎስ ባካ ስለ ባለቤቱና ስለ ሶስት ልጆቹ እናት Shayira Santiago ሲናገር
.....
ከአመታት በኋላ. .
ዛሬ ላይ ያ በኮሎምቢያ ጎዳናዎች ላይ የሚሸጥ አሳ ይዞ ፡ ይዞር የነበረው ይህ ሰው ፡ የአሳ መረቡን ጥሎ የእግር ኳሱን አለም ከተቀላቀለ ከጥቂት አመታት በኋላ 24 ሚሊየን ፓውንድ ሀብት በባንክ ያከማቸ በተለያዩ የአውሮፓ ክለቦች የተጫወተና ፡ በአሁኑ ወቅት የአትሌቲኮ ጁኒየር የፊት አጥቂ የሆነ ዝነኛ ተጫዋች ሆኗል ።
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
አንዳንዴ በመረቤ ውስጥ አንድም አሳ ሳይገባ ቀርቶ ባዶ ኪሴን ወደቤት ስመጣ ፡ በፍቅር አይን እያየችኝ ፡ አይዞህ ይሄ ሁሉ ነገር አንድ ቀን ይለወጣል አታስብ እያለች ፡ የቤት ወጭ ከምሰጣት ላይ የተረፋትን ብር ጥቅልል አድርጋ በእጄ አስጨብጣኝ ፡ ሻይ ቡና ብለህ ና ትለኛለች ።
......
አምላክ ብቻዬን እንዳልተወኝ አውቅ ዘንድ ከኔ ጋር እንድትሆን የላካት ይህች ሴት አብራኝ ባትሆን ኖሮ ፡ ዛሬ የደረስኩበት ደረጃ አልደርስም ነበር " ይላል ካርሎስ ባካ ስለ ባለቤቱና ስለ ሶስት ልጆቹ እናት Shayira Santiago ሲናገር
.....
ከአመታት በኋላ. .
ዛሬ ላይ ያ በኮሎምቢያ ጎዳናዎች ላይ የሚሸጥ አሳ ይዞ ፡ ይዞር የነበረው ይህ ሰው ፡ የአሳ መረቡን ጥሎ የእግር ኳሱን አለም ከተቀላቀለ ከጥቂት አመታት በኋላ 24 ሚሊየን ፓውንድ ሀብት በባንክ ያከማቸ በተለያዩ የአውሮፓ ክለቦች የተጫወተና ፡ በአሁኑ ወቅት የአትሌቲኮ ጁኒየር የፊት አጥቂ የሆነ ዝነኛ ተጫዋች ሆኗል ።
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
05.05.202514:14
✔️ኡሚ ቴክኖሎጂስ የ Digital Marketing የ ኦንላይን ስልጠና ምዝገባ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ይቀራሉ!
⚡️ ከሌላው ምን ይለየናል
👉 ባሉበት ሆነው ባመችዎት ሰዐት መከታተል የሚችሉት ስልጠና።
👉 ያለ አስተማሪ በራስዎት ፍጥነት መውሰድ የሚችሉበት አማራጭ ያካተተ።
👉ሙሉ በሙሉ በተግባር የሚሰጥ መሆኑ።
👉 ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ ከ ፕሮፌሽናል ሰርተፍኬት በተጨማሪ portfolio website የሚኖርዎት መሆኑ።
⚡️ ስልጠናው ምን ምን ያካትታል ?
✔️ Digital marketing Theories
💥 Graphics design with Canva basics
💥International payment cards
💥Shopify and WordPress website development
💥Upwork
⚡️ ስልጠናው በምን ያክል ጊዜ ይጠናቀቃል ?
With instructor:- በ 1 ወር
self-paced :- depending on your pace from 1 week to 4 weeks.
ሰልጥነው እንደጨረሱ፦
🔥Professional Certificate እና
🖥 ሰልጣኞች የሰሯቸዉን ስራዎች የሚያሳዩበት portfolio website
🌼 ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ቀድመው ይመዝገቡ!
✅ ለመመዝገብ: በአካል ወይም Umi Registration Bot
🔗 ለበለጠ መረጃ:
📞📞+251924868543
➡️ Customer Support
አድራሻ:- 22 ማዞሪያ KW ህንፃ 1ኛ ፎቅ
✨ Umi technilogies ✨
Website | Telegram | Linkdin | Telegram bot
⚡️ ከሌላው ምን ይለየናል
👉 ባሉበት ሆነው ባመችዎት ሰዐት መከታተል የሚችሉት ስልጠና።
👉 ያለ አስተማሪ በራስዎት ፍጥነት መውሰድ የሚችሉበት አማራጭ ያካተተ።
👉ሙሉ በሙሉ በተግባር የሚሰጥ መሆኑ።
👉 ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ ከ ፕሮፌሽናል ሰርተፍኬት በተጨማሪ portfolio website የሚኖርዎት መሆኑ።
⚡️ ስልጠናው ምን ምን ያካትታል ?
✔️ Digital marketing Theories
💥 Graphics design with Canva basics
💥International payment cards
💥Shopify and WordPress website development
💥Upwork
⚡️ ስልጠናው በምን ያክል ጊዜ ይጠናቀቃል ?
With instructor:- በ 1 ወር
self-paced :- depending on your pace from 1 week to 4 weeks.
ሰልጥነው እንደጨረሱ፦
🔥Professional Certificate እና
🖥 ሰልጣኞች የሰሯቸዉን ስራዎች የሚያሳዩበት portfolio website
🌼 ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ቀድመው ይመዝገቡ!
✅ ለመመዝገብ: በአካል ወይም Umi Registration Bot
🔗 ለበለጠ መረጃ:
📞📞+251924868543
➡️ Customer Support
አድራሻ:- 22 ማዞሪያ KW ህንፃ 1ኛ ፎቅ
✨ Umi technilogies ✨
Website | Telegram | Linkdin | Telegram bot


05.05.202508:50
Ads
😌😌ዛሬ ማታ ትልቅ GIVEAWAY አለ የSTAR, የTON ወይም ብር የምንሸልም ይሆናል ማንም እንዳይቀር ✌️FAMILY😌😌
#Ads
GIVEAWAY ላይ ለመሳተፍ በቅድሚያ የዚህን CHANNEL JOIN ማለት አለባችሁ 😏@UNIQUECRYPTO_24l7😮
GIVEAWAY? 🤝 @UNIQUECRYPTO_24l7 👈JOIN HERE
😌😌ዛሬ ማታ ትልቅ GIVEAWAY አለ የSTAR, የTON ወይም ብር የምንሸልም ይሆናል ማንም እንዳይቀር ✌️FAMILY😌😌
#Ads
GIVEAWAY ላይ ለመሳተፍ በቅድሚያ የዚህን CHANNEL JOIN ማለት አለባችሁ 😏@UNIQUECRYPTO_24l7😮
GIVEAWAY? 🤝 @UNIQUECRYPTO_24l7 👈JOIN HERE


04.05.202516:30
ዛሬ ደግሞ የምጠቁማችሁ ቻናል የሚገራርሙ ዓለም አቀፍ እውነታዎችን ሳይኮሎጂዎችን የሚለቅ የሚያስገርሙ ለማመን የሚከብዱ የዓለማችንን ጉዶች የምታገኙበት ትምህርት ምትቀስሙበት ምርጥ ቻናል ነው!
ቻናሉን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ንኩት
👇👇👇
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
ቤተሰብ ይሄን ሼር በማድረግ ተባበሩኝ !
ቻናሉን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ንኩት
👇👇👇
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
ቤተሰብ ይሄን ሼር በማድረግ ተባበሩኝ !
06.05.202517:12
የሆስፒታል ወግ...
የህፃናት ክፍል ተመድበን ካርድ ስናገላብጥ "አሳጥረው ሲፅፉት ከባድ ነገር አይመስልም እንደውም የሰው ስም ነው የሚመስለው አይደል?" አለቺኝ ዶክተሮቹ የፃፉት ካርድ ላይ አልነበብ ያለውን ፅሁፋቸውን ለማንበብ እየሞከረች
አየሁት የበሽታ አይነት የሚለው ላይ "SAM" ይላል severe acute malnutrition ማለት ነው በምግብ እጥረት በጣም የቀነጨረ ህፃን ማለት ነው።
"ቆይ ግን SAM ላለበት ሰው ምንድነው የሚደረገው?!" አለችው አጠገቧ ላለው ነርስ
"ያው acute malnutrition ከሆነ ቶሎ ቶሎ ምግብ እና ፈሳሽ እንሰጠዋለን በጣም severe ደረጃ ላይ ከደረሰ ግን ምግብ ትንሽ ትንሽ ነው የሚሰጠው" አላት እጁን በአልኮል እያፀዳ
"እንዴ እንደውም በደንብ የሚያስፈልገው ለባሰበት አይደለ እንዴ ጭራሽ ትንሽ እንሰጠዋለን?!" አለች ወገቧን ይዛ
"አየሽ ሰውነትሽ አንድን ነገር በጣም ፈልጎ ሲያጣ ያለሱ መኖርን መለማመድ ይጀምራል ስለዚህ ያ በጣም የተፈለገው ነገር ጠላት ይሆናል ሰውነትሽ ያለሱ ለመኖር ሲጣጣር አሰራሩ ይቀየራል ምግብን በአግባቡ ከመጠቀም በትንሽ ምግብ መኖር መለማመድ ይጀምራል
ስለዚህ ብዙ ምግብ ሲያገኝ እንደባዕድ ነገር ይቆጥረው እና ለማውጣት ሲጨነቅ ያልተጠበቀ ጉዳት ሊያመጣበት ይችላል አሁን ገባሽ" አላት
"ዋው ወይ ጉድ ሰውነታችን እኮ ሁሌም ነው የሚደንቀኝ" አለችው እና ወደ እኔ ዞራ "አይገርምም" አለቺኝ
"ቀላል እንደውም ከዘመኔ ትውልድ ጋር ተመሳሰለብኝ" አልኳት ራሴን በግርምት እየነቀነቅኩ ተመሳስሎው ገርሞኝ
"ረሀብ ላይ ስለሆንን ብለሽ ነው?!" አለች ግራ መጋባቷ ፊቷ ላይ እየተስተዋለ
"አይደለም ስለ አካላዊ ርሀብ እና መቀንጨር አይደለም እኔ የማወራው ስለ ፍቅርን እንደ ምግብ ስለተራበው ልባችን ነው የፆታዊ ብቻ ሳይሆን ሁሉም አይነት ፍቅር ነው የምልሽ እና በጣም የሚያስፈልገን ፍቅር ሆኖ acute የሆነውን ፍቅር ብናገኝ የምናልፍበትን stage አልፈን
አሁን severe love-deficit ሆነን ብቻችን መኖር ብቻችንን መደሰት ብቻችንን ማዘን ብቻችንን ከሀዘን መውጣት እየተለማመድን ሳለ ልባችን "ሰውን መውደድ" የነበረው መደበኛ ስራዋን ትታ "ብቻ መኖርን" ለመደች
አሁን ጠብታ ፍቅር ሲቀርበን ልባችን ይገፋዋል ምክንያቱም መራራቅን እንጂ መቀራረብን ረስተናል ፍቅር እንዴት መቀበል እንዳለብን እንዴት መስጠት እንዳለብን ባጠቃላይ እንዴት ፍቅርን handle ማድረግ እንዳለብን ረስተናል
ስለዚህ እንደ SAM ታካሚ ፍቅርን በጥቂት በጥቂቱ መለማመድ አለብን ምክንያቱም በብዙ የመጣ ፍቅር ለእኛ ጠላት ነው እንዴት እንደሚያዝ አናውቅበትም ለዛ እኮ ነው የቀረበንን በሙሉ ሰበብ እየፈለግን ስንርቅ የኖርነው አይገርምም መመሳሰሉ" አልኳት ጥርስ ጥርስ ሆኜ
"ለዛ እኮ ነው ነርሲንግን ትተሽ ፍልስፍና ተማሪ ስልሽ የነበረው አሁን ነይ ለልጆቹ መድሀኒታቸውን እንስጣቸው በረሀብ ሳያልቁ" አለች
የእኛንስ ልብ ማነው በትንሽ በትንሽ በትንሹ ፍቅር የሚያስለምደው??
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss
የህፃናት ክፍል ተመድበን ካርድ ስናገላብጥ "አሳጥረው ሲፅፉት ከባድ ነገር አይመስልም እንደውም የሰው ስም ነው የሚመስለው አይደል?" አለቺኝ ዶክተሮቹ የፃፉት ካርድ ላይ አልነበብ ያለውን ፅሁፋቸውን ለማንበብ እየሞከረች
አየሁት የበሽታ አይነት የሚለው ላይ "SAM" ይላል severe acute malnutrition ማለት ነው በምግብ እጥረት በጣም የቀነጨረ ህፃን ማለት ነው።
"ቆይ ግን SAM ላለበት ሰው ምንድነው የሚደረገው?!" አለችው አጠገቧ ላለው ነርስ
"ያው acute malnutrition ከሆነ ቶሎ ቶሎ ምግብ እና ፈሳሽ እንሰጠዋለን በጣም severe ደረጃ ላይ ከደረሰ ግን ምግብ ትንሽ ትንሽ ነው የሚሰጠው" አላት እጁን በአልኮል እያፀዳ
"እንዴ እንደውም በደንብ የሚያስፈልገው ለባሰበት አይደለ እንዴ ጭራሽ ትንሽ እንሰጠዋለን?!" አለች ወገቧን ይዛ
"አየሽ ሰውነትሽ አንድን ነገር በጣም ፈልጎ ሲያጣ ያለሱ መኖርን መለማመድ ይጀምራል ስለዚህ ያ በጣም የተፈለገው ነገር ጠላት ይሆናል ሰውነትሽ ያለሱ ለመኖር ሲጣጣር አሰራሩ ይቀየራል ምግብን በአግባቡ ከመጠቀም በትንሽ ምግብ መኖር መለማመድ ይጀምራል
ስለዚህ ብዙ ምግብ ሲያገኝ እንደባዕድ ነገር ይቆጥረው እና ለማውጣት ሲጨነቅ ያልተጠበቀ ጉዳት ሊያመጣበት ይችላል አሁን ገባሽ" አላት
"ዋው ወይ ጉድ ሰውነታችን እኮ ሁሌም ነው የሚደንቀኝ" አለችው እና ወደ እኔ ዞራ "አይገርምም" አለቺኝ
"ቀላል እንደውም ከዘመኔ ትውልድ ጋር ተመሳሰለብኝ" አልኳት ራሴን በግርምት እየነቀነቅኩ ተመሳስሎው ገርሞኝ
"ረሀብ ላይ ስለሆንን ብለሽ ነው?!" አለች ግራ መጋባቷ ፊቷ ላይ እየተስተዋለ
"አይደለም ስለ አካላዊ ርሀብ እና መቀንጨር አይደለም እኔ የማወራው ስለ ፍቅርን እንደ ምግብ ስለተራበው ልባችን ነው የፆታዊ ብቻ ሳይሆን ሁሉም አይነት ፍቅር ነው የምልሽ እና በጣም የሚያስፈልገን ፍቅር ሆኖ acute የሆነውን ፍቅር ብናገኝ የምናልፍበትን stage አልፈን
አሁን severe love-deficit ሆነን ብቻችን መኖር ብቻችንን መደሰት ብቻችንን ማዘን ብቻችንን ከሀዘን መውጣት እየተለማመድን ሳለ ልባችን "ሰውን መውደድ" የነበረው መደበኛ ስራዋን ትታ "ብቻ መኖርን" ለመደች
አሁን ጠብታ ፍቅር ሲቀርበን ልባችን ይገፋዋል ምክንያቱም መራራቅን እንጂ መቀራረብን ረስተናል ፍቅር እንዴት መቀበል እንዳለብን እንዴት መስጠት እንዳለብን ባጠቃላይ እንዴት ፍቅርን handle ማድረግ እንዳለብን ረስተናል
ስለዚህ እንደ SAM ታካሚ ፍቅርን በጥቂት በጥቂቱ መለማመድ አለብን ምክንያቱም በብዙ የመጣ ፍቅር ለእኛ ጠላት ነው እንዴት እንደሚያዝ አናውቅበትም ለዛ እኮ ነው የቀረበንን በሙሉ ሰበብ እየፈለግን ስንርቅ የኖርነው አይገርምም መመሳሰሉ" አልኳት ጥርስ ጥርስ ሆኜ
"ለዛ እኮ ነው ነርሲንግን ትተሽ ፍልስፍና ተማሪ ስልሽ የነበረው አሁን ነይ ለልጆቹ መድሀኒታቸውን እንስጣቸው በረሀብ ሳያልቁ" አለች
የእኛንስ ልብ ማነው በትንሽ በትንሽ በትንሹ ፍቅር የሚያስለምደው??
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss


06.05.202510:56
Ads
✅ዛሬ ማታ ትልቅ GIVEAWAY አለ የSTAR, የTON ወይም ብር የምንሸልም ይሆናል ማንም እንዳይቀር ✌️FAMILY✅
GIVEAWAY ላይ ለመሳተፍ በቅድሚያ የዚህን CHANNEL JOIN ማለት አለባችሁ 😏@UNIQUECRYPTO_24l7😮
GIVEAWAY? 🤝 @UNIQUECRYPTO_24l7 👈JOIN HERE
✅ዛሬ ማታ ትልቅ GIVEAWAY አለ የSTAR, የTON ወይም ብር የምንሸልም ይሆናል ማንም እንዳይቀር ✌️FAMILY✅
GIVEAWAY ላይ ለመሳተፍ በቅድሚያ የዚህን CHANNEL JOIN ማለት አለባችሁ 😏@UNIQUECRYPTO_24l7😮
GIVEAWAY? 🤝 @UNIQUECRYPTO_24l7 👈JOIN HERE
05.05.202519:34
ረጅም ፀሎት ኖሮኝ አያውቅም.....ይሄ በህይወት ዘመኔ የፀለይኩት ሁለተኛ ፀሎቴ ነው.....አንደኛው "እናቴን ቤቷ መልስልኝ...."....ነበር.....
ውጤቴ እስኪደርስ ከዚህ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ ዝብርቅርቅ ስሜት ተጫወተብኝ.....
የምፅአት ቀን እራሱ እንደዚህ የሚርቅ አይመስለኝም።
"እድል ሰጠኝ......".....ተጠራሁ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
ውጤቴ እስኪደርስ ከዚህ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ ዝብርቅርቅ ስሜት ተጫወተብኝ.....
የምፅአት ቀን እራሱ እንደዚህ የሚርቅ አይመስለኝም።
"እድል ሰጠኝ......".....ተጠራሁ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
Өчүрүлгөн06.05.202512:21
05.05.202513:23
👇English Grammar Rule Quiz 👇
Every sentence must have a subject and___.
Every sentence must have a subject and___.
04.05.202520:00
✨✨ፍቅር ቅብ-15✨✨
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka


04.05.202513:15
✅አዲስ የተጋቡ ጥንዶች የበፊት መኖሪያቸውን ይለቁና ሌላ ሰፈር ተከራይተው መኖር ይጀምራሉ ። አዲሱ ቤታቸው በገቡ ማግስት ጠዋት ላይ ቁጭ ብለው ቁርሳቸውን በመብላት ላይ ሳሉ ፡ ሚስትየው በመስኮቱ መስታወት በኩል ውጪውን ስትመለከት ፡ አንዲት የጎረቤት ሴት ልብስ አጥባ ስታሰጣ አየች ።
✔️ከዚያም ፊቷን ቅጭም አድርጋ ወደ ባሏ ዞረችና "ውዴ ! ልጅቷ ልብስ ማጠቡን አልቻለችበትም መሠለኝ ምንም ሳይፀዳ እስከ ቆሻሻው ነው ያሰጣችው!" አለችው ። ባሏ ግን ምንም አልመለሰላትም ፤ ፈገግ ብሎ ብቻ በዝምታ አለፈ ።
የጎረቤቷ ልጅ ሁሌ ዘውትር ጠዋት ጠዋት እየተነሳች የቤተሰቦቿን ቤት ታፀዳና ልብስ አጥባ ታሰጣለች ። አዲሶቹ ሙሽሮችም ለቁርስ በተቀመጡበት ቦታ ሆነው በመስኮታቸው መስታወት በኩል ይህን የዘውትር የጎረቤታቸውን ስራን ያያሉ ። ሚስትየውም ሁሌም "ያሰጣችው ልብስ ዛሬም አልፀዳም !" የሚለውን ትችቷን ለባሏ ትነግረዋለች ።
ባልየውም የምፀት ፈገግታ ፈገግ እያለ በዝምታ ያልፋታል ። አዲሱ ቤታቸው በገቡ በወራቸው ጠዋት ላይ እንደተለመደው ቁርሳቸውን ሲበሉ ፡ ሚስትየው በመደነቅና በመደሰት ወደ ባሏ ዞራ "ውዴ ተመልከትማ ! ጎረቤታችን ዛሬ ጎብዛለች ። ልብስ የማጠብ ልምድ አካበተች መሠለኝ ዛሬ ልብሶቹን ፅድት አድርጋ ነው አጥባ ያሰጣችው!" አለችው በደስታ እየተፍለቀለቀች ።
ዛሬ ግን ባልየው ዝም አላለም ። የምፀት ፈገግታውን እያሳያት "ዛሬኮ በለሊት ተነስቼ የቤታችንን መስኮት መስታወቶችን አፀዳሁት !" አላት !🙄 ለካ እስከዛሬ ሚስትየው በጎረቤቷ ላይ የምታቀርበው ትችት ልክ አልነበረም ።
በእውነትም ጎረቤቷ የምታሰጣው ልብስ ያልፀዳ ሆኖ ሳይሆን ፡ ሚስትየው አሻግራ የምታይበት የመስኮታቸው መስታወት ያልፀዳ በመሆኑ ነበር ልብሱን ቆሻሻ አስመስሎ ያሳያት ።
እናረጋግጥ
እና ምን ለማለት ነው፦ ሌሎች ሰዎችን ስናይ ፡ የምናየው ነገር ፡ በምናይበት መነፅር ንፁህነት ይወሰናል እንደማለት ነው !
ስለ ሌሎች ሰዎች የባህሪም ሆነ የተግባር መቆሸሽ ከማውራታችን በፊት ፡ ያንን ነገር ያየንበት የእይታ መነፅራችን ንፁህ መሆኑን !!! 🙏
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
✔️ከዚያም ፊቷን ቅጭም አድርጋ ወደ ባሏ ዞረችና "ውዴ ! ልጅቷ ልብስ ማጠቡን አልቻለችበትም መሠለኝ ምንም ሳይፀዳ እስከ ቆሻሻው ነው ያሰጣችው!" አለችው ። ባሏ ግን ምንም አልመለሰላትም ፤ ፈገግ ብሎ ብቻ በዝምታ አለፈ ።
የጎረቤቷ ልጅ ሁሌ ዘውትር ጠዋት ጠዋት እየተነሳች የቤተሰቦቿን ቤት ታፀዳና ልብስ አጥባ ታሰጣለች ። አዲሶቹ ሙሽሮችም ለቁርስ በተቀመጡበት ቦታ ሆነው በመስኮታቸው መስታወት በኩል ይህን የዘውትር የጎረቤታቸውን ስራን ያያሉ ። ሚስትየውም ሁሌም "ያሰጣችው ልብስ ዛሬም አልፀዳም !" የሚለውን ትችቷን ለባሏ ትነግረዋለች ።
ባልየውም የምፀት ፈገግታ ፈገግ እያለ በዝምታ ያልፋታል ። አዲሱ ቤታቸው በገቡ በወራቸው ጠዋት ላይ እንደተለመደው ቁርሳቸውን ሲበሉ ፡ ሚስትየው በመደነቅና በመደሰት ወደ ባሏ ዞራ "ውዴ ተመልከትማ ! ጎረቤታችን ዛሬ ጎብዛለች ። ልብስ የማጠብ ልምድ አካበተች መሠለኝ ዛሬ ልብሶቹን ፅድት አድርጋ ነው አጥባ ያሰጣችው!" አለችው በደስታ እየተፍለቀለቀች ።
ዛሬ ግን ባልየው ዝም አላለም ። የምፀት ፈገግታውን እያሳያት "ዛሬኮ በለሊት ተነስቼ የቤታችንን መስኮት መስታወቶችን አፀዳሁት !" አላት !🙄 ለካ እስከዛሬ ሚስትየው በጎረቤቷ ላይ የምታቀርበው ትችት ልክ አልነበረም ።
በእውነትም ጎረቤቷ የምታሰጣው ልብስ ያልፀዳ ሆኖ ሳይሆን ፡ ሚስትየው አሻግራ የምታይበት የመስኮታቸው መስታወት ያልፀዳ በመሆኑ ነበር ልብሱን ቆሻሻ አስመስሎ ያሳያት ።
እናረጋግጥ
እና ምን ለማለት ነው፦ ሌሎች ሰዎችን ስናይ ፡ የምናየው ነገር ፡ በምናይበት መነፅር ንፁህነት ይወሰናል እንደማለት ነው !
ስለ ሌሎች ሰዎች የባህሪም ሆነ የተግባር መቆሸሽ ከማውራታችን በፊት ፡ ያንን ነገር ያየንበት የእይታ መነፅራችን ንፁህ መሆኑን !!! 🙏
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
Өчүрүлгөн07.05.202512:47


06.05.202509:41
⭐Ads
✅Work visa
✅Student visa
✅Visit visa
✅Contact us
✔️@Classictravelandtureagency
Tg📞 +251983845700
💬whatsapp +251951392587
✅https://t.me/classictravelandtouragency
✅Work visa
✅Student visa
✅Visit visa
✅Contact us
✔️@Classictravelandtureagency
Tg📞 +251983845700
💬whatsapp +251951392587
✅https://t.me/classictravelandtouragency
05.05.202519:34
✨✨ፍቅር ቅብ-16✨✨
ዮናስ ደጄን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ መመንመን የጀመርኩ መሰለኝ.....ጉንጮቼ በሁለት ቀን የሰመጡ አጥንቶቼም የተንኮታኮቱ ...ፀጉሬ ሳልነካው ተነቅሎ ያለቀ አይኔም ያለመነፅር አሻፈረኝ የሚል መሰለኝ....ከበሽታ በላይ እርጅና ተሰማኝ....
ምግብ የሚባል እምቢ አለኝ....በትግል የበላሁትም ወዲያው ይወጣል....አኳሀኔ የታመመም....ያረገዘም.....ያረጀም ሰው አይነት ነበር.....
የመክብብ ጓደኛ ጋር መሄድ አልፈለግኩም....ምንም ቢሆን የመክብብ ጓደኛ ነው....ዛሬ እንደታማሚ በቅንነት ቢያነጋግረኝ ነገ ላይ የመክብብ የሆነ ነገር ሆኜ ቢያየኝ ጣቱን ለመቀሰር አንደኛ ነው.....
ምንም ባደርግ ሊለቀኝ ያልቻለው መክብብ ላይ ያለኝ ተስፋ ነው....እንዲህ ነው ብሎ አፍ አውጥቶ አልነገረኝ ነገር.....ፍቅር ይኑርበት ሀዘኔታ በውል አለየሁት ነገር....ነገ ኖረም አልኖረም ግን ውስጤ የሚጠነቀቅለት ብቸኛው ሰው ነው....
*****
"ከባለቤቴ ጋር ስንተዋወቅ ጀምሮ ቫይረሱ ነበረበት....አልነገረኝም.....እንኳን ይሄ ቫይረስ ጉንፋን አሞት የሚያውቅም አይመስልም ነበር....በጣም እንደሚወደኝ በአስር ጣቴ የምፈርምለት ሰው ነበር....ወደ አልጋ ሲገፋኝ በጄ አላልኩትም ነበር.....እንደሚወደኝ እና ከኔ ሌላ ማግባት እንደማይፈልግ ....ከኔ ሌላ ማንንም እንደማያልም እያለቀሰ ነገረኝ.....ትዝ ይለኛል አለቃቀሱ....ያሳሳ ነበር....ግን ስላለቀሰ አልነበረም ያመንኩት.....እንዲሁ ዝም ብዬ ነው ያመንኩት....
ከሱ ጋር በተኛሁ ማግስት ህዳር ሚካኤል ነበር......ሌላ ጊዜ ማህሌት አድሬ ቅዳሴን አስቀድሼ እስኪያልበኝ የምዘምረው ልጅ አዳሩን እስኪያልበኝ ባለግኩ.....
የሆነ አፋፍ ላይ ቆሜ በርቀት ታቦት ሸኘሁ.....በርቀት አለቀስኩበት....
ቀናት ወራትን ሲወልዱ በእንባ ተለምኜ የሰጠሁትን ገና ሲጠጋኝ ማቀበል ጀመርኩ....ሀጥያት ሲለመድ ፅድቅ ይመስላል...ማፈር ስናቆም ውድቀታችን "ሀ" ብሎ ይጀምራል.....
"ሀ" አልኩኝ....
ልክ ያልሆነ ስራ እየሰራሽ የሚሰማሽ ልክነት ካለ አእምሮሽ ሚዛኑን እየሳተ ነው.....የሰው ልጅ ይለምዳል.....ደግነትንም ክፋትንም....ሀጥያትንም ፅድቅንም....ጉብዝናንም ስንፍናንም.....መልበስንም መራቆትንም....ማግኘትንም ማጣትንም.....ቤተ እምነቱንም ክለቡንም.....ሁሉንም ይለምዳል.....
ጭንቅላት ሞኝም ብልጥም ነው....ያስብልሻልም አያስብልሽምም......ያስለመድሽውን ይለምዳል.....ስታስቀሪበት እንደራበው ህፃን ልጅ ያጣድፍሻል.....ጭንቅላት ባለጌም ጨዋም ነው.....ሁሉንም ይለምዳል.....ጭንቅላት የልብ ወዳጅ ነው አይገምትሽም.....ጭንቅላት ከአባት ገዳይ የከፋ ጨካኝም ነው.....ሲበቃው በቃው ነው።
ባለቤቴ እንክርዳድ የሌለበት ስንዴ ነበረ....የተለቀመ ስንዴ.....እንዲህ ነው ብለሽ እንከን የማታወጪለት አይነት ሰው.....
ከሰጠኝ በሽታ በላይ የሄደበት መንገድ አቆሰለኝ....የሞኝ ውሳኔ ቢሆንም ቫይረሱ እንዳለበት ቢነግረኝ እንደማልተወው ነው የምነግርሽ.....ይሄ ለኔ ልክ ያልሆነ ልክነት ነው.....አልተወውም ነበር....የሄደበት አቋራጭ መንገድ ግን እኔን በአካል ሰጥቶ በመንፈስ ነጠቀው......
ምክንያቱ "እወድሻለሁ" ነበር....ውስጠ ምስጢሩ ጎን ራስ ወዳድነት ነበር....አይገርምም ሁሉም ለራሱ ነው....ሲወድሽ እራሱ ለራሱ ነው....ላንቺ ብሎ የሚወድሽ አምላክሽ ብቻ ነው።
በሽታውን ሲሰጠኝ አስቦበት እንደነበር ሲነግረኝ አላፈረም....ምናል ባይነግረኝ.....ሁሉም መነገር የለበትም አይደል.....ምናል ድንገት ስሜታዊ ሆኜ ምናምን ቢለኝ....."ይሄን በሽታ ካሲያዝኳት ጥላኝ አትሄድም ብዬ ነው ያደረግኩት....ደሞም ልክ ነበርኩ አልሄድሽም.....".....ነበር ያለኝ.....ሞኝ ሆኖ እንጂ ሄጃለሁ....".....አለችኝ እና መጣሁ ያለ እንባዋን በአውራ ጣቷ ወደጎን አሽቀነጠረችው......ልመረመር ከሄድኩበት ክሊኒክ ህመምተኛ መቀበያ ወንበር ላይ የተቀመጠች ጎልማሳ ሴት ታሪክ ነው.....
"ሰው ሲከፋው ከድንጋይ ጋርም ያወራል...."....አለችኝ በትኩረት እያየችኝ.....መገረሜ በታሪኳ ብቻ ሳይሆን እንዴት ዘርግፋ ነገረችኝ በሚለውም ስለነበር ማስተዋሏ ገረመኝ።
ከሰፈር በጣም ርቄ የሄድኩበት ክሊኒክ ነው....ከሰፈር መራቄ ሀፍረቴን የሚቀንስልኝ መስሎኝ ነበር....አልቀነሰም።
"እድል ሰጠኝ....."......ስሜ ከውስጥ ተጠራ.....
እንደስሜ እድል እንዲሰጠኝ እየተመኘሁ ወደውስጥ ዘለቅኩ።
ከዶክተሩ ጋር አንድ አንድ አንድ ነገር ተነጋገርንና ሌላም ምርመራ ጨምሮ ወደ ላብራቶሪ ክፍል ላከኝ....
ላብራትሪስቷ ደሜን ቀዳች......የገላመጠችኝ መሰለኝ.....ለነገሩ በሶስት ታክሲ ስመጣ ሶስተኛው ታክሲ ውስጥ ጋቢና የተቀመጠው ሰውዬ ራሱ አስተያየቱ ስራዬን እንደሚያውቅ ነገር ነው....ከታክሲ ስወርድ ያየኃቸው አሮጊት አይነ ውሀቸው አላማረኝም....የክልኒኳ ፅዳት ሰራተኛ በምታፀዳው መሬት ፈንታ እኔን ብታፀዳኝ ደስ እንደሚላት አይኗ ነግሮኛል....ዶክተሩም ስራ ሆኖበት ነው.....
አባዬ ደወለ....ባነሳው "አንቺ ባለጌ...." የሚለኝ መሰለኝ....አላነሳሁትም....
የራሴን ስሜት ሰው ሁሉ ላይ እያየሁት ስሸበር ወጣ ብዬ ተነፈስኩ...."ተረጋጊ እድል ማንም አያውቅም ተረጋጊ.....".....አልኩኝና የቅድሟን ሴትዮ ጥዬ ወደመጣሁበት ወንበር አመራሁ.....የለችም።
ተመልሼ ወጥቼ ሰማዩ ላይ አፈጠጥኩበት.....ደመና ነበር....ወደላይ አንጋጥጬ "አደራህን አምላኬ አደራህን" አልኩት.....
ዮናስ ደጄን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ መመንመን የጀመርኩ መሰለኝ.....ጉንጮቼ በሁለት ቀን የሰመጡ አጥንቶቼም የተንኮታኮቱ ...ፀጉሬ ሳልነካው ተነቅሎ ያለቀ አይኔም ያለመነፅር አሻፈረኝ የሚል መሰለኝ....ከበሽታ በላይ እርጅና ተሰማኝ....
ምግብ የሚባል እምቢ አለኝ....በትግል የበላሁትም ወዲያው ይወጣል....አኳሀኔ የታመመም....ያረገዘም.....ያረጀም ሰው አይነት ነበር.....
የመክብብ ጓደኛ ጋር መሄድ አልፈለግኩም....ምንም ቢሆን የመክብብ ጓደኛ ነው....ዛሬ እንደታማሚ በቅንነት ቢያነጋግረኝ ነገ ላይ የመክብብ የሆነ ነገር ሆኜ ቢያየኝ ጣቱን ለመቀሰር አንደኛ ነው.....
ምንም ባደርግ ሊለቀኝ ያልቻለው መክብብ ላይ ያለኝ ተስፋ ነው....እንዲህ ነው ብሎ አፍ አውጥቶ አልነገረኝ ነገር.....ፍቅር ይኑርበት ሀዘኔታ በውል አለየሁት ነገር....ነገ ኖረም አልኖረም ግን ውስጤ የሚጠነቀቅለት ብቸኛው ሰው ነው....
*****
"ከባለቤቴ ጋር ስንተዋወቅ ጀምሮ ቫይረሱ ነበረበት....አልነገረኝም.....እንኳን ይሄ ቫይረስ ጉንፋን አሞት የሚያውቅም አይመስልም ነበር....በጣም እንደሚወደኝ በአስር ጣቴ የምፈርምለት ሰው ነበር....ወደ አልጋ ሲገፋኝ በጄ አላልኩትም ነበር.....እንደሚወደኝ እና ከኔ ሌላ ማግባት እንደማይፈልግ ....ከኔ ሌላ ማንንም እንደማያልም እያለቀሰ ነገረኝ.....ትዝ ይለኛል አለቃቀሱ....ያሳሳ ነበር....ግን ስላለቀሰ አልነበረም ያመንኩት.....እንዲሁ ዝም ብዬ ነው ያመንኩት....
ከሱ ጋር በተኛሁ ማግስት ህዳር ሚካኤል ነበር......ሌላ ጊዜ ማህሌት አድሬ ቅዳሴን አስቀድሼ እስኪያልበኝ የምዘምረው ልጅ አዳሩን እስኪያልበኝ ባለግኩ.....
የሆነ አፋፍ ላይ ቆሜ በርቀት ታቦት ሸኘሁ.....በርቀት አለቀስኩበት....
ቀናት ወራትን ሲወልዱ በእንባ ተለምኜ የሰጠሁትን ገና ሲጠጋኝ ማቀበል ጀመርኩ....ሀጥያት ሲለመድ ፅድቅ ይመስላል...ማፈር ስናቆም ውድቀታችን "ሀ" ብሎ ይጀምራል.....
"ሀ" አልኩኝ....
ልክ ያልሆነ ስራ እየሰራሽ የሚሰማሽ ልክነት ካለ አእምሮሽ ሚዛኑን እየሳተ ነው.....የሰው ልጅ ይለምዳል.....ደግነትንም ክፋትንም....ሀጥያትንም ፅድቅንም....ጉብዝናንም ስንፍናንም.....መልበስንም መራቆትንም....ማግኘትንም ማጣትንም.....ቤተ እምነቱንም ክለቡንም.....ሁሉንም ይለምዳል.....
ጭንቅላት ሞኝም ብልጥም ነው....ያስብልሻልም አያስብልሽምም......ያስለመድሽውን ይለምዳል.....ስታስቀሪበት እንደራበው ህፃን ልጅ ያጣድፍሻል.....ጭንቅላት ባለጌም ጨዋም ነው.....ሁሉንም ይለምዳል.....ጭንቅላት የልብ ወዳጅ ነው አይገምትሽም.....ጭንቅላት ከአባት ገዳይ የከፋ ጨካኝም ነው.....ሲበቃው በቃው ነው።
ባለቤቴ እንክርዳድ የሌለበት ስንዴ ነበረ....የተለቀመ ስንዴ.....እንዲህ ነው ብለሽ እንከን የማታወጪለት አይነት ሰው.....
ከሰጠኝ በሽታ በላይ የሄደበት መንገድ አቆሰለኝ....የሞኝ ውሳኔ ቢሆንም ቫይረሱ እንዳለበት ቢነግረኝ እንደማልተወው ነው የምነግርሽ.....ይሄ ለኔ ልክ ያልሆነ ልክነት ነው.....አልተወውም ነበር....የሄደበት አቋራጭ መንገድ ግን እኔን በአካል ሰጥቶ በመንፈስ ነጠቀው......
ምክንያቱ "እወድሻለሁ" ነበር....ውስጠ ምስጢሩ ጎን ራስ ወዳድነት ነበር....አይገርምም ሁሉም ለራሱ ነው....ሲወድሽ እራሱ ለራሱ ነው....ላንቺ ብሎ የሚወድሽ አምላክሽ ብቻ ነው።
በሽታውን ሲሰጠኝ አስቦበት እንደነበር ሲነግረኝ አላፈረም....ምናል ባይነግረኝ.....ሁሉም መነገር የለበትም አይደል.....ምናል ድንገት ስሜታዊ ሆኜ ምናምን ቢለኝ....."ይሄን በሽታ ካሲያዝኳት ጥላኝ አትሄድም ብዬ ነው ያደረግኩት....ደሞም ልክ ነበርኩ አልሄድሽም.....".....ነበር ያለኝ.....ሞኝ ሆኖ እንጂ ሄጃለሁ....".....አለችኝ እና መጣሁ ያለ እንባዋን በአውራ ጣቷ ወደጎን አሽቀነጠረችው......ልመረመር ከሄድኩበት ክሊኒክ ህመምተኛ መቀበያ ወንበር ላይ የተቀመጠች ጎልማሳ ሴት ታሪክ ነው.....
"ሰው ሲከፋው ከድንጋይ ጋርም ያወራል...."....አለችኝ በትኩረት እያየችኝ.....መገረሜ በታሪኳ ብቻ ሳይሆን እንዴት ዘርግፋ ነገረችኝ በሚለውም ስለነበር ማስተዋሏ ገረመኝ።
ከሰፈር በጣም ርቄ የሄድኩበት ክሊኒክ ነው....ከሰፈር መራቄ ሀፍረቴን የሚቀንስልኝ መስሎኝ ነበር....አልቀነሰም።
"እድል ሰጠኝ....."......ስሜ ከውስጥ ተጠራ.....
እንደስሜ እድል እንዲሰጠኝ እየተመኘሁ ወደውስጥ ዘለቅኩ።
ከዶክተሩ ጋር አንድ አንድ አንድ ነገር ተነጋገርንና ሌላም ምርመራ ጨምሮ ወደ ላብራቶሪ ክፍል ላከኝ....
ላብራትሪስቷ ደሜን ቀዳች......የገላመጠችኝ መሰለኝ.....ለነገሩ በሶስት ታክሲ ስመጣ ሶስተኛው ታክሲ ውስጥ ጋቢና የተቀመጠው ሰውዬ ራሱ አስተያየቱ ስራዬን እንደሚያውቅ ነገር ነው....ከታክሲ ስወርድ ያየኃቸው አሮጊት አይነ ውሀቸው አላማረኝም....የክልኒኳ ፅዳት ሰራተኛ በምታፀዳው መሬት ፈንታ እኔን ብታፀዳኝ ደስ እንደሚላት አይኗ ነግሮኛል....ዶክተሩም ስራ ሆኖበት ነው.....
አባዬ ደወለ....ባነሳው "አንቺ ባለጌ...." የሚለኝ መሰለኝ....አላነሳሁትም....
የራሴን ስሜት ሰው ሁሉ ላይ እያየሁት ስሸበር ወጣ ብዬ ተነፈስኩ...."ተረጋጊ እድል ማንም አያውቅም ተረጋጊ.....".....አልኩኝና የቅድሟን ሴትዮ ጥዬ ወደመጣሁበት ወንበር አመራሁ.....የለችም።
ተመልሼ ወጥቼ ሰማዩ ላይ አፈጠጥኩበት.....ደመና ነበር....ወደላይ አንጋጥጬ "አደራህን አምላኬ አደራህን" አልኩት.....


05.05.202510:47
የእድሜያችን ጉዳይ!
(“ምርጫና ውሳኔ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ ታሪክ)
☑️ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን በጀመርኩባት በመጀመሪያዋ ቀን ፕሮፌሰራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን ካስተዋወቀ በኋላ፣ እኛም በተራችን ሁላችንም እርስ በርሳችን እንድንተዋወቅ አበረታታን፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ የምተዋወቀውን ሰው ለመፈለግ ወዲህና ወዲያ በማለት ቃኘት ሳደርግ ከጀርባዬ አንድ እጅ በስሱ ዳበስ አደረገኝ፡፡ ማን እንደነካኝ ለማየት ዘወር ስል ከፈገግታዋ የተነሳ ሁለንተናዋ የሚያበራ አንዲት ፊቷ እጅጉን የተጨማደደ በእድሜ የገፋች ሴት ነች፡፡
☑️“ መልከ መልካም ሆይ፣ እንዴት ነህ? ስሜ ሮዝ ይባላል፡፡ የሰማንያ ሰባት አመት ሴት ነኝ፡፡ እቅፍ አድርጌ ሰላም ልልህ እችላለሁ?” በማለት ያልጠበኩትን ሰላምታ አቀረበችልኝ፡፡
☑️ ፈገግ ካልኩኝ በኋላ በታላቅ ጉጉት፣ “በሚገባ” አልኳት፡፡ እቅፍ አድርጋ ሰላም ካለችኝ በኋላ ጊዜ ሳላባክን አንድ ጥያቄ አቀረብኩላት፡፡
“ለምንድን ነው በዚህ ለጋና የዋህ እድሜሽ ዩኒቨርሲቲ ለመማር የመጣሽው?” በማለት ቀለድኳት፡፡
እርሷም በቀልድ፣ “እዚህ የመጣሁት ሃብታም ባል ባገኝ ላገባውና ሁለት ልጆች ለመውለድ ነው” አለችኝ፡፡
“እየቀለድኩኝ እኮ አይደለም” አልኳት፣ በዚህ እድሜዋ ለትምህርት ያነሳሳት ምን እንደሆነ ለማወቅ ፍላጎት ስላደረብኝ፡፡
“ሁል ጊዜ የኮሌጅ ዲግሪ እንዲኖረኝ ሕልሙ ነበረኝ፣ አሁን ጊዜው ደርሶ ይኸው ዲግሪዬን ልይዝ ነው” አለችኝ፡፡
☑️ ክፍለ ጊዜው ካለቀ በኋላ ወደ ተማሪዎች መዝናኛው ሕንጻው አቅጣጫ በቀስታ እየተራመድን የሚጠጣ ነገር ተገባበዝን፡፡ ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት ከትምህርት ሰዓት በኋላ አብረን በማሳለፍ እንነጋገር ነበር፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ያካፈለችኝ በእድሜ ያገኘችው ጥበብና ልምምዷ እጅግ አስገራሚ ነበር፡፡
በቀጣዮቹ አመታት ሮዝ የትምህርት ቤቱ ታዋቂ ሴት ወደ መሆን መጣች፡፡ በሄደችበት ቦታ ሁሉ በቀላሉ ወዳጆችን ታፈራ ነበር፡፡ ዝንጥ ብላ መልበስን ታዘወትር ነበር፡፡ ሴሚስተሩ መጨረሻ ላይ በነበረን የኳስ ጨዋታ ግብዣ ላይ ንግግር እንድታደርግ ጋበዝናት፡፡ ወደ መድረኩ ተጋብዛ ንግግር ስታደርግ ያስተማረችንን በፍጹም አልዘነጋውም፡፡
“መጫወት የምናቆመው በእድሜ ስላረጀን አይደለም፣ መጫወት ስላቆምን ነው የምናረጀው፡፡ ደስተኞችና ስኬታማዎች መሆን ከፈለጋችሁ፣ ምስጢራቱ ግልጽ ናቸው፡፡ በየቀኑ የሚያስቅ ነገር ፈልጋችሁ ማግኘት አለባችሁ፡፡ የምትከታተሉት ሕልም ሊኖራችሁ ይገባል፣ ምክንያቱም ሕልማችሁን ስታጡ ትሞታላችሁ፡፡ በዙሪያችን በርካታ ሰዎች ሞተው እንኳን እንደሞቱ አልገባቸውም፡፡ በማርጀትና በማደግ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ፡፡ የአስራ ዘጠኝ አመት ወጣት ሆነህ አመቱን ሙሉ ምንም ሳትሰራ በአልጋ ላይ ካሳለፍክ ሃያ አመት ወደ መሆን መምጣትህ አይቀርም፡፡ እኔ ደግሞ ሰማንያ ሰባት ዓመቴ ሆኖ አመቱን ሙሉ በአልጋዬ ላይ ባሳልፍ፣ ሰማንያ ስምንት ወደመሆን መምጣቴ አይቀርም፡፡
በአድሜ መግፋት ለሁሉም የተሰጠ እውነታ ነው፡፡ እድሜን መቁጠር ምንም አይነት ልዩ ስጦታና ችሎታ አይጠይቅም፡፡ ለማለት የፈለኩት በሚከናወኑት የሕይወት ለውጦች ውስጥ ሁሉ ያለንን እድል በመጠቀም ማደግ ይኖርብናል ነው፡፡ እኛ በእድሜ የገፋን ሰዎች ያለፈውን ሕይወታችንን አስመልክቶ በአብዛኛው የሚኖርብን ጸጸት ስላደረግናቸው ነገሮች ሳይሆን ስላላደረግናቸው ነገሮች ነው፡፡ ማርጀትንና መሞትን የሚፈሩ ሰዎች ብዙ ጸጸት ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡
በዲግሪ በተመረቀች በአንድ ሳምንት ውስጥ ሮዝ በሰላም ከዚህ አለም ተሰናበተች፡፡ በቀብር ስነስርአቷ ላይ የተገኘን ተማሪዎች በሙሉ፣ መሆንና ማድረግ የምንፈልገው ደረጃ ለመድረስ ከፈለግን በማንኛውም ጊዜ ያንን ማድረግ እንደምንችል ስናስታውስ ዋልን፡፡
ዶክተር እዮብ ማሞ
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988
(“ምርጫና ውሳኔ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ ታሪክ)
☑️ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን በጀመርኩባት በመጀመሪያዋ ቀን ፕሮፌሰራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን ካስተዋወቀ በኋላ፣ እኛም በተራችን ሁላችንም እርስ በርሳችን እንድንተዋወቅ አበረታታን፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ የምተዋወቀውን ሰው ለመፈለግ ወዲህና ወዲያ በማለት ቃኘት ሳደርግ ከጀርባዬ አንድ እጅ በስሱ ዳበስ አደረገኝ፡፡ ማን እንደነካኝ ለማየት ዘወር ስል ከፈገግታዋ የተነሳ ሁለንተናዋ የሚያበራ አንዲት ፊቷ እጅጉን የተጨማደደ በእድሜ የገፋች ሴት ነች፡፡
☑️“ መልከ መልካም ሆይ፣ እንዴት ነህ? ስሜ ሮዝ ይባላል፡፡ የሰማንያ ሰባት አመት ሴት ነኝ፡፡ እቅፍ አድርጌ ሰላም ልልህ እችላለሁ?” በማለት ያልጠበኩትን ሰላምታ አቀረበችልኝ፡፡
☑️ ፈገግ ካልኩኝ በኋላ በታላቅ ጉጉት፣ “በሚገባ” አልኳት፡፡ እቅፍ አድርጋ ሰላም ካለችኝ በኋላ ጊዜ ሳላባክን አንድ ጥያቄ አቀረብኩላት፡፡
“ለምንድን ነው በዚህ ለጋና የዋህ እድሜሽ ዩኒቨርሲቲ ለመማር የመጣሽው?” በማለት ቀለድኳት፡፡
እርሷም በቀልድ፣ “እዚህ የመጣሁት ሃብታም ባል ባገኝ ላገባውና ሁለት ልጆች ለመውለድ ነው” አለችኝ፡፡
“እየቀለድኩኝ እኮ አይደለም” አልኳት፣ በዚህ እድሜዋ ለትምህርት ያነሳሳት ምን እንደሆነ ለማወቅ ፍላጎት ስላደረብኝ፡፡
“ሁል ጊዜ የኮሌጅ ዲግሪ እንዲኖረኝ ሕልሙ ነበረኝ፣ አሁን ጊዜው ደርሶ ይኸው ዲግሪዬን ልይዝ ነው” አለችኝ፡፡
☑️ ክፍለ ጊዜው ካለቀ በኋላ ወደ ተማሪዎች መዝናኛው ሕንጻው አቅጣጫ በቀስታ እየተራመድን የሚጠጣ ነገር ተገባበዝን፡፡ ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት ከትምህርት ሰዓት በኋላ አብረን በማሳለፍ እንነጋገር ነበር፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ያካፈለችኝ በእድሜ ያገኘችው ጥበብና ልምምዷ እጅግ አስገራሚ ነበር፡፡
በቀጣዮቹ አመታት ሮዝ የትምህርት ቤቱ ታዋቂ ሴት ወደ መሆን መጣች፡፡ በሄደችበት ቦታ ሁሉ በቀላሉ ወዳጆችን ታፈራ ነበር፡፡ ዝንጥ ብላ መልበስን ታዘወትር ነበር፡፡ ሴሚስተሩ መጨረሻ ላይ በነበረን የኳስ ጨዋታ ግብዣ ላይ ንግግር እንድታደርግ ጋበዝናት፡፡ ወደ መድረኩ ተጋብዛ ንግግር ስታደርግ ያስተማረችንን በፍጹም አልዘነጋውም፡፡
“መጫወት የምናቆመው በእድሜ ስላረጀን አይደለም፣ መጫወት ስላቆምን ነው የምናረጀው፡፡ ደስተኞችና ስኬታማዎች መሆን ከፈለጋችሁ፣ ምስጢራቱ ግልጽ ናቸው፡፡ በየቀኑ የሚያስቅ ነገር ፈልጋችሁ ማግኘት አለባችሁ፡፡ የምትከታተሉት ሕልም ሊኖራችሁ ይገባል፣ ምክንያቱም ሕልማችሁን ስታጡ ትሞታላችሁ፡፡ በዙሪያችን በርካታ ሰዎች ሞተው እንኳን እንደሞቱ አልገባቸውም፡፡ በማርጀትና በማደግ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ፡፡ የአስራ ዘጠኝ አመት ወጣት ሆነህ አመቱን ሙሉ ምንም ሳትሰራ በአልጋ ላይ ካሳለፍክ ሃያ አመት ወደ መሆን መምጣትህ አይቀርም፡፡ እኔ ደግሞ ሰማንያ ሰባት ዓመቴ ሆኖ አመቱን ሙሉ በአልጋዬ ላይ ባሳልፍ፣ ሰማንያ ስምንት ወደመሆን መምጣቴ አይቀርም፡፡
በአድሜ መግፋት ለሁሉም የተሰጠ እውነታ ነው፡፡ እድሜን መቁጠር ምንም አይነት ልዩ ስጦታና ችሎታ አይጠይቅም፡፡ ለማለት የፈለኩት በሚከናወኑት የሕይወት ለውጦች ውስጥ ሁሉ ያለንን እድል በመጠቀም ማደግ ይኖርብናል ነው፡፡ እኛ በእድሜ የገፋን ሰዎች ያለፈውን ሕይወታችንን አስመልክቶ በአብዛኛው የሚኖርብን ጸጸት ስላደረግናቸው ነገሮች ሳይሆን ስላላደረግናቸው ነገሮች ነው፡፡ ማርጀትንና መሞትን የሚፈሩ ሰዎች ብዙ ጸጸት ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡
በዲግሪ በተመረቀች በአንድ ሳምንት ውስጥ ሮዝ በሰላም ከዚህ አለም ተሰናበተች፡፡ በቀብር ስነስርአቷ ላይ የተገኘን ተማሪዎች በሙሉ፣ መሆንና ማድረግ የምንፈልገው ደረጃ ለመድረስ ከፈለግን በማንኛውም ጊዜ ያንን ማድረግ እንደምንችል ስናስታውስ ዋልን፡፡
ዶክተር እዮብ ማሞ
➡️ @Enmare1988
➡️@Enmare1988
➡️@Enmare1988


04.05.202520:00
04.05.202511:41
✔️ኡሚ ቴክኖሎጂስ የ Digital Marketing የ ኦንላይን ስልጠና ምዝገባ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ይቀራሉ!
⚡️ ከሌላው ምን ይለየናል
👉 ባሉበት ሆነው ባመችዎት ሰዐት መከታተል የሚችሉት ስልጠና።
👉 ያለ አስተማሪ በራስዎት ፍጥነት መውሰድ የሚችሉበት አማራጭ ያካተተ።
👉ሙሉ በሙሉ በተግባር የሚሰጥ መሆኑ።
👉 ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ ከ ፕሮፌሽናል ሰርተፍኬት በተጨማሪ portfolio website የሚኖርዎት መሆኑ።
⚡️ ስልጠናው ምን ምን ያካትታል ?
✔️ Digital marketing Theories
💥 Graphics design with Canva basics
💥International payment cards
💥Shopify and WordPress website development
💥Upwork
⚡️ ስልጠናው በምን ያክል ጊዜ ይጠናቀቃል ?
With instructor:- በ 1 ወር
self-paced :- depending on your pace from 1 week to 4 weeks.
ሰልጥነው እንደጨረሱ፦
🔥Professional Certificate እና
🖥 ሰልጣኞች የሰሯቸዉን ስራዎች የሚያሳዩበት portfolio website
🌼 ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ቀድመው ይመዝገቡ!
✅ ለመመዝገብ: በአካል ወይም Umi Registration Bot
🔗 ለበለጠ መረጃ:
📞📞+251924868543
➡️ Customer Support
አድራሻ:- 22 ማዞሪያ KW ህንፃ 1ኛ ፎቅ
✨ Umi technilogies ✨
Website | Telegram | Linkdin | Telegram bot
⚡️ ከሌላው ምን ይለየናል
👉 ባሉበት ሆነው ባመችዎት ሰዐት መከታተል የሚችሉት ስልጠና።
👉 ያለ አስተማሪ በራስዎት ፍጥነት መውሰድ የሚችሉበት አማራጭ ያካተተ።
👉ሙሉ በሙሉ በተግባር የሚሰጥ መሆኑ።
👉 ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ ከ ፕሮፌሽናል ሰርተፍኬት በተጨማሪ portfolio website የሚኖርዎት መሆኑ።
⚡️ ስልጠናው ምን ምን ያካትታል ?
✔️ Digital marketing Theories
💥 Graphics design with Canva basics
💥International payment cards
💥Shopify and WordPress website development
💥Upwork
⚡️ ስልጠናው በምን ያክል ጊዜ ይጠናቀቃል ?
With instructor:- በ 1 ወር
self-paced :- depending on your pace from 1 week to 4 weeks.
ሰልጥነው እንደጨረሱ፦
🔥Professional Certificate እና
🖥 ሰልጣኞች የሰሯቸዉን ስራዎች የሚያሳዩበት portfolio website
🌼 ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ቀድመው ይመዝገቡ!
✅ ለመመዝገብ: በአካል ወይም Umi Registration Bot
🔗 ለበለጠ መረጃ:
📞📞+251924868543
➡️ Customer Support
አድራሻ:- 22 ማዞሪያ KW ህንፃ 1ኛ ፎቅ
✨ Umi technilogies ✨
Website | Telegram | Linkdin | Telegram bot
Көрсөтүлдү 1 - 24 ичинде 1 286
Көбүрөөк функцияларды ачуу үчүн кириңиз.