Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
ከእለታት....📖📚📖📚📖📚 avatar

ከእለታት....📖📚📖📚📖📚

ለአስተያየታችሁ @Shedorka
TGlist рейтинг
0
0
ТипАчык
Текшерүү
Текшерилбеген
Ишенимдүүлүк
Ишенимсиз
Орду
ТилиБашка
Канал түзүлгөн датаБер 18, 2023
TGlistке кошулган дата
Серп 22, 2024
Тиркелген топ

Telegram каналы ከእለታት....📖📚📖📚📖📚 статистикасы

Катталгандар

9 879

24 саат
6
0.1%Жума
84
0.9%Ай
488
5.2%

Цитация индекси

0

Эскерүүлөр2Каналдарда бөлүштү0Каналдарда эскерүүлөр2

1 посттун орточо көрүүлөрү

989

12 саат989
1.7%
24 саат989
1.7%
48 саат972
35.9%

Катышуу (ER)

2.78%

Кайра посттошту9Комментарийлер0Реакциялар75

Көрүүлөр боюнча катышуу (ERR)

0%

24 саат0%Жума
4.86%
Ай
2.58%

1 жарнама посттун орточо көрүүлөрү

989

1 саат31231.55%1 – 4 саат15515.67%4 - 24 саат18118.3%
Биздин ботту каналыңызга кошуп, анын аудиториясынын жынысын билүү.
Акыркы 24 саатта бардык посттор
3
Динамика
3

"ከእለታት....📖📚📖📚📖📚" тобундагы акыркы жазуулар

✨✨ፍቅር ቅብ...3✨✨



"በናትሽ ሀኒ አትቀልጂ...ጭንቅ ብሎኛል..."...ስላት የማያባራ የመሰለኝ ሳቋን ባንዴ ቁርጥ አደረገችውና ማውራት ጀመረች...


"ይኧውልሽ ዮናስ ትዳር በትክክል ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቀው ነገር የለም...'ለምን ማግባት ፈለግክ' ተብሎ ሲጠየቅ ውስጡ ቢመልስ ኖሮ መልሱ 'የአልጋ ላይ ቡጊ ቡጊን የመሰለ ምን አለ...ያለ ገደብ እሱን ለማስነካት ነው' ነበር የሚሆነው..ግን የሚመልሰው አፉ ነው...'ስለምወድሽ ስለማፈቅርሽ...ማሬ ቅብርጥሴ' እያለ ይጠግርሻል....አይንሽን ክፈቺ...ከቃላቱ በላይ ድርጊቱን እይው...ላንቺም ቢሆን በባዶ ሆድ ነጋ ጠባ አልጋ ላይ መጨፈሩ ጥሩ አይደለም...u know energy የሚባል ነገር አለ...በባዶ ሆድ ስራ ካካካካካ...."...የተለመደው ሳቋን አስከተለች።


እኔ ውስጤ በጥያቄ መራወጥ ጀመረ...
ስራ ላይ የሌለ ትዕግስት ለኔ ከየት መጣ...ለሌላ ሰው የሌለው አክብሮት ለእኔ ከየት ተፈበረከ....የሚበላው አጥቶ እርሱን ለሚለምን ህፃን የሌለ ርህራሄ ለእኔ ከወዴት ተገኘ....?....በጥያቄ ታጨቅኩ....



****


ሶስት ቀን ከሞላው የልብ ካልሆነ ኩርፊያ በኃላ የሉሲ እኩያ የሚመስል ካፌ ቀጠረኝ...ዛሬ ስለዚህ ግንኙነት በግልፅ ላወራው ነበር ሀሳቤ....በአልጋ ላይ ትርኢት እና በውብ ቃላቶች ብቻ የታጀበው ግንኙነት እንዲያበቃ አልያም መስመር እንዲይዝ...


"እድሌ..."


"እድልክ አይደለሁም...እድል ካልከኝ ይበቃል...."...ከዚህ አጠራሩ በኃላ ምን እንደሚከተል ስለማውቅ እየተጠነቀቅኩ ነው...በኔ ቤት።


የፈራሁት አልቀረልኝም ተጠጋኝ...ከእርሱ ሌላ ማየት እስከማልችል ድረስ ቀረበኝ...ከዛም የምወድለትን አስተያየት አየኝ...እጄን አጥብቆ ይዞ ወደራሱ ሲያስጠጋኝ አር የነካው እንጨት እንደያዝከኩ ነገር መነጨቅኩት...'ጎበዝ እድል እንዲህ ነው መጀገን' ብዬ ራሴን አበረታታው...ቢያንስ እናውራ አይባልም...?...አኩርፌ ነበር እኮ...


"እድሌ ይገባኛል አጥፍቻለሁ...በጣም እያበሳጨሁሽ እንደሆነ ይገባኛል...ግን እመኚኝ እለወጣለሁ...በቅርቡ አንድ አሪፍ ስራ አግኝቻለሁ...እንደሚሳካ አልጠራጠርም...ከዛ እንጋባለን...."


"ኧረ ጉድጓድ ግባ"....በሆዴ ነው...በአፌ ምንም አልተነፈስኩም...ግን ምናለ ትንሽ ራቅ ብሎ ቢያወራ...የትንፋሹ ሙቀት እስኪሰማኝ ድረስ ተጠግቶኛል...ከአይኑ ግጭት እንዳልወድቅ እየተጠነቀቅኩ ነው....


"አፈቅርሻለሁ...አፈቅርሻለሁ...ሌላውን እርሺው..."...ካለኝ በኃላ ገፄን ገፁ ውስጥ አገኘሁት...አላስገደደኝም...ግን አስገድዶኛል...ዝብርቅርቅ ያለ ስሜት ነው...ግራ መጋባት አለው...መወሰንም አለመወሰንም...አዎ ከዚህ በኃላ በ'አፈቅርሻለሁ' ትርክት ላለመቀጠል መወሰኔን ላውጅ ነበር አመጣጤ...በነበር ቀረ እንጂ...


"ክክክ-ክክክ".....የሆነ አጠገባችን ያለ  ሰው ጉሮሮውን ሲጠራርግ ነው ከንፈሮቻችን ወደየ ቦታቸው የተመለሱት...


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ገና ስሙ ሲጠራ ያ ለግላጋው ቁመቱ አይታወሰኝም...ከዛ ይልቅ የሚጎላብኝ የአክሱሙ ርዝመት ነው...ዘናጩ ዮናስ አእምሮዬ ውስጥ የለም...ራቁቱን ቅልብጭ ይልብኛል...


ዮናስ ሲባል ሰው ሁሉ የሚደነግጥለት መልኩ እና ጆሮ ሚጠልፈው ድምፁ ጭራሽ አይታወሰኝም...ከጠራው ቆዳው በላይ በላብ የተጠመቀ ሰውነቱ ነው የሚመጣልኝ.....ከምወድለት ድምፁ በላይ አልጋ ላይ ስንጨፍር የሚያወራቸው ትርጉም የለሽ መዘላበዶች እና ቅስቻዎች ናቸው ትውስታዎቼ....


ገና "እድሌ" ከማለቱ ከስሜ በላይ ኩርፊያዬን የሚያስረሳ አለም ውስጥ እንደሚከተኝ በስውር ስለሚነግረኝ ነው ከራሴ ጋር ትግል ውስጥ የሚጨምረኝ....የሚያንቀለቅለኝ መጨረሻዬ ሁለት በሁለት የሆነች ጎጆ ውስጥ እንደሚሆን ስለማውቅ ነው....በራሱ ሜዳ... ራሱ ፈረስ ሆኖ...ራሱ ጋሪ ሆኖ... ራሱ ነጂ ሆኖ ነው የሚሾፍረኝ...


ከባነንኩ በኃላ ተበሳጨሁ...'ለዚህ ነበር ይሄ ሁሉ ፉከራ'...ጠየቅኩ ራሴን...በቃ በቅፅበት ለምረሳው ነው እንዲህ ያዙኝ ልቀቁኝ አልኩ ደግሜ።


"ይቅርታ ከዚህ ካፌ ብዙም ሳትርቁ ፔንሲዮን አለ...."....አለ የቀሰቀሰን አስተናጋጅ...ጉሮሮ አጠራረጉ ግን ይቺን ለመናገር ብቻ አይመስልም ነበር...ነብሳቸውን ይማረውና የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ጉሮሮ እንኳን ያን ሰረቅራቃ ድምፅ ጀባ ለማለት እንደዚህ የሚጠራረግ አይመስለኝም።


"እሺ እሺ ሂሳብ አምጣልን..."....እኔ የሆነ ቦታ ለመሄድ ስጣደፍ በማወጣው ድምፅ ከአስተናጋጁ ጋር ያወራል...እኔ ሽምቅቅ እንዳልኩ አለሁ...

"የኔ ጌታ ምንም አላዘዛችሁም እኮ...."....ከማለቱ ሳቄ አመለጠኝ...አስተናጋጁም ከእኔ ጋር ተደመረ...የዮናስ ግንባር ላይ ችፍ ያለው ላብ የሀፍረት ብቻ አይመስልም...አይኑም በመደፍረስ አገዘው...ከመርበትበቱ የተነሳ ላልተጠቀምነው ነገር ቲፕ ሰጠ...ባሁኑ አልሳቅኩም ጤንነቱን ጠረጠርኩ እንጂ.....


ከካፌው ወጣንና ከእኔና እሱ ውጪ ደንበኛ ከሌለው ቁርቁዝ ካለ  ፔንሲዮን ገባን...የተለመደው እርግጫ...የተለመደውን ጭፈራ ጨፈርን....ይሄን ጭፈራ ለሳምንት ቀጠልን...እንዳይደብረኝ ብሎ የሚያደርገው ነገር ቢኖር ፖዝሽን መቀየር ብቻ ነው...ያኔ አንድ ጭፈራ የነበረው ወደ ብሄር ብሄረሰቦች ጭፈራ ይቀየራል...'በባዶ ሆድ ስራ' አለች ሀኒ...



***


✍ሸዊት



ይቀጥላል....react እያረጋችሁ






https://t.me/shewitdorka
Кайра бөлүшүлгөн:
✍ዮ_ሚን avatar
✍ዮ_ሚን
ትንሳኤውን ለትንሳኤ ያድርግልን !

@yomin1_2
I don't know why ግን dark ነገር ፃፊ ፃፊ የሚለኝ መንፈሴ ተቀስቅሷል....እንኳን ደህና መጣህ በሉትማ😁



የዛሬው dark story ይሄ ነበር....ነገ በተመሳሳይ ሰአት በሌላ dark story እንገናኝ።


ቆዩልኝ💙
"ኧረ ሙልዬ ልጅ በእንጨት አይመታም...."....ብላ ለትንሿ ልጇ የሰነዘረችውን ማማሰያ አሰጣለቻት....እናቴ ናት....ትክ ብዬ አየዋት....አይኗን በደንብ አየሁት....የምሯን ነበር....

ታዲያ እኔን ከአራተኛ ክፍል ጀምሮ በመወልወያ እንጨት የመታችኝ እኩያዋ መስያት ነበር... አልገባሽ አለኝ።


እናቴ በማማሰያ መምታት አትወድም.... 'የልብ አያደርስም' የምትለው ነገር አላት....ፍልጥ ነገር ትወዳለች....ለማገዶ የሚገዛው እንጨት ከመንደዱ በፊት እኔን ያነደኝ እንደነበር ትዝ ይለኛል....


ከቁጥጥሯ በላይ የሆነ ንዴት አለባት....አንድ ሁለቴ የምትከትፈውን ሽንኩርት ትታ እኔን ለመክተፍ ቢላ ወርውራለች....ንዴቷን 'ትናደዳለች' የሚለው ቃል አይገልፀውም.....


አኩራፊም ናት....እናቴን ማባበል ቋሚ ስራዬ ነበር....


አንድ ቀን እንደውም እሷን ለማስደሰት የጓደኞቼን የሙያ እርዳታ ጠይቄ አራት አይነት ወጥ ሰርቼ ጠበኳት.....ስትናደድ በያዘችው ነገር መምታት ይቀናታል....በያዘችው ሶስት ሊትር ጀሪካን አናቴን ስትለኝ ማንነቴ ጠፋብኝ....


"ዘይቴን ልትጨርሺ.....አምስት አይወጣ ካንቺ....እግዚኦ አቃጥለሽ ልደፊኝ....አቃጥያት ብለው ነው የላኩሽ....".....አለችኝ....ከማን እንደተላኩ የማላውቀው እኔ አንገቴን እንደቀበርኩ ተጠቅልዬ ተኛሁ....

አባቴን የምታውቀው እሷ ብቻ ናት።

የምንተኛው ከእሷ ጋር ነው...


ስተኛ ጠብቃ እኔ በምተኛበት በኩል ከቁም ሳጥኑ ጀርባ የሚገባውን ብርድ በውስጥ ልብሷ ትደፍንልኛለች....የተኛሁ መስዬ  አያታለሁ...


አልገባትም እንጂ ከብርዱ በላይ የምታሳምመኝ እሷ ነበረች....


ራስጌ እና ግርጌ ስንተኛ አትወድም....አጠገቧ ስተኛ ነው ደስ የሚላት...እንቅልፍ ከወሰዳት በኃላ በሰመመን ታቅፈኛለች....ምቾት አይሰማኝም....በውኗ አቅፋኝ አታውቅም....የማላውቃት ሴትዮ ያቀፈችኝ ይመስለኝና ሽክክ ይለኛል...ሸርተት ብዬ ከእቅፏ እወጣለሁ....


እንደምትኮራብኝ ያወቅኩት በቅርቡ ነው....ስመረቅ....ያኔ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ፈገግ ብላ ያየቺኝ....የኩራት ፊቷን ለማየት ድፍን 23 አመት ጠብቄያለሁ ብል ማን ያምነኛል....


" ከእርሱ ጋር መኖር እፈልጋለሁ....እናቴን አልፈልጋትም" ብዬ የፃፍኩትን ዲያሪ የሰፈር ሰው ለቡና በተሰበሰበበት አንብባ  'አይን ይብላሽ' ተብያለሁ....ምን አጉድላብኝ ከሰፈር ወጠጤ ጋር ለመኖር መመኘቴን አልጠየቀችኝም....

የገዛ እናቴ አደባባይ ላይ ስታሰጣኝ ማየት ሞት ነበር....በፊቷ ከንፈር ይመጡላታል....ከንፈር መጠጣ ጤፍ ይሸምትላት ይሆን እንጃ ትወደዋለች....

"አሳዳጊ የበደላት" በሚለው ትዝብት ውስጥ በዳይ መባሏን አታስተውልም።

"ባንቺ ምክንያት በረኪና ልጠጣ ነው....አይገባሽም እንዴ" ....ብዬ ቢጫውን ብልቃጥ ሳሳያት እርግት ብላ ነበር ያዳመጠችኝ....


"መጠጣት የሚፈልግ ሰው ሲወጣለት ጠብቆ ነው የሚጠጣው"....ብላ እንዴት እንደሚሞት ስትነግረኝም ተረጋግታ ነበር...

ሳይውል ሳያድር ደግሞ ደንቦችን ሰብስባ መጣች...."አንድ ልጄ ልትሞትብኝ ነው ምከሩልኝ"....ብላን ነው የመጣነው አሉ.....ደስ እያለኝ አመንኳቸው....


መካሪዎቹ እግራቸው እንደወጣ "ከቤቴ ሬሳ ቢወጣ እኔ ተጠያቂ አይደለሁም...ፖሊስ አጥቼ ነው ደንቦችን ያመጣሁት"....ብላ ደስታዬን ከአፈር ጨመረችው።


ከአንዴም ብዙ ጊዜ ልረዳት ሞከርኩ....ፍቅሯን በፊቴ የማታደርገው ለምን እንደሆነ ግን 50 አመትም ብኖር የምረዳት አልመስልሽ አለኝ...

ነገሯ ሁሉ 'አውቆ የተኛ' ሆነብኝ....ለምን ልትገለጥልኝ እንደማትፈልግ እንጃ ....እኔ ውስጥ ማንን እንደምታይ እንጃ...ለምን ጨለማ ጠብቃ እንደምትወደኝ እንጃ....



✍Shewit



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
True story😁


በቅርቡ ነው የለጠጥኩት አለች አንዷ ቲክቶክ ላይ😁....እኔም ገና ሁለት ወር የቤት ኪራይ መክፈሌ ነው....

ታድያ ተከራይነት ምን ይመስላል ብትሉኝ "መከልከል ይበዛዋል" ነው መልሴ።

እኔም በሁለት ወሬ የመጀመሪያውን ክልከላ አስተናግጃለሁ.....


"ቆጣሪ በጣም እየቆጠረብኝ ነው.... ከዚህ በኃላ በስቶቭ እንዳትሰሩ...."....የሚል ቀጭን ትዕዛዝ ከተሰጠን በኃላ እኔና ጎረቤቶቼ ሰይጣን ልጁን የሚድርበትን ሰአት ጠብቀን ድስታችንን ማንቋቋት ሆኗል ስራችን....

'እንደው ይቺህ ልጅ በፀሎት ነው ምትኖረው'....ብለው እንዳይሉኝ በሳምንት ሁለት ቀን ከእንቅልፍ በሚቀሰቅስ ጭስ ግቢውን አጥነዋለሁ....

እሳት ቶሎ አይያያዝልኝም(ነገረኛ ሰው መሆን ነበረብኝ 😁)


"ጎሽ....ቆቅ እኮ ነሽ....በሳምንት ሁለት ጊዜ በሰራሻት ሳምንት ምትቆዪ....አለች እንጂ የኔዋ ጉድ እንደው አፍሼ ማመጣው ነው ሚመስላት...ነጋ በርበሬውን ድፍት...ነጋ ሽሮውን ድፍት...ዘይቱን ግልብጥ....ወጡን ትጠጣዋለች ስልሽ....እንደው ምከሪያት...."....አከራዬ ልጃቸውን ያሙልኛል....


"ሙያ በልብ ነው"....የምትለዋን የእናቴ ተረት  በሆዴ ብዬ ለልጃቸው የምክር ቀጠሮ ሰጥቼ ወደስራዬ እሄዳለሁ....


የሆነ ነገር ከጉዳይ የማይቆጠረው ለካ ያ ነገር ሲኖረን ነው....ለምሳሌ ገንዘብ ያለው ሰው ገንዘብን ጉዳዬ ብሎ ከየት ላምጣው አይነት ጭንቀት አይጨነቅም....

እንደዛ ነው እኔም ላይ የሆነው።


"እስከ ዛሬ እንዴት 10 ከሰል በቀላሉ የማቀጣጠያ መንገዶች የሚል መፅሀፍ አልተፃፈም....ይሄ ነገር እኮ እንደ ሀገር የሚያሳስብ ጉዳይ ነው....." ምናምን እያልኩ ነው ቀኔን የምጀምረው.....


"ለክርስትና ልጅሽ አልብሺ እንጂ....ፋሲካ ደርሷል....ምን የመሰለ ቀሚስ ተሰቅሎ አይቻለሁ እዚ ወንዴ ጋር ብር ላኪና ለበአል ከድፎ ጋር ይዤው ሄዳለሁ....".... እናቴ በጠዋት ደውላ እንዲህ ስትለኝ ይሄን ሊያሰማኝ ነው ሲያቃዠኝ ያደረው ብያለሁ....... አላየችኝም እንጂ እንደ ማልቀስ ነገርም አርጎኝ ነበረ ..."እንኳን እናቴ ሞታ እንዲሁም አልቅሽ አልቅሽ ይለኛል" የሚለው ተረት ቦታውን ያገኘ መሰለኝ...."እንኳን ላኪ ተብዬ እንዲሁም አበዳሪ ጨርሻለሁ".....

"እኔ አሁን አልችልም ቀጣይ ልክልሻለሁ.....".....ያልኳት ማስታወሻ ደፍተሬን አውጥቼ የብድር ዝርዝሬን እያየሁ ነበር...

"ቱ ቱ ቱ አንቺስ አትረቢም....እንደ ልጄ ላሳድጋት ላስተምራት ብለሽ ቃል ገብተሽ....አንቺን ብሎ የክርስትና እናት....."....ታዘበችኝ።

"እንዴ ምን አደረግኩ....እንደ ልጄ ላሳድጋት የሚለው ቃልኪዳን በሀይማኖት ነው....በሀይማኖት ማሳደግንና በገንዘብ ማሳደግን አምታተነዋል".....አልኳት አፌን ሞልቼ....ከልቤ ነበር...

"ኡኡቴ ኪኪኪኪኪ ድንቄም....የኛ ሀይማኖተኛ....ለማንኛውም እኔ ራሴ ገዛላታለሁ ወደፊት ትሰጪኛለሽ.... ከኔ ራስ መች እኖደምትወርጂ አላቅም ወደ እናንተ የሚመጣ ሰው ካገኘሁ ቂቤ አንጥሬ እልክልሻለሁ ለበአል ".....ብላኝ ተሰነባበትን....ማሳረጊያውን ወደድኩት።

እናቴ ያልገባት አንድ ነገር አለ...ትምህርት መጨረስ ብቻ ከእነሱ ራስ አያወርደንም...እንደውም ክብደታችንን ጨምረን ነው የምንወዘፍባቸው.....

ስልኩን እንደዘጋሁት የአከራዬ ድምፅ ጆሮዬን ሰነፈጠኝ....

"ደግመህ እየው....ቆጣሪው ከተበላሸ ደግሞ ወስዳችሁ ስሩት....ተከራዮቼ ጨምሮ ሁላችንም በከሰል ነው ምንሰራው አልበዛም እንዴ....."....አከራዬ ጆሮ በሚሰነጥቅ ድምፅ መብራት ከሚቆጥረው ልጅ ጋር ሲያወሩ አጠገባቸው ካለ ሰው ጋር ሚያወሩ አይመስልም ነበር ....

"ኧረ በጣም አበዙት....ተረጋጉ እርሶ....".....ያለው ለሊት የሰራትን ምስር ወጥ በስቶቭ ለማሞቅ ቤተክርስትያን መሄጃ ሰአታቸውን የሚጠብቀው ጎረቤቴ ባልቻ ነበር...



ሸዊት ነበርኩ።



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
ዝግመተ ለውጥ

ከአለማየሁ ገላጋይ 🙌

በሶፊ 😃

👉👂😜 @bestletters
#ዛብሎን

ዕዝራ ካሳሁን


And this is my favorite voice record 🤌


ስሙትማ🫠🫨🫡
"እምባዬ ጠብ ሲል ያየሁት የምትናገረውን ሰምቼ ሳላበቃ ነበር። ካንተ አልጠብቅማ። አንዱ መንገደኛ ሊገለኝ ቢያስፈራራኝ አንተ እጄን ከጠመዘዝከው ጋር አላወዳድረውም።
ምክንያቱም ካንተ ሲመጣ ; እንኳን መመታትን መገልመጥን  ፈራዋለው። ከብዙ ሰዎች ስድብ ይልቅ ፤  ያንተ እኔን ስታወራኝ ድምጽህን ከፍ ማድረግ ለመከፋት በቂዬ ነው። ምክንያቱም አንተን ራሴን በማምነው ልክ አምንሀለው።
 
"እንዴት ትተሽኝ ሄድሽ?"ብለህ ጠይቀኸኛል። ልነግርህ ነው የመጣሁት። የሄድኩ 'ለት  አንተን ከማይወዱኝ ሰዎች መሀል ተቀምጠህ አየሁክ። የምትናገረውን ስሰማ ነበር  ፤ ግን አላስጨረስኩህም።
እነሱን መርጠህ እኔን እየተውከኝ መስሎኝ ነበር። ትግልህ እኔን ለማስወደድ እንደነበር ግን ዛሬ ከነዝያ ሰዎች አንዱ አብራርቶልኝ ነው የገባኝ።
ከሁለት ዓመት በፊት ፤ እዛ ክፍል ውስጥ ሁለት ደቂቃ ብቆይ ፤ ምናልባት ሕይወት እንዲህ ከራስ የገጠሙት ትግል አይሆንብኝም ነበር ይሆናል።
ካላንተ ልቤ እንዲመታ ባልታገልኩ ነበር።
ግን እይ ሴኮንዶች የሕይወቴን አቅጣጫ እንደምን እንደቀየሩት?!
አሁን እዚህ ጋር ምናገረው ነገር ምንም ለውጥ አያመጣ ይሆናል።
ግን ማወቅ ስላለብህ እነግርሀለው። የምወደውን ሰው ከነዛ ሰዎች ጋር ሲተባበር ማየት አቅቶኝ ነው ቃልህን ሳትጨርስ ሮጬ ያመለጥኩት።

ልቤን በራሴው ሀሳብ ቀጣሁት።
ይግረምህ!
አንተን ብቻ አይደለም ራሴንም ነው የገደልኩት።
ጊዜ ጌታው>>
ምን አ'ረክ? ተብሎ አይከሰስ ነገር......ጊዜን ለፍቅር ስል መታገስ አቅቶኝ የተቀጣሁትን እኔን መልሰህ ትቀጣኝ??" አለችው።

አይኑ ብቻ አይደለም ልቡም እምባን ዘራ። "ፍቅር አበባ ነው። እንደ አደይ ተናፍቆ ብቅ የሚል" ብሎ ስለሚያምን ሊከሳት አልቻለም ፤ እጇን ላልያዘበት ጊዜ""""""ጊዜን ረገመው።
  "ቢረፍድም ደርሰሻል" በጁ እጇን እንደያዘ በጆሮዋ ነገራት።


ቲና ✍️

https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
🚀 Check out our new channel! 🎉

We've created this channel especially for freshman students. Many exciting videos are coming your way, so stay tuned!

👉 Subscribe now and join our Telegram community!
https://youtube.com/@tekamineger?si=7KpY9HBAMW7zZ6S5
.
Telegram
https://t.me/tekamineger
pleas vote
Кайра бөлүшүлгөн:
🫂ሰው ሁን ከሰውም ሰው️️ avatar
🫂ሰው ሁን ከሰውም ሰው️️
CODE 1

                        አይፍቱኝ አባ

"እና ምን ታስባለህ?" ነበር ያለኝ.... በጥያቄው ተደናግጬ የምለው ጠፍቶብኝ ስደናገር "አቅመ ደካማ ነክ በቂ የሆነ የገቢ ምንጭ የለክም.... ይቺኛዋ ለዘላለሙ አርፋለች እና የቀረችውን ብታተርፍ ይሻልካል.... እኛ ጋር የተፈጠረው ስህተት ለማንም ማትናገር ከሆነ የቀረችውን ልጅ ውጪ ወስደን እናሳክማታለን" አለኝ..... እንዴት እንዳላፈረ ተገረምኩ.... አንዷን ልጄ ላይ ላደረሰው ስህተት የሌላኛዋ ልጄ ነብስ ቁማር ላይ ሲያስቀምጣት...... ንዴት ናረብኝ ተነስቼ አንባረኩበት
"እንዴት እንዲህ ትጠይቀኛለክ?? አባቷ እኮ ነኝ.... ስንት ነገር ያየሁባት ልጄ ናት:: እንዴት በቀላሉ በቃ ሞተች ስተቱ የኛ ስለሆነ ያቺኛዋን እናሳክማት ዝም በል ብለክ ትጠይቀኛለክ?? እንዴት አታፍርም? ህሊና እንዴት አይኖርክም? እንዴት በጥፋትክ እንኳን ኃላፊነት አትወስድም?" ምይዘው ምጨብጠው አጣው......እንደ እብድ አደረገኝ.... አንዷ መሞቷ ሳያንስ ሌላኛዋም እንደምትሞት ሲነግሩኝ እራስነቴን ጠላው.... ድህነቴን እረገምኩት አቅመ ቢስ መሆኔ አስጠላኝ.... ከሰው ሁሉ አነስኩኝ ሰማይ ምድሩ ዞረኝ.....ለአንድ አባት ልጆቹ ማለት አይኑ ናቸው.....የኔ አንዷ አይኔ ጠፋች ሌላኛዋም ትጠፋለች ሲሉ... ሳትጠፋ በፊት የኔ አይን የጠፋ መሰለኝ.... ሁሉም ነገር ጭልም አለብኝ ሰውየው አሁንም አልተመለሰም ከመቀመጫው ተነስቶ " ይሄ የኛ ስህተት አይደለም አላልኩም ግን በአንድ ስህተት የእድሜ ልክ ልፋቴ ከንቱ ሆኖ ሲተን ዝም ብዬ ፍትህ ይቀድማል ብዬ የምቀመጥ ሰው አይደለውም....ጥፋቱን ያደረሱትን ባለሙያዎች ተገቢውን ቅጣት ያገኛሉ.... ግን በራሴ መንገድ" ብሎ አንባረቀ በተራው...... " ሁላችሁም የእጃችሁን ታገኛላቹ" ብዬ ፎክሬ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው ።

ከክፍሉ እንደወጣው ባለቤቴ የልጇ ሞት ተነግሯት ለያዥ ለገናዥ አስቸግራ ትጮሀለች ትንሿ ልጄ አንዱን ግድግዳ ተደግፋ ታነባለች..... አንዳች ስሜት ሰውነቴን ወረረኝ እዛው እንዳሉ ጥያቸው ሆስፒታሉን ለቅቄ ወጣው.... አስፓልት ተሻግሬ ሰው ጭር ያለበት አንድ መግቢያ ፈልጌ ወዲህ ወዲያ እየተንቆራጠጥኩኝ ማሰብ ያዝኩኝ ድህነት መጥፎ ነው አባ..... ሃዘንክን እንኳን በአግባቡ እንድትወጣ ዕድል አይሰጥም..... የሞተችውን ልጄን የነብስ ዋጋ ተቀብዬ የቀረችውን ባተርፍስ ብዬ ሳስብ አባትነቴ ልቤን አቆሰለው የመጣው ይምጣ ብዬ የልጄ ጉዳዮች በህግ ብሄድ.... በየትኛው አቅሜ ጠበቃ አቆማለው.... በዛ ላይ ዳኛው ጠበቃው ጠቅላላ የገንዘብ ሰው.... እውነት ይዞ የመጣ ሳይሆን በእጁ ይዞ የመጣን የሚያስቀድሙ ስግብግብ ጭራቆች እንዴት አምኘ ተሟገቱልኝ እላለው.. የቀረችውን ልጄ አንድ ነገር ስትሆን እንዲ ያበደችው ባለቤቴ ምን ትሆንብኝ ይሆን... አባ ለአንድ አባት ለቤተሰቡ በቂ አለመሆን ትልቅ ውድቀት ነው ግን እንደኔ ደሞ የአንዷን ልጄ ሬሳ ረገጦ ሌላዋን የማትረፍ ቁማር ውስጥ የገባን አባት ምን እንደሚባል እንጃ......ነብሴን አርክሼ.... የድህነት ጅራፍ ጀርባዬን እያደማው የወንድነት ክብር ደረቴን ሰብቆ ትንፋሼን እያሳጣኝ....
አንገቴን ደፍቼ ቢሮው ገባው እና በሃሳቡ ተስማማው

ልጄን እያለቀስኩ ቀበርኳት... ለምን ሄድሽ ከሚለው ይልቅ ይቅር በይኝ በሚል ተማፅኖ ከአፈር አስገባዋት ከአንድ ሁለት ሳምንት በዋላ ትንሿን ልጅ ቃል በገቡት መሰረት አሳከሟት...
ጊዜ ባለፈ ቁጥር.... ባለቤቴ በትንሿ ልጅ እርዳታ ፊቷ እየፈካ መጣ ልጄም ቢሆን ከተደረገላት ሕክምና ሰውነቷ ደና ሆነ የኔ ግን ሁለቱንም እየጠፋ መጡ.... ገፅታዬም ሰውነቴም.... ስራዬ ሆን ብሎ ከነሱ መሸሽ ነበር.... ያለ ልክ ጭንቅላቴ ማሰብ እስኪያቆም እጠጣለው..... እንዲጠሉኝ ያልሆኑትን ሆናችሁ ብዬ እሳደባለው..... ባለቤቴ በዚህ ነው አናግረው ብላ የላከቾት አባ እኔ መኖር ሚገባኝ ሰው አደለውም.... የራሴን ስንፍና እና ፍርሃት ነው በልጄ ነብስ የቀየርኩት.... ልጅህን ለማትረፍ ነው እንዳትሉኝ.... እራሴን ለማዳን ነው ያረኩት..... በባለቤቴ አይን ያለኝን ክብር ላለማጣት.... ወልዶ ወልዶ ለሞት ከሚለው የማህበረሰብ ሀሜት ለማምለጥ.... ገፊ እየተባልኩኝ ሰው አፍ እንዳልሰደብ.... የወንድነቴን ክብር ለማትረፍ ነው ልጄን ያተረፍኳት።.....እንደው ባለቤቴ ምን ትለኝ ይሆን አንዷ ልጃችንን ያተረፍኩት የሌላኛዋን ልጄን የሰውነት መብት ገፍፌ ነው ብላት ምን ትል ይሆን? ለልጄስ የእህትሽ ነብስ ነው ባንቺ ነብስ የቀየርኩት ብላት ምን ትለኝ ይሆን??.... በነሱ አይን ለመክበር ብዬ ያደረኩት ነገር በራሴ አይን አወረደኝ ......


አሁን የመጣውት አባ ባለቤቴ እዳለችው ከእርሶ ጋር ተማክሬ ለመስተካከል አይደለም ወይም ሀጥያቴን ተናግሬ እንዲፈቱኝም አይደለም..... የልጄ ድምፅ እንቅልፍ ነስቶኛል..... እርሶ ለፈጣሪ ስለሚቀርቡ እንዲህ ብለው ይንገሩልኝ አባ..... በምድር ጠብቃት ብለክ የሰጠከኝ አባቷ የልጅቱን ነብስ ከራሱ ክብር አስበልጦ ማየት አልቻለም እና አንተው የሰማይ አባቷ ጠብቃት..... ምንም የማታውቅ የዋህ ነብስ ናትና አንተው ከልብህ አቆያት ....የምድር አባቷ ያጎደለባትን ፍቅር እና ፍትህ አንተ በቤትህ ሙላላት .....ያልተገባትን ሆናለችና የሚገባትን ስጣት" በሉት አባ ይቅር እንድትለኝ አይደለም ብቻ ነብሷን እንድትረጋጋልኝ ይንገሩት.... አባቷ ደካማ ሆኖ ነው እንጂ ለውድ ልጄ ያ ተገብቷት አይደለም.... እኔ ስራዬ ነው እስከለተ ሞቴ እራሴን ጠልቼ እና ወቅሼ እንድኖር ያደረገኝ ስራዬ ነው.... እሷ ምን በወጣት ነብሷ ይታወክ...... አባ ለሚያምኑት አምላክ ይሄን ይንገሩልኝ ....እኔ በምድር የሰራሁትን በምድርም በሰማይም ቅጣቴን እቀበላለሁ... የልጄን ነብስ ብቻ እንዲያረጋጋ ለፈጣሪ ይንገሩልኝ ...እኔ ጥፋቴ ነው አባ ይቅርብኝ አይፍቱኝ..... አይፍቱኝ አባ.....


✍️kalkidan

https://t.me/storyweaver36
🚀 Check out our new channel! 🎉

We've created this channel especially for freshman students. Many exciting videos are coming your way, so stay tuned!

👉 Subscribe now and join our Telegram community!
https://youtube.com/@tekamineger?si=7KpY9HBAMW7zZ6S5
.
Telegram
https://t.me/tekamineger
‹‹ለቀቀ››
----


እየኖርኩ ነው ብሎ ያስባል፤ ነገር ግን ተረጋግቶ መቀመጥን የማያውቅና የቁጭ ብድግ ሕይወት ነው የሚገፋው፡፡ ይቅበዘበዛል፡፡
ከእረፍቱ ይልቅ ማረፊያውን ፍለጋ በጉዞ የሚያጠፋው ጊዜ ያመዝናል፡፡ የእድሜው እኩሌታ ገመናውን ከምተከትለት ጎጆ ለመግባት መንገድ ላይ እያለፈ ነው፡፡

---------
መጀመሪያ የተከራየው ቤት አራት ኪሎ አካበቢ ነበር፡፡ በንጉሡ ጊዜ የተሰራ ትልቅና ውብ የድንጋይ ቪላ ቤት ጀርባ ጥግ ላይ፣ ከዋናው ቪላ መስሪያ በተራረፉና፣ ‹‹ከሚጣሉ›› ተብለው ከተሰበሰቡ ትርፍ የግንባታ እቃዎች እንደነገሩ ተሰርቶ የተወሸቀ የሚመስል አንድ ክፍል ሰርቪስ ቤት፡፡


ክፍሉ ጠባብ ቢሆንም በቂ ብርሃን ያገኛል፣ አንድ የኮርኒስ ተንጠልጣይ አምፖል አለችው፡፡ ቅር ያሰኘው ለደቂቃዎች ተጉዞና ግቢውን አቋርጦ ወደ ዋናው በር መግቢያ ላይ የሚያገኘው የጋራ ቁጢጥ ሽንትቤት ነው፡፡ ከርቀቱ አለመመቸቱ፡፡


አከራዩ ሁሉን ነገር አሳይቶት ሲያበቃ፣ ‹‹ለረጅም ጊዜ የሰራተኛ ክፍል የነበረ ነው፡፡ ሽንት ቤቱን ከዘበኛውና ከሰራተኛዋ ጋር ነው የምትጠቀመው›› አለው፡፡

ኪራዩ የማይጎዳ፣ ሰፈሩ መሃል ከተማና ለታክሲ አመቺ መሆኑን አይቶ ብዙ እንከኖቹን ችላ አለና እቃውን ሸክፎ ገባ፡፡

‹‹ለጊዜው ነው…ለአመት ወይ ቢበዛ ለሁለት አመት›› ብሎ ራሱን ደልሎ፡፡

በሰባተኛው ወር አከራዩ አንኳኳና፣

‹‹ ስማ፤ የኑሮ ሁኔታ እንደምታየው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ነው፡፡ ስለዚህ ኪራይ መጨመር አለብህ›› አለው፡፡
ኮተቱን ሰብስቦ ስለመሄድ እያሰበ ጭንቅላቱን በእሺታ ነቀነቀ፡፡ ምን አማራጭ አለው!

-
ለቀቀ፡፡
-

ቀጥሎ የተከራየው ቤት ባምቢስ ጀርባ ነበር፡፡

ይሄኛው ደግሞ የረጅምና ተከታታይ ሰርቪስ ቤቶች አካል የሆነ አንድ ክፍል ነበር፡፡
ከአራት ኪሎው የሚጠብ፡፡ መስኮት የሌለው፡፡ መብራት ካላበራ በቀትር የሚጨልም፡፡


አለቅጥ ዝቅ ያለውን የበሩን ጣሪያ ላለመንካት አጎንብሶ መግባት ነበረበት፡፡ በዚህ ላይ የጎረቤቱ የማያባራ የቴሌቪዥን ጩኸት እረፍት ነስቶት ነበር፡፡

አሁንም ‹‹ለጊዜው ነው እንጂ ዘልአለም አልኖርበት…›› ብሎ ራሱን አሞኝቶ መኖር ቀጠለ፡፡

አስር ወር ከመኖሩ ሰፈሩ፣ ግቢውና ቤቱ ሙሉ በሙሉ ፈርሰው የመኪና ማቆሚያ ሊሆኑ ስለመሆኑ ሰማ፡፡
-
ለቀቀ፡፡
-
ደግነቱ በዚያው ሰሞን የደረጃና የደሞዝ እድገት አገኘ፡፡
ያ ጊዜ ከሰው ኩሽና እና ግልምጫ ልላቀቅ ብሎ ኮንዶሚኒየም ማማተር ጀመረ፡፡



ከብዙ መማሰን በኋላ ስሙ መገናኛ እውነተኛ አድራሻው ግን ኮተቤ የሆነ ባለ አንድ መኝታ የኮንዶሚኒየም ቤት ተከራየ፡፡

በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ገመና ከታች፣ ባሰኘው ሰአት ገብቶ የሚወጣበትና ብቻውን የሚጠቀምበት ሽንት ቤት ያለው ቤት ስላገኘ ተደሰተ፡፡

ቅዳሜና እሁድ ረፋዱ ላይ ጠባቡ ግን የግሉ በረንዳ ላይ ቆሞ ሻዩን እየጠጣ ከታች ጥሩምባቸውን የሚያንባርቁ ሚኒባሶችን የሚያይበት ቤቱ ተስማማው፡፡


ሰፋው፡፡

ሶስት ሰው የሚያስቀምጥ ቆንጆ ሶፋ ገዛ፡፡ የመጽሐፍት መደርደሪያ አሰራ፡፡

የመዝናናትና የመረጋጋት ስሜቴን አጣጥሞ ሳይጨርስ ግን ኪራይ ጨምር ተባለ፡፡
‹‹ያው ጊዜው ነው፡፡›› አለ ባለቤቱ ትከሻውን እየሰበቀ፡፡
‹‹አንተም የምታውቀው ነው፡፡ ኑሮ እሳት ሆኗል››

-
ለቀቀ፡፡
-


አያት ገባ፡፡ ሌላ ኮንዶሚኒየም፡፡ ከከተማው የልብ ትርታ ራቅ ያለ፡፡ ከበፊቱ ጠበብ ያለ፡፡ በረንዳው አዝናንቶ የማያስቆም፡፡
እንደ ድሮው ወጥቶ ሻይ የማይጠጣበት፣ የማይንጠራራበት፡፡

ተሳቀቀ፡፡ የቤት እቃ መግዛት አቆመ፡፡

አመት ሳይሞላው የቤት ኪራይ ጨመረ፡፡
-
ለቀቀ፡፡
-

ኮዬ ፈጬ፡፡
አሁን ከከተማው ያለው ርቀት በኪሎሜትሮች የሚመተር ብቻ አልነበረም፡፡ ጊዜው ታክሲ እና ሃይገር ላይ እምሽክ ብሎ ያልቃል፡፡
ከስራ በኋላ ከጓደኞቹ ጋር ተገናኝቶ አንድ ሁለት ማለት አቁሟል፡፡
ሰው መጠየቅ፣ በሰው መጠየቅ ትቷል፡፡ ከናካቴው መኖር አቁሟል፡፡

ስራ ይውላል፤ ጀምበር ከጠለቀች በኋላ፣ ችምችም ያሉት የሰፈሩ ኮንዶሚኒየሞች በጨለማ ከተዋጡ በኋላ ቤቱ ይገባል፡፡
ጎኑ አልጋ ከመንካቱ ይነሳል፤ ስራ ይውላል….

አዙሪቱ የኑሮውን ጣእም ነጠቀው፡፡
እንደ ሰው የመኖር ፍላጎቱን ሰለበው፡፡

ኪራይ ተጨመረበት፡፡
-
ለቀቀ፡፡
-

እዚያው ኮዬ ፈጬ ከበፊቱ የሚጠብ ኮንዶሚኒየም ተከራየ፡፡ ሶፋውን ሸጦ፡፡ የኪችን ኮተቱን በግማሽ ቀንሶ፡፡ መፅሐፎቹን ለሰው አከፋፍሎ፡፡

ኪራይ ጨመረበት፡፡
-
ለቀቀ፡፡
-

አሁን የገባበት ቤት ስቱዲዮ ነው፡፡ በኮንዶሚኒየም ታሪክ ጠባቡ ስቱዲዮ ውስጥ፡፡ ያልለማው፣ ተከራይ ያልደፈረው የህንጻዎቹ ሁሉ መደምደሚያ የሆነው የኮዬ አካል ውስጥ፡፡ መብራት፣ ብልጭ ድርግም፡፡ ውሃ ሄድ እልም የሚሉበት፡፡

ሰፈሩ ብቻ ሳይሆን ሕይወቱም ከሚወደው ነገር ሁሉ የራቀ፣ ያራቀው መሰለው፡፡

ስምንት ወራት አለፉ፡፡

ከዚያ አከራዩ ደወለ፡፡
እንደነገሩ ሰላም ብሎት ሲያበቃ፣
‹‹እንግዲህ መቼም ሁሉ ነገር ሰማይ እየነካ ነው…እኛም ገና የቤቱን ክፍያ አልጨረስንም…ስለዚህ…›› ሲል አቋረጠው፡፡

‹‹አታፍሩም…!? እግዜርን አትፈሩም?! ቀለም እንኳን ያልተቀባ ቤት…ያውም እዚህ ጅብ የሚተራመስበት የሚያስፈራ ሰፈር እሺ ብዬ ብከራይ ገና አመት እንኳን ሳይሞላኝ ጨምር…በዚህ ላይ ውሃ የለ…መብራት የለ…››

አከራዩ በተራው በቁጣ አቋረጠው፡፡

‹‹ባንተ ብሶ ትቆጣለህ እንዴ…?!! ለምነህ እንጄ ለምነንህ ነው እንዴ የገባኸው…?! ማነህ ባክህ! እንደውም ቤቱን እፈልገዋለሁ…ቶሎ ልቀቅ...!›› ብሎ ጆሮው ላይ ዘጋው፡፡

--
ሳቁ እንደ ገደል ማሚቶ በጨለማውና ወናው የህንጻው ኮሪደሮች እስኪያስተጋባ ድረስ፣
‹‹ልቀቅ ነው ያልከኝ…?! .እ…ልቀቅ ?!….እለቃለሁ…እለቃለሁ…! ምን ችግር አለው እ-ለ-ቃ-ለ-ሁ!›› አለ

ከ-----ት ብሎ እየጮኸ፣ ደግሞ እየሳቀ፡፡

--
ከዚያ ምሽት በኋላ ያዩት ጎረቤቶች ሁሉ፣ በገባና በወጣ ቁጥር እንዲህ እንዲህ እያለ ብቻውን ሲያወራና ሲወራጭ ሲመለከቱ፣

‹‹ወይኔ ይሄ ልጅ ደህና ልጅ አልነበረ እንዴ? …በቃ ለቀቀ እንዴ?! ›› መባባል ጀመሩ፡፡

Рекорддор

20.04.202523:59
9.9KКатталгандар
20.03.202520:35
600Цитация индекси
28.02.202513:54
1.4K1 посттун көрүүлөрү
28.02.202510:35
1.4K1 жарнама посттун көрүүлөрү
29.03.202523:59
56.82%ER
10.09.202423:59
23.32%ERR

ከእለታት....📖📚📖📚📖📚 популярдуу жазуулары

07.04.202514:05
True story😁


በቅርቡ ነው የለጠጥኩት አለች አንዷ ቲክቶክ ላይ😁....እኔም ገና ሁለት ወር የቤት ኪራይ መክፈሌ ነው....

ታድያ ተከራይነት ምን ይመስላል ብትሉኝ "መከልከል ይበዛዋል" ነው መልሴ።

እኔም በሁለት ወሬ የመጀመሪያውን ክልከላ አስተናግጃለሁ.....


"ቆጣሪ በጣም እየቆጠረብኝ ነው.... ከዚህ በኃላ በስቶቭ እንዳትሰሩ...."....የሚል ቀጭን ትዕዛዝ ከተሰጠን በኃላ እኔና ጎረቤቶቼ ሰይጣን ልጁን የሚድርበትን ሰአት ጠብቀን ድስታችንን ማንቋቋት ሆኗል ስራችን....

'እንደው ይቺህ ልጅ በፀሎት ነው ምትኖረው'....ብለው እንዳይሉኝ በሳምንት ሁለት ቀን ከእንቅልፍ በሚቀሰቅስ ጭስ ግቢውን አጥነዋለሁ....

እሳት ቶሎ አይያያዝልኝም(ነገረኛ ሰው መሆን ነበረብኝ 😁)


"ጎሽ....ቆቅ እኮ ነሽ....በሳምንት ሁለት ጊዜ በሰራሻት ሳምንት ምትቆዪ....አለች እንጂ የኔዋ ጉድ እንደው አፍሼ ማመጣው ነው ሚመስላት...ነጋ በርበሬውን ድፍት...ነጋ ሽሮውን ድፍት...ዘይቱን ግልብጥ....ወጡን ትጠጣዋለች ስልሽ....እንደው ምከሪያት...."....አከራዬ ልጃቸውን ያሙልኛል....


"ሙያ በልብ ነው"....የምትለዋን የእናቴ ተረት  በሆዴ ብዬ ለልጃቸው የምክር ቀጠሮ ሰጥቼ ወደስራዬ እሄዳለሁ....


የሆነ ነገር ከጉዳይ የማይቆጠረው ለካ ያ ነገር ሲኖረን ነው....ለምሳሌ ገንዘብ ያለው ሰው ገንዘብን ጉዳዬ ብሎ ከየት ላምጣው አይነት ጭንቀት አይጨነቅም....

እንደዛ ነው እኔም ላይ የሆነው።


"እስከ ዛሬ እንዴት 10 ከሰል በቀላሉ የማቀጣጠያ መንገዶች የሚል መፅሀፍ አልተፃፈም....ይሄ ነገር እኮ እንደ ሀገር የሚያሳስብ ጉዳይ ነው....." ምናምን እያልኩ ነው ቀኔን የምጀምረው.....


"ለክርስትና ልጅሽ አልብሺ እንጂ....ፋሲካ ደርሷል....ምን የመሰለ ቀሚስ ተሰቅሎ አይቻለሁ እዚ ወንዴ ጋር ብር ላኪና ለበአል ከድፎ ጋር ይዤው ሄዳለሁ....".... እናቴ በጠዋት ደውላ እንዲህ ስትለኝ ይሄን ሊያሰማኝ ነው ሲያቃዠኝ ያደረው ብያለሁ....... አላየችኝም እንጂ እንደ ማልቀስ ነገርም አርጎኝ ነበረ ..."እንኳን እናቴ ሞታ እንዲሁም አልቅሽ አልቅሽ ይለኛል" የሚለው ተረት ቦታውን ያገኘ መሰለኝ...."እንኳን ላኪ ተብዬ እንዲሁም አበዳሪ ጨርሻለሁ".....

"እኔ አሁን አልችልም ቀጣይ ልክልሻለሁ.....".....ያልኳት ማስታወሻ ደፍተሬን አውጥቼ የብድር ዝርዝሬን እያየሁ ነበር...

"ቱ ቱ ቱ አንቺስ አትረቢም....እንደ ልጄ ላሳድጋት ላስተምራት ብለሽ ቃል ገብተሽ....አንቺን ብሎ የክርስትና እናት....."....ታዘበችኝ።

"እንዴ ምን አደረግኩ....እንደ ልጄ ላሳድጋት የሚለው ቃልኪዳን በሀይማኖት ነው....በሀይማኖት ማሳደግንና በገንዘብ ማሳደግን አምታተነዋል".....አልኳት አፌን ሞልቼ....ከልቤ ነበር...

"ኡኡቴ ኪኪኪኪኪ ድንቄም....የኛ ሀይማኖተኛ....ለማንኛውም እኔ ራሴ ገዛላታለሁ ወደፊት ትሰጪኛለሽ.... ከኔ ራስ መች እኖደምትወርጂ አላቅም ወደ እናንተ የሚመጣ ሰው ካገኘሁ ቂቤ አንጥሬ እልክልሻለሁ ለበአል ".....ብላኝ ተሰነባበትን....ማሳረጊያውን ወደድኩት።

እናቴ ያልገባት አንድ ነገር አለ...ትምህርት መጨረስ ብቻ ከእነሱ ራስ አያወርደንም...እንደውም ክብደታችንን ጨምረን ነው የምንወዘፍባቸው.....

ስልኩን እንደዘጋሁት የአከራዬ ድምፅ ጆሮዬን ሰነፈጠኝ....

"ደግመህ እየው....ቆጣሪው ከተበላሸ ደግሞ ወስዳችሁ ስሩት....ተከራዮቼ ጨምሮ ሁላችንም በከሰል ነው ምንሰራው አልበዛም እንዴ....."....አከራዬ ጆሮ በሚሰነጥቅ ድምፅ መብራት ከሚቆጥረው ልጅ ጋር ሲያወሩ አጠገባቸው ካለ ሰው ጋር ሚያወሩ አይመስልም ነበር ....

"ኧረ በጣም አበዙት....ተረጋጉ እርሶ....".....ያለው ለሊት የሰራትን ምስር ወጥ በስቶቭ ለማሞቅ ቤተክርስትያን መሄጃ ሰአታቸውን የሚጠብቀው ጎረቤቴ ባልቻ ነበር...



ሸዊት ነበርኩ።



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
20.04.202517:38
✨✨ፍቅር ቅብ...3✨✨



"በናትሽ ሀኒ አትቀልጂ...ጭንቅ ብሎኛል..."...ስላት የማያባራ የመሰለኝ ሳቋን ባንዴ ቁርጥ አደረገችውና ማውራት ጀመረች...


"ይኧውልሽ ዮናስ ትዳር በትክክል ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቀው ነገር የለም...'ለምን ማግባት ፈለግክ' ተብሎ ሲጠየቅ ውስጡ ቢመልስ ኖሮ መልሱ 'የአልጋ ላይ ቡጊ ቡጊን የመሰለ ምን አለ...ያለ ገደብ እሱን ለማስነካት ነው' ነበር የሚሆነው..ግን የሚመልሰው አፉ ነው...'ስለምወድሽ ስለማፈቅርሽ...ማሬ ቅብርጥሴ' እያለ ይጠግርሻል....አይንሽን ክፈቺ...ከቃላቱ በላይ ድርጊቱን እይው...ላንቺም ቢሆን በባዶ ሆድ ነጋ ጠባ አልጋ ላይ መጨፈሩ ጥሩ አይደለም...u know energy የሚባል ነገር አለ...በባዶ ሆድ ስራ ካካካካካ...."...የተለመደው ሳቋን አስከተለች።


እኔ ውስጤ በጥያቄ መራወጥ ጀመረ...
ስራ ላይ የሌለ ትዕግስት ለኔ ከየት መጣ...ለሌላ ሰው የሌለው አክብሮት ለእኔ ከየት ተፈበረከ....የሚበላው አጥቶ እርሱን ለሚለምን ህፃን የሌለ ርህራሄ ለእኔ ከወዴት ተገኘ....?....በጥያቄ ታጨቅኩ....



****


ሶስት ቀን ከሞላው የልብ ካልሆነ ኩርፊያ በኃላ የሉሲ እኩያ የሚመስል ካፌ ቀጠረኝ...ዛሬ ስለዚህ ግንኙነት በግልፅ ላወራው ነበር ሀሳቤ....በአልጋ ላይ ትርኢት እና በውብ ቃላቶች ብቻ የታጀበው ግንኙነት እንዲያበቃ አልያም መስመር እንዲይዝ...


"እድሌ..."


"እድልክ አይደለሁም...እድል ካልከኝ ይበቃል...."...ከዚህ አጠራሩ በኃላ ምን እንደሚከተል ስለማውቅ እየተጠነቀቅኩ ነው...በኔ ቤት።


የፈራሁት አልቀረልኝም ተጠጋኝ...ከእርሱ ሌላ ማየት እስከማልችል ድረስ ቀረበኝ...ከዛም የምወድለትን አስተያየት አየኝ...እጄን አጥብቆ ይዞ ወደራሱ ሲያስጠጋኝ አር የነካው እንጨት እንደያዝከኩ ነገር መነጨቅኩት...'ጎበዝ እድል እንዲህ ነው መጀገን' ብዬ ራሴን አበረታታው...ቢያንስ እናውራ አይባልም...?...አኩርፌ ነበር እኮ...


"እድሌ ይገባኛል አጥፍቻለሁ...በጣም እያበሳጨሁሽ እንደሆነ ይገባኛል...ግን እመኚኝ እለወጣለሁ...በቅርቡ አንድ አሪፍ ስራ አግኝቻለሁ...እንደሚሳካ አልጠራጠርም...ከዛ እንጋባለን...."


"ኧረ ጉድጓድ ግባ"....በሆዴ ነው...በአፌ ምንም አልተነፈስኩም...ግን ምናለ ትንሽ ራቅ ብሎ ቢያወራ...የትንፋሹ ሙቀት እስኪሰማኝ ድረስ ተጠግቶኛል...ከአይኑ ግጭት እንዳልወድቅ እየተጠነቀቅኩ ነው....


"አፈቅርሻለሁ...አፈቅርሻለሁ...ሌላውን እርሺው..."...ካለኝ በኃላ ገፄን ገፁ ውስጥ አገኘሁት...አላስገደደኝም...ግን አስገድዶኛል...ዝብርቅርቅ ያለ ስሜት ነው...ግራ መጋባት አለው...መወሰንም አለመወሰንም...አዎ ከዚህ በኃላ በ'አፈቅርሻለሁ' ትርክት ላለመቀጠል መወሰኔን ላውጅ ነበር አመጣጤ...በነበር ቀረ እንጂ...


"ክክክ-ክክክ".....የሆነ አጠገባችን ያለ  ሰው ጉሮሮውን ሲጠራርግ ነው ከንፈሮቻችን ወደየ ቦታቸው የተመለሱት...


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ገና ስሙ ሲጠራ ያ ለግላጋው ቁመቱ አይታወሰኝም...ከዛ ይልቅ የሚጎላብኝ የአክሱሙ ርዝመት ነው...ዘናጩ ዮናስ አእምሮዬ ውስጥ የለም...ራቁቱን ቅልብጭ ይልብኛል...


ዮናስ ሲባል ሰው ሁሉ የሚደነግጥለት መልኩ እና ጆሮ ሚጠልፈው ድምፁ ጭራሽ አይታወሰኝም...ከጠራው ቆዳው በላይ በላብ የተጠመቀ ሰውነቱ ነው የሚመጣልኝ.....ከምወድለት ድምፁ በላይ አልጋ ላይ ስንጨፍር የሚያወራቸው ትርጉም የለሽ መዘላበዶች እና ቅስቻዎች ናቸው ትውስታዎቼ....


ገና "እድሌ" ከማለቱ ከስሜ በላይ ኩርፊያዬን የሚያስረሳ አለም ውስጥ እንደሚከተኝ በስውር ስለሚነግረኝ ነው ከራሴ ጋር ትግል ውስጥ የሚጨምረኝ....የሚያንቀለቅለኝ መጨረሻዬ ሁለት በሁለት የሆነች ጎጆ ውስጥ እንደሚሆን ስለማውቅ ነው....በራሱ ሜዳ... ራሱ ፈረስ ሆኖ...ራሱ ጋሪ ሆኖ... ራሱ ነጂ ሆኖ ነው የሚሾፍረኝ...


ከባነንኩ በኃላ ተበሳጨሁ...'ለዚህ ነበር ይሄ ሁሉ ፉከራ'...ጠየቅኩ ራሴን...በቃ በቅፅበት ለምረሳው ነው እንዲህ ያዙኝ ልቀቁኝ አልኩ ደግሜ።


"ይቅርታ ከዚህ ካፌ ብዙም ሳትርቁ ፔንሲዮን አለ...."....አለ የቀሰቀሰን አስተናጋጅ...ጉሮሮ አጠራረጉ ግን ይቺን ለመናገር ብቻ አይመስልም ነበር...ነብሳቸውን ይማረውና የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ጉሮሮ እንኳን ያን ሰረቅራቃ ድምፅ ጀባ ለማለት እንደዚህ የሚጠራረግ አይመስለኝም።


"እሺ እሺ ሂሳብ አምጣልን..."....እኔ የሆነ ቦታ ለመሄድ ስጣደፍ በማወጣው ድምፅ ከአስተናጋጁ ጋር ያወራል...እኔ ሽምቅቅ እንዳልኩ አለሁ...

"የኔ ጌታ ምንም አላዘዛችሁም እኮ...."....ከማለቱ ሳቄ አመለጠኝ...አስተናጋጁም ከእኔ ጋር ተደመረ...የዮናስ ግንባር ላይ ችፍ ያለው ላብ የሀፍረት ብቻ አይመስልም...አይኑም በመደፍረስ አገዘው...ከመርበትበቱ የተነሳ ላልተጠቀምነው ነገር ቲፕ ሰጠ...ባሁኑ አልሳቅኩም ጤንነቱን ጠረጠርኩ እንጂ.....


ከካፌው ወጣንና ከእኔና እሱ ውጪ ደንበኛ ከሌለው ቁርቁዝ ካለ  ፔንሲዮን ገባን...የተለመደው እርግጫ...የተለመደውን ጭፈራ ጨፈርን....ይሄን ጭፈራ ለሳምንት ቀጠልን...እንዳይደብረኝ ብሎ የሚያደርገው ነገር ቢኖር ፖዝሽን መቀየር ብቻ ነው...ያኔ አንድ ጭፈራ የነበረው ወደ ብሄር ብሄረሰቦች ጭፈራ ይቀየራል...'በባዶ ሆድ ስራ' አለች ሀኒ...



***


✍ሸዊት



ይቀጥላል....react እያረጋችሁ






https://t.me/shewitdorka
15.04.202515:31
I don't know why ግን dark ነገር ፃፊ ፃፊ የሚለኝ መንፈሴ ተቀስቅሷል....እንኳን ደህና መጣህ በሉትማ😁



የዛሬው dark story ይሄ ነበር....ነገ በተመሳሳይ ሰአት በሌላ dark story እንገናኝ።


ቆዩልኝ💙
Кайра бөлүшүлгөн:
✍ዮ_ሚን avatar
✍ዮ_ሚን
20.04.202509:15
ትንሳኤውን ለትንሳኤ ያድርግልን !

@yomin1_2
02.04.202519:02
አባቴ ጥቁር ነበር ፊቱ አይፈታም። ወታደር ነበር መቶ አለቃም ነበር ። ፀጉር ጥቅጥቅ ያለ ነበር ። አናፂ ነበር ። ብዙ አያወራም ነበር ።

ይወደኝ ነበር ። ያለውን ብር አውጥቶ ሱሪ ጥልፍልፍ ጫማ አቡወለድ ይገዛልኛል ።  አታጨማልቀው ይሉት ነበር ። መቶኝ አያውቅም ።

ከጁ ሲጋራ ከእጁ እኔ አልጠፋም ነበር ። ሲጋራ ሽታው አባቴን ስለሚያስታውሰኝ ሲጋራ እወዳለሁ ። ሲጋራ አጤሳለሁ ።

           አባቴ ኮስተር እንዳለ ነበር ውለታ የሚውለው ። አኮሰታተሩ አዲስ ሰው አያቀርብም ። የቀረበው ሁሉ ግን ይወደዋል ።  ዝናብ ይወድ ነበር ። ፀሃይ ከረረ ብሎ አይነጫነጭም ብርድ ነው ሙቀት ነው እያለ ስለ አየር ሁኔታው አያብራራም ። ከተፈጥሮ ጋ ሲጨቃጨቅ ሰምቼው አላቅም ።

አባቴን እወደዋለሁ ። አይኑ ላይ የማየው ቸርነት እና ፍቅር የትም ስፍራ የትም ፊት ላይ አይቼው አላውቅም ። ምንም ነገር ለኔ ከሆነ ሲሳሳ አይቼ አላውቅም ። አለም ላይ ብቸኛ እንድበልጠው የሚፈልገው አባቴ ነው ።

አባቴ ሲናፍቀኝ ፎቶውን አያለሁ ኮቱን እለብሳለሁ ። ያለኝን አስታውሳለሁ ። ሳላማርር እናፍቀዋለሁ ። ከተፈጥሮ ጋር ሳልጨቃጨቅ ያወረሰኝን መልካምነት እኖረዋለሁ ።

መልኬን እምወደው ስለማምር አይደለም እሱን ስለምመስል ነው። አምሳያዬ ሶስት ቀን ብሎኝ ያውቃል ። እሱ እወዳቸዋለሁ ያለኝን ሰዎች ሁሉ እወዳቸዋለሁ ።
ናፈቀኝ .....ማግኘት የሌለበት  ናፍቆት ደስ አይልም መሰለኝ ።
   
     ©    Adhanom Mitiku
Кайра бөлүшүлгөн:
Open reading 🕊⃤ avatar
Open reading 🕊⃤
1-ድግስ ላይ አንዲት ቆንጆ ልጅ አይተ በመሄድ "ሃብታም ነኝ አግቢኝ" ብትላት፤ ይህ “Direct marketing” ቀጥታ ማርኬቲንግ ነው።

2-የሆነ ግብዣ ላይ ቆንጆ ሴት አይተህ አንዱ ጓደኛህ ወደዛች ልጅ በመሄድ ወደ አንተ እየጠቆመ ሀብታም ነው አግቢው ካለ ይህ “Advertising” ማስታወቂያ ነው።

3-አንዲት ቆንጆ ልጅ ወደ አንተ በመምጣት፡-"ሀብታም ነህ አግባኝ" ካለችህ ይህ “Brand” የምርት ስም እውቅና ነው።

4-አሁንም እቺ ልጅ ጋር ተጠግተህ "ሀብታም ነኝ አግቢኝ" ስትላት በምላሹ በጥፊ ብትመታህ ይህ “Costumer feedback” የደንበኛው አስተያየት ነው።

5-ግብዣው ጋር ወዳለችው ሴት ሄደህ ልታወራ ስትል አንድ ሌላ ቦርጫም ሰውዬ መጥቶ "ሀብታም ነኝ አግቢኝ" ቢላት ይሄ “competition” ውድድር ይባላል።

6-አንተ የፍቅር ጥያቄ አቅርበህላት እሷ ግን ከባሏ ጋር ብታስተዋውቅህ ይህ “Supply and demand gap” የአቅርቦት እና የፍላጎት ክፍተት ነው።

7-አንተ ወደ እርሷ ሄደህ ምንም ከማለትህ በፊት ሚስትህ ብትመጣ እነዚህ አዳዲስ ገበያዎች ወደ አንተ እንዳይመጡ የቀረጥና የቦታ ገደቦች ተጥሎብሃል እንደማለት ያለህ ነው።

ይህ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ውስጥ ፕሮፌሰሩ ስለማርኬቲንግ ለተማሪዎቻቸው በአሪፍ እውነታ ምሳሌዎችን በመስጠት ያስረዱት ነው!
◆━━━━━━✎✦✎━━━━━━━◆
                   ~ @open_reading1 ~

                   ~ @open_reading1 ~
06.04.202511:19
ዝግመተ ለውጥ

ከአለማየሁ ገላጋይ 🙌

በሶፊ 😃

👉👂😜 @bestletters
so true🙌
26.03.202502:45
📚ርዕስ፦ የአማኑኤል ሆስፒታል ታሪኮች
✍️ደራሲ፦ ዶ/ር ዮናስ ላቀው

አማኑኤል ሆስፒታል ብዙ የሚገመቱና የማይገመቱ ነገሮች ይከሰታሉ።

✈️ @Bemnet_Library
27.03.202504:11
ለፍቅር ሲሉ ራሳቸውን መስዋዕት ያደረጉ በድራማ በልብወለድ ወይም በውኑ አለም ያሉ ሰዎችን እንደጀግና ነው የምንቆጥራቸው....እናጨበጭብላቸዋለን....'ጀግና' እንላቸዋለን... ናቸው ግን....?....የፍቅር ግቡ ራስን ማጥፋት ነው....?

ፍቅር ራስን ከማጥፋት ሳይሆን ከማኖር ...ራስን ከመውደድ ራስን ከማክበር ነው የሚጀምረው እንደውም....ጀግንነት ያለው ራስን በመውደድ እና በማክበር ወስጥ ነው...ፍቅር ማለት መስጠትና መቀበል ነው....ሰጥቶ መቅረት አይደለም....መቀበል ብቻም አይደለም....ለመስጠት መጀመሪያ አንተ ራስህ ሊኖርህ ይገባል....ኖሮህም ደግሞ ለመስጠት መፍቀድ አለብህ....በመስጠትህ ልትደሰት ይገባል....ራስህን ልታዋርድ ሳይሆን ልታከብር ነው ሚገባህ።

ራስህን ስትወድ ሌሎችንም ትወዳለህ....ምክንያቱም መውደድን በራስህ ተለማምደኃዋል....አይከብድህም....ለሌሎች ክብር መስጠት አይከብድህም።....ራስህን እንድትጠላ እና ራስህን እንድትጎዳ...ትራስህን በእንባ እንድታረሰርስ አያደርግህም ፍቅር...

ፍቅር ገድሎ አያውቅም....ሰዎች ግን ራሳቸውን ጎዶተዋል....ራሳቸውን በድለዋል....ራሳቸውን አጥፍተዋል...ሌሎችንም አጥፍተዋል...እሱ ፍቅር ሳይሆን የታመመ ፍቅር ነው።




"📚ምን ሆኛለሁ"



https://t.me/shewitdorka
04.04.202519:58
"እምባዬ ጠብ ሲል ያየሁት የምትናገረውን ሰምቼ ሳላበቃ ነበር። ካንተ አልጠብቅማ። አንዱ መንገደኛ ሊገለኝ ቢያስፈራራኝ አንተ እጄን ከጠመዘዝከው ጋር አላወዳድረውም።
ምክንያቱም ካንተ ሲመጣ ; እንኳን መመታትን መገልመጥን  ፈራዋለው። ከብዙ ሰዎች ስድብ ይልቅ ፤  ያንተ እኔን ስታወራኝ ድምጽህን ከፍ ማድረግ ለመከፋት በቂዬ ነው። ምክንያቱም አንተን ራሴን በማምነው ልክ አምንሀለው።
 
"እንዴት ትተሽኝ ሄድሽ?"ብለህ ጠይቀኸኛል። ልነግርህ ነው የመጣሁት። የሄድኩ 'ለት  አንተን ከማይወዱኝ ሰዎች መሀል ተቀምጠህ አየሁክ። የምትናገረውን ስሰማ ነበር  ፤ ግን አላስጨረስኩህም።
እነሱን መርጠህ እኔን እየተውከኝ መስሎኝ ነበር። ትግልህ እኔን ለማስወደድ እንደነበር ግን ዛሬ ከነዝያ ሰዎች አንዱ አብራርቶልኝ ነው የገባኝ።
ከሁለት ዓመት በፊት ፤ እዛ ክፍል ውስጥ ሁለት ደቂቃ ብቆይ ፤ ምናልባት ሕይወት እንዲህ ከራስ የገጠሙት ትግል አይሆንብኝም ነበር ይሆናል።
ካላንተ ልቤ እንዲመታ ባልታገልኩ ነበር።
ግን እይ ሴኮንዶች የሕይወቴን አቅጣጫ እንደምን እንደቀየሩት?!
አሁን እዚህ ጋር ምናገረው ነገር ምንም ለውጥ አያመጣ ይሆናል።
ግን ማወቅ ስላለብህ እነግርሀለው። የምወደውን ሰው ከነዛ ሰዎች ጋር ሲተባበር ማየት አቅቶኝ ነው ቃልህን ሳትጨርስ ሮጬ ያመለጥኩት።

ልቤን በራሴው ሀሳብ ቀጣሁት።
ይግረምህ!
አንተን ብቻ አይደለም ራሴንም ነው የገደልኩት።
ጊዜ ጌታው>>
ምን አ'ረክ? ተብሎ አይከሰስ ነገር......ጊዜን ለፍቅር ስል መታገስ አቅቶኝ የተቀጣሁትን እኔን መልሰህ ትቀጣኝ??" አለችው።

አይኑ ብቻ አይደለም ልቡም እምባን ዘራ። "ፍቅር አበባ ነው። እንደ አደይ ተናፍቆ ብቅ የሚል" ብሎ ስለሚያምን ሊከሳት አልቻለም ፤ እጇን ላልያዘበት ጊዜ""""""ጊዜን ረገመው።
  "ቢረፍድም ደርሰሻል" በጁ እጇን እንደያዘ በጆሮዋ ነገራት።


ቲና ✍️

https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
ጣቶቿን አያቸዋለሁ....ጫፎቻቸው እንደ ቲማቲም የቀሉ....ብትዘቀዝቃቸው የሚንጠባጠቡ የደም ጤዛዎች ይመስላሉ....ውብ ጣቶች....


በእያንዳንዱ ብልጭታ የሀኑንን ውብ ፊት አእምሮዬ እንደ ፎቶ እያተመ ያስቀምጣል....በግራ ትከሻዋ በኩል አልፎ ጡቷ ላይ የሚርመሰመሰው ፀጉሯ በግማሽ ፊቷን የከበበ ውብ ፍሬም መስሏል....እስከ ዛሬ ሀኑንን ሳስብ ያ መልኳ ነው ቀድሞ ሚታወሰኝ....እንደ ቲማቲም የቀሉ ከንፈሮች....ከመቅላቱ ብዛት በወርቃማ ቆዳ የተለበጠ የሚመስል ደረት....ስዕል❤️



አሌክስ አብርሀም
(ከእለታት ግማሽ ቀን)



https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
የስነ ልቦና የምክክር ህክምና አንዳንድ ሰዎች ጓደኞቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን እንደሚመክሩት አይነት ይመስላቸዋል....በእርግጥ ተመሳሳይ ነገሮች ሊሆኑ ይችላሉ...በሌላ መልኩ ደግሞ መሰረታዊ የሆኑ ልዩነቶች አሉት....ልዩነቱ ልክ እንደ ወጥ ቤት ሰራተኛ እና የ'ሼፍ' አይነት ነው...ሁለቱም መጨረሻ ላይ የሚያቀርቡት ምግብ ነው....

ምግቡ ግን ልዩነት አለው።




(ዶክተር ዮናስ ላቀው)
"የአማኑኤል ሆስፒታል ታሪኮች"


https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
ለመላው የእስልምና ተከታይ  ቤተሰቦቻችን እንኳን  እንኳን ለ1446'ኛው የኢድ አልፈጥር በኣል በሰላም አደረሳችሁ 💛


ኢድ ሙባረክ❤️

    
Көбүрөөк функцияларды ачуу үчүн кириңиз.