Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 avatar
Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 avatar
Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
የውይይት ጥሪ ለሰለሞን ሽፈራው (እፎይ)‼
=============================
«እፎይ መጽሐፋችሁን አነበበ እንጂ ምን አጠፋ?» ለሚሉ ሁሉ አድርሱላቸውና ቀርቦ ከስድብ በጸዳ መልኩ በጨዋ ደንብ ይወያይ።
||
✍️ ትናንት ለማኅበረ ቅዱሳኑ መምህር ፈንታሁን ዋቄ የውይይት ጥሪ ቀርቦለት ነበር። እርሱ ግን በትክክለኛው የውይይት መድረክ ከመምጣት ይልቅ በፌስቡክ ፖስቴ ስር እየተሰዳደበ ነበር። ምናልባትም በቀሪ ቀናቶች ወደ መድረኩ ደፍሮ ከመጣ እንጠብቀዋለን።

ነገር ግን ብዙዎች «እፎይን ተወያዩት» ሲሉ እየተመለከትኩ ነበር። በእኔ እሳቤ እፎይ ለአቅመ ውይይት የደረሰ ነው ብዬ አላምንም። እፎይ ሐሰትም ቢሆን በዕውቀት የሚነጋገር ሳይሆን በአፉ የሚፀዳዳ፣ ስርዓት የሌለው፣ በብልግና ስድቦች አፉን የፈታ የሚመስል ከግብረ ገብነት ጭምር ያፈነገጠ ሰው ነው።

ሆኖም አንዳንዶች አዋቂ መስሏቸው እንዳይሸወዱና እርሱም እንደዛ አክት ስለሚያደርግ፤ ይሄው ይፋዊ የውይይት ጥሪ ሰለምቴ በሆነው ወንድማችን ቃልአሚን ጸጋዬ በኩል ቀርቦለታልና እውነትን ለሚፈልግ ሁሉ አድርሱላቸው።

መልዕክቱን እንደወረደ፦

«አንዳንድ "የእፎይ Culቲስቶች" ኮመንት ስር ውር ውር ሲሉ እያየሁ ነው።

እነዚህ ሰዎች በትክክል ማወቅ ያለባቸው "እፎይ"  የራሱ እውቀት ያለው ምሁር አይደለም። ወሬውም  የሚከተለውም የሙግት አደረጃጀት አቅጣጫ  እስልምናን መፅሀፍት በትክክል ከማንበብና ከመገምገም የሚመነጭም አይደለም።

አመለካከቱና የሙግት አደረጃጀቱ ብቻ ሳይሆን ባህሪና ብልግናውም ጭምር በቀጥታ የሚቀዳው ከሳም-ሻሙን ስራዎች ነው።

ለማንኛውም የሳም ሻሞን ስራዎች ሲንኮታኮቱ  የዚህ ጥገኛና ተለጣፊ አመለካከት ምንጩ ይደርቃል። ግንዱ ሲወድቅ ሀረጉ እራሱን ችሎ መቆም ስለማይችል ይጨፈለቃል።  የቀጣዩ ኦፕሬሽንም የትኩረት አቅጣጫም መሆን ያለበት ይህ ነው። በኔ ግምገማ ጥገኛና ተለጣፊው  ብቻ ሳይሆን  ቤዙም ጭምር መናድ ይኖርበታል።  ለማንኛውም ግን በእፎይ  ስነልቦና ከተሸነፋችሁ እናንተው ባላችሁበት እኔን ከእፎይ ጋር ማገናኘትና እንደማያውቅ ላረጋግጥላችሁ ዝግጁ ነኝ። ማድረግ ያለባችሁ ቴሌግራም መክፈት ። እኔና እሱን ማገናኘት። As simple as that!

እፎይ የዓኢሻን ጋብቻ ጉዳይ አጀንዳ አድርጎ ሲያጮህ ነበር። 

በአኢሻ ጋብቻ ጉዳይና በዮሐንስ 1:1 High ክርስቲዮሎጂ ዙሪያ እሱን ለመወያየት ዝግጁ ነኝ

ክርስትያኖች ግለሰቡ  በዚህ ርዕስ ከተስማማ ጠይቁትና በውስጥ አሳውቁኝ። ስለውይይቱ ፎርማሊቲ ከሱ ጋር እናወራለን።»

||
t.me/MuradTadesse
20.04.202518:08
«"የሀገር ልጆች ሰርተን እንብላ

በተለያየ መንገድ የኛውን ኡመት ሀብቱን ለመጨረስ የቁማር ስራዎች በቴክኖሎጂ ታግዘው, በቴሌግራም ተሰብስባችሁ የኦንላይን ስራ ተብሎ ትንሽ ብር አስገብታቹ ባልታወቀ መንገድ አትርፈው ሸውደዋችሁ ቡሀላም ብዙ ብር አስገቡ ተብላችሁ አሁን ተዘግቶባቹ እያለቀሳቹ ነው

ተው እሱን ትታችሁ ሰርታችሁ ብሉ በአካውንት የገባ ሁሉ የሀቅ ብር አደለም።

አንድ ሰውዬ በመዲናችን አ.አ ለብዙ ሰዎች እየዞረ ስራቹን በኦንላይን ላስተዋውቅላቹ በማለት ሰዎቻችን እያስለመደብን ነው ተጠንቀቁ

የሚገርመው ነገር የተሸወደውም ለሌላው ከመናገር ይልቅ ዝም ማለትን መርጡዋል።

እዛ ቻናል ያላችሁ ሰዎች ቶሎ የማትወጡ ከሆነ ማን ማን እንደሆናችሁ, ስንት እንደሆናችሁ እና ስንት ብር እንደተበላቹ ለኡመቱ ይፋ አወጣለሁ። "»

ተሻሽሎ የተተረጎመ
ከኮመንት ማኅደር
20.04.202506:56
ወገኖቻችን እንደሚሉት ከሆነ፤ ከትናንት በፊት ጁሙዓህ እየሱስ ተሰቅሎ ከተገደለ፤ ከዛ ቅፅበት ጀምሮ ዛሬ ሞትን ድል አድርጎ እስከሚነሳ ድረስ ፍጥረተ ዓለሙን ማን እያስተናበረው ነበር⁉️

አብ እንዳትሉኝ። አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ አይደሉ? ስለዚህ እነርሱም አብረው እርሱ የሆነውን ሆነዋል።
የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②③∅⑨]👌


#ቁርኣን
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②③①∅]👌


#ቁርኣን
የባድ ወልድ የከስቤ የትረዘቂስ

በሉላሉሌ ኡንጋ የኛነይ አመ ሰብ ዱኒያክ ለፍዶት የቁማር ብልቻ በቴክኖሎጂ ታንቀፋኔ በቴሌግራም ጭም ባሞኔ ኦንላይን ዝልዛሎ ባሌኔ ጢት ሰንቲብ አገባሞ ሀድኩዝ አተረፌ አበለጡመ በሬርከ ብዢ ዲነት አግቡ ባሉማኔ ጋረይ ኦንጡቡማኔ ቲበኩን አለሙ

ነሙስ ሂደጉ ከሲቦ ቢሎ በአካውንት የገበ ግዝ ሁል ሃንጡራዋ ጡሃረ ግዝ አሎንሰ አይነኒ ማሽነሪ በአይታይ አህድ ገባሞኔ ቲዲጋለሎም መሰለሙ ሂደጉስ

ሀድ ጣማ አለ ለብዢ ሰብቸ ዞረዞራኔ ቢላሙ በኦንላይን ያቻቺላቅ ባላኔ በቡርቴ ከተመ ሉላሎሌ ሱቅቸ ኢታወራን ሂነሚ ገገበያ ለኛይ አመሰብ ያራሮሽን አለ ተቃጠቡ

የረከቢ ግዝ ሁል አይዋጢ ላዬ መጠ የበሊ

የአጂባነይንገ የተበለጠሚ ሰብ ጃንጎ ገናይ ኢላትቃጥብ እዬ የትበለጥኩኮ ተበለጡ ባላኔ አፈክ ኤፋን

ቢታድጉ ጠቅለማን ሀነይ ቻናል ሂደጉይ በሎነንጋ ሱማሙ ጃጎ ማማ ሚስተ የትበለኮ ለአማይ ሰብ ኢልቢጢጦ ያቴራያው
ቢኒያሚን
20.04.202511:37
ብዙ ላጤ ሲጀመር ለአማና አይሆንም። ወሳኝ የሆነ ኃላፊነትና አደራ ለላጤ መስጠት ይከብዳል።
ዝም ብላችሁ ከታዘባችሁ በሰፈር ወይም በጀማዓህ የሆነ ከባድ አማናና ኃላፊነት የሚጠይቅ ጉዳይ ካለ ለላጤ ለመስጠት ያስፈራል።

በቃ! ስልኩን ዘግቶ ቢጠፋ ምኑን ትይዘዋለህ?

ባለ ትዳር ከሆነስ? ይሄ የበሰለ ነው። ኑሮ አስተምሮታል። ኃላፊነትን ቤት በመምራት ያውቃል። እርሱ እንኳ ቢጠፋ በባለቤቱና ቤተሰቦቿ በኩል ድራሹ ይገኛል… ወዘተ።

ባይሆን ይህንን ስል ባለትዳር ተብዬውን የሚያስንቁ ቁም ነገረኛ ላጤዎች የሉም አላልኩም።
20.04.202508:12
ዝም ብላ «ዱዓእ አደርግልሻለሁ፤ አላህ ሷሊሑን ይወፍቅሻል!» አለች።
እሺ! ዱዓሽ መቅቡል ሆኖ ያንቺን ባል ወፈቃት፤ ፍቀጅለታ ታዲያ¡
20.04.202506:26
«አብዛኛው ሰው ማግባት ጠፍቶት ወይም ጥቅሙን ሳያቅ ቀርቶ አይደለም፤ ሚያገባበት ፍሉስ (ገንዘብ) አጥቶ እንጂ!» የምትሉኝ ላጤዎች፤ ታዲያ ገንዘብ ተኝተህ እያደርክ ከሰማይ እንዲወርድልህ ፈልገህ ነው እንደ?

የጠፋው ገንዘብ ሳይሆን ወንድነት ነው።
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②③∅⑧]👌


#ቁርኣን
ግልፅ የውይይት ጥሪ‼
================
『ለፋንታሁን ዋቄ ( Fantahun Wakie )』

መልዕክቱን አድርሱለት!
||
✍️ መምህር ፋንታሁን ዋቄ በመባል የሚታወቀው የቀድሞ የማህበረ ቅዱሳን አመራር ፤ በተለያዩ ግዜያት እስልምና እና ሙስሊሞችን አስመልክቶ ሆን ተብሎና ታቅዶ በሚመስል መልኩ አሳሳች እንዲሁም ሕዝብን ከሕዝብ ሊያጋጩ የሚችሉ መልእክቶችን አስተላልፏል።በዚህ መልኩ የሚዳክሩ አካላት የከሸፈ ሕልም ፣ ድብቅ ፖለቲካዊ አጀንዳ ፣ ተስፋ የመቁረጥ አባዜ እና ጥልቅ የሆነ ፀረ እስልምና አቋም የላቸውም ብሎ ለመደምደም ያስቸግራል።

የሆነው ሆኖ ፋንታሁን ዋቄ እራሱን እንደ ከፍተኛ የጥናት ባለሙያ ፣ የተዋጣለት ሊቅ ፣ ጉምቱ አዋቂ አድርጎ በሚገልፅ መልኩ አምሳዮቹ ብቻ በሚቆጣጠሩት ፕላት ፎርም ተገድቦ እንዳሻው በእስልምና ላይ ሙስሊሞች ላይ መርዙን መርጨቱ ጎበዝ አያሰኘውም።ስለሆነም ከአንደበቱ አዘውትሮ በሚተፋው ርእስ ( ስለ ግድ'ያ እና ጦ'ርነት ) እንደ ዮኒ ማኛ ወይም መሰል ሰዎች አወያይ በሆኑበት መድረክ ፤ ከስድብና ውሸት በራቀ መልኩ ስርአትን ተላብሰን አንደኛው በሌላኛው ሃይማኖት ላይ ወሰን ሳያልፍ በእውቀት ፣ መረጃና ማስረጃ ላይ ተመስርተን ለሕብረተሰቡ ቀጥታ በሚተላለፍ መድረክ እንድንወያይ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ደርሼበታለሁ ፣ አጥንቼያለሁ ፣ አቃለሁ ስለሚለው ሁሉ አግባብ በሆነ መልኩ ስለእምነታችን ስለ መፅሐፍቶቻችን በማስረጃ ይሞግተን ፤ ስለ እምነቱ ስለ መፅሐፍቶቹ በማስረጃ እንሞግተው  ❗️

ከድህረ ውይይቱ በኋላ ውሳኔውን ለሕዝቡ እንተዋለን።

ርእስ ፦ ጦር'ነት እና ግ'ድያ እንዲሁም ሰላም በእስልምናና ክርስትና ያለው አንደምታ


ዐብዱ-ል-ሐኪም ኢድሪስ (አቡ ማሪያ)

||
t.me/MuradTadesse
20.04.202514:21
አላህ ቀልብን ቀያያሪ ነውና እፎይም እንደነ Good Idea ሰልሞ መስጅድ እንገናኝ እንደሆነ እንጂ፤ Ethiopian Federal Police ይዞት ፍርድ ቤት ያገናኘናል ብለን ማሰብ የዋህነት ነው። አላህ ሂዳያ ይስጠው‼
20.04.202511:16
«በትዳር ጉዳይ 90% መወቀስ ካለበት የሚወቀሰው ወንዱ ነው። ሪጃላነት ጠፍቷል። Y ክሮሞዞሙ desensitized ሆኖ risk ይፈራል። በ X single ክሮሞዞም ሲፋ እየኖረ ነው።»

ፕሮፌሰር ቃልኪዳን
ትዳር !
ማግባት ለምን ያስፈልጋል ካሉህ…!
19.04.202519:55
አሁን ያለንበትን ፈሳድ የበዛበት ዘመን ተጨባጭ ጠንቅቆ የታዘበ ሙስሊም፤ ከትዳር ጋር ተያይዞ በሚነሱ ማናቸውም ኸይር ጉዳዮች ላይ አያፌዝም።
ይህን ያደረጉት ሙስሊሞች ቢሆኑ ኖሮ፤ በርካታ መግለጫዎች በርካታ አንቀፆችን በመረጃ በማጣቀስ በተዥጎደጎዱ ነበር።


ግን ሙስሊም ለሆነ ተበዳዩ ባላዬ ነው የሚታለፉት።

እውነት ያለው ሰው በመረጃ ያሳምናል፣ ይሰብካል እንጂ፤ በጉልበት አስገድዶ እምነቴን ተቀበሉ አይልም፣ በስድብና ዘለፋ አይጠመድም።

እነዚህን በቪድዮው የሚታዩትን መክሰስ ይቻል ነበር። ግን ለማን ይከሰሳል? ማን መፍትሄ ሊሰጥ?

||
t.me/MuradTadesse
20.04.202514:02
«አንዱ የዱንያ መገለጫ ውድድር (تفاخر) ነው። ሙእሚን በዚች አለም ቋሚ ነኝ ብሎ አያስብም። ስታንዳርዱንም አለቅጥ አይለጥጥም። ሙእሚን አላማው በዚች ዱንያ በአደብ ኖሮ አኼራውን አበጅቶ ወደ ፊርደውስ መሄድ ነው።

ሌላውን ትተህና ትተሽ እንደራስህና እንደራስሽ ጎጆ ቀልሽ። የአላህ እርዳታ ወዲያውኑ ይከታተላል።

እንደኛ ገና በ21 እና 22 አመታችን አገር ጉድ እያለ ሶስት በሶስት ክፍል ቤት ውስጥ ጎጆ የቀለስን ሰዎች በአፍላው እድሜያችን ኑሮን ግብግብ ገጥመን አሸንፈናታል። ሀቁ ግን ጉድ ሲሉ የነበሩ ሁሉ ጉድ ሆነዋል። ውጤቱ በብዙ መልኩ እጅግ ጥሩ ነበር። አሁን እንደ እህትና ወንድም የሚመክሩን የሚደግፉን ልጆች አድርሰናል።

ያለገባችሁ ነቃነቃ በሉ። ዱንያን ለየብቻ ከመግጠም በጥንድ ግጠሟት።»

አሕመድ ሙሐመድኑር
በዝሙት አንዘምን‼
በኒካሕ እንሰልጥን‼
20.04.202507:17
ያገባችዋ ጓደኛሽ በደረቁ «እወድሻለሁ!» ከማለት ይልቅ የእውነት ከልቧ ከወደደችሽ ለራሷ የወደደችውን ላንቺም ልትወድልሽ ይገባልና ባሏን በሐላሉ ታካፍልሽ።
20.04.202505:01
«በትዳር ላይ የሚሳለቁትን፣ዝሙትን ውስልትናን የሚያስተምሩትን ሚሊየኖች ተከታይ ሲያገኙ፣ባለሀብት ስናደርጋቸው ሌሎችም አርአያ አድርጓቸው ሲከተሏቸው ዝም ያልነውን የትዳር አጀንዳ ሲነሳ ለመሳለቅ እንዴት ደፈርን ?

በመጀመሪያ ደረጃ እንዲህ ያሉ የወረዱ ሰዎችን ጉዳይ በማጋራቴ ትልቅ ይቅርታ እጠይቃለሁ ። ነገር ግን እነዚህ እህት እና ወንድሞቻችን በሚሊየኖች ተከታይ ያገኙ ፣በነውረኝነታቸው ታዋቂ አድርገን በገንዘብም በእውቅናም ዝነኛ ያደርግናቸው ብዙዎች የሚያውቋቸው ናቸውና ለማስተማሪያነት እዚህ ማምጣቴ ግድ አለኝ ።

ሁልጊዜ ማለት በሚቻል መልኩ ትዳርን የሚያጥላላ፣በትዳር ላይ መውሰለትን፣ትዳር ማለት አስቀያሚ መሆኑን ረቂቅ በሆነ መንገድ መርዛቸውን ነውራቸውን ሲረጩ ከርመዋል። ረቂቅ በሆነ ቀልድ በሚመስል መንገድ እሴት ተሸርሽሯል :: ያልተጋቡ ሴት እና ወንድ እየተሻሸሹ ኮንቴንት መስራት ሚሊየን ተከታዮችን እና ሚሊየን ብሮችን የሚያስገኝም ሁኗል ::

አንድ ተው ብሎ ያወገዘ አላየሁም ። እንዲያውም በክብር የተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ፣ኢስላማዊ ፕሮግራሞች ላይ ጭምር በክብር ሲጠሩ፣ከዚያም አልፎ ተርፎ ኡምራ ፓኬጅን ጨምሮ ለተለያዩ ድርጅቶች ማስታወቂያ በማሰራት የሀብት ማማ ላይ አድረሰናቸዋል። እንደዚህ ያሉ ልጆችን መውቀስ መናገር በራሱ ''ቀንተህባቸው ነው በነሱ ልትሸቅልባቸው ነው '' የሚያስብል ስድብም፣ ይከተላል ።

ታዲያ እነዚህን እና መሰል ትልልቅ የሆኑ ኢስላማዊ እሴቶችን ለሚሽሩ ለሚሸረሽሩ ሰዎች ሰዎች ጥብቅና የሚቆሙ ሰዎች ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ ገና ስለ ትዳር ዘውጁና ብሎ ሲናገር አጀንዳውን እንኳን በይፋ ሳያብራራ ሙድ ያዙበት፣ተሳለቁበት

ሃቂቃ ወዴት እይሄድን ነው ? የኡስታዝ ኑሩ አካሄድ ትክክል ያልሆነ ነገር ካለው ማስተካከል በጨዋ ደንብ ሃሳብ መስጠት ይቻላል። ነገር ግን በዚያውጅ ሃሳቡ ላይ መሳለቅ ነውረኞችን በክብር ተቀብለን ስናስተናድ ያላፈርነውን እንደ ማህበረሰብ ስንዘቅጥ ምንም ያልሰመሰለንን የትዳር አጀንዳ ሲነሳ ለመሳለቅ ደረስን !

በጣም አሳዛኝ ጊዜ ነው ። ቆም ብለን እናስብ ! ነውረኞችን ስናከብር አንዳች ያልተነፍስነውን ኸይር የሚሰሩ ሲነሱ አንሳለቅ ። እንዲህ ያሉ ነውረኞችን ጭምር ማስታወቂያ የምታሰሩ የንግድ ድርጅቶች ልታፍሩ ይገባችኋል ።

ቢመርም እውነታው ይኼው ነው።»

©: ዐብዱ-ር'ረሒም አሕመድ
⑩) በሃገሪቱ የዜጎች የሰብዓዊ መብት እንዳይከርና መልካም አስተዳደር እንዳይሰፍን እንቅፋት ይሆናል፣

⑪) ሰላምን አምጪ ሳይሆን ላልተፈለገ ፍጥጫ እና ግጭት የሚዳርግ፣ ጥላቻን የሚያዳብር፣ በመንግስት እና በዜጎቹ መካከል አለመተማመንን የሚያጎለብት ሰነድ ወደመሆኑ ያዘነብላል፣

በአጭሩ፦ በሴኪዩላሪዝም ሽፋን የሚፈፀመው የሒጃብ ገፈፋ በአስቸኳይ ይቁም!
ባለቤት የሌለውን ህግ ሙስሊሙን የሚጨቁን ስለሆነ ብቻ ሕያው በማድረግ፤ በሰበብ አስባቡ ሙስሊሙን መጨቆን፣ እህቶችን በየአመቱና በየቦታው መጨቆንና ማንገላታት ይቁም‼



ፎቶ: የኢህአዴግ ዘመኑ ዶ/ር ሽፈራው እና ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

እንዲሁም 2000 ላይ ከወጣው ረቂቅ ኒቃብን በተመለከተ ክልከላ ያለበት ገፅ



||
t.me/MuradTadesse
Shown 1 - 24 of 1014
Log in to unlock more functionality.