Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Event Addis Media avatar

Event Addis Media

Connect with Addis Ababa's artistic community! Find out about art exhibitions, music events, workshops, and cultural experiences. Contact: @Tmanaye
Website:https://eventaddis.com/
TGlist 评分
0
0
类型公开
验证
未验证
可信度
不可靠
位置
语言其他
频道创建日期Jun 07, 2022
添加到 TGlist 的日期
Oct 20, 2024
关联群组

记录

11.05.202523:59
9.3K订阅者
26.04.202523:59
200引用指数
24.03.202514:33
2.4K每帖平均覆盖率
17.04.202512:42
2.4K广告帖子的平均覆盖率
03.05.202513:27
2.88%ER
23.04.202512:42
25.79%ERR
订阅者
引用指数
每篇帖子的浏览量
每个广告帖子的浏览量
ER
ERR
NOV '24DEC '24JAN '25FEB '25MAR '25APR '25MAY '25

Event Addis Media 热门帖子

📌የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ አውደርዕይ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ 17ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውስጥ ያካሂዳል።

በነዚህ ቀናት በዩኒቨርሲቲው በመገኘት አውደርዕዩን ጎብኙ፣መጽሐፍት ግዙ፣ስለ ንባብ ተወያዩ ተብላችኋል።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
📌"በመኖር በኩል" መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል

የደራሲ አድኃኖም ምትኩ "በመኖር በኩል" መጽሐፍ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ተመርቆ ለንባብ ይበቃል ተብሏል።

"በመኖር በኩል" መጽሐፍ አስራ ሰባት አጫጭር እና የተያያዙ ታሪኮች ያሉበትን የልብወለድ መጽሀፍ ነው።

ደራሲ አድኃኖም ምትኩ የበኩር ስራው የሆነውን "አዎ እሱ ጋ ያመኛል" የተሰኘ የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ መፅሃፍ በግንቦት ወር 2015 ዓ.ም ለአንባብያን ያደረሰ ሲሆን መጽሀፉ ተወዳጅነትን በማትረፍ በአጭር ግዜ ውስጥ አምስተኛ ህትመት ደርሶ ከአስራ ስምንት ሺ ኮፒ በላይ መሸጥ እንደተቻለ ተነግሯል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
📌ድምጻዊ ልዑል ሲሳይ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል

(መግቢያው በነፃ ነው)

የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር ልዑል ሲሳይን ጋብዟል::

የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች"ከልዑል ጋር በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ የፊታችን  ማክሰኞ ሚያዚያ 28, 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ ገለጸዋል።

በዕለቱ ከድምጻዊ ልዑል ሲሳይ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::

ፕሪስቴጅ አዲስ ከልዑል ሲሳይ ጋር  የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ  ማክሰኞ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:

📎 በ ዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱

 https://jazzio.land/register

መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
📌የአይዳ ሙሉነህ የፎቶግራፍ ዓውደርዕይ

በአይዳ ሙሉነህ ተዘጋጅቶ በ ዘ-ኢንድ ፈንድ አዘጋጅነት እና በሪቺንግ ዘ-ላስት ማይል ድጋፍ ለህዝብ የቀረበው ሪፍሬሚንግ ኔግሌክት የተሰኘ የፎቶ ዓውደ-ርዕይ ተከፈተ፡፡

በዓውደ-ርዕዩ አይዳ ሙሉነህን ጨምሮ የሰባት አፍሪካዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ስራ ስብስብ የቀረበ ሲሆን በዋነኝነትም ደሀ ከሚባሉ አገራት ውስጥ ከሚከሰቱ በሽታዎች ያላቸውን ማህበራዊ እና ኢኮሚያዊ ጫና ለተመልካች ለማቅረብና የአፍሪካዊያንን ድምፅ ለአለም ለማሰማት የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በስራዎቻቸው ጠንካራ ታሪክን በፎቶ የማስቀረት እና ማህረሰቡ የሚያልፍበትን እውነታ የማንፀባረቅ ድንቅ ችሎታ ያላቸው የስድስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች 54 የስነጥበብ ስራዎችና ዘጋቢ‐ፎቶዎች የተካተተበት ዓውደ-ርዕይ ስነ-ጥበብ ምን ያህል ወሳኝ ጉዳዮችን የማጉላት ትልቅ አቅም እንዳለው ያሳያሉ ተብሏል፡፡

እ.ኤ.አ በ2022 ተጀምሮ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በአፍሪካ 2.8 ሚሊዮን ሰዎችን ተደራሽ ያደረገው ይሄው ዓውደ-ርዕይ በታላቅ ክብረበአል ሚያዚያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰአት ጀምሮ እስከ ግንቦት 19 2017ዓ.ም በገብረክርስቶስ ደስታ ማዕከል ለተመልካች ክፍት ይሆናል፡፡

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌"በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም"

የሠዓሊ አሸናፊ ማስቲካ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም" የተሰኘ የሥዕል አውደርዕይ ባሳፍነው ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኘው አርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ በቅቷል።

ይህ የሥዕል አውደርዕይ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ድርስ እንደሚቆይ አዘጋጆቹ ተናግረዋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌ዛሬ ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ቀን ነው!

የዓለም መጽሐፍ ቀን በየዓመቱ ሚያዝያ 15 ይከበራል

ሚያዝያ 15 ለዓለምአቀፍ የመጽሐፍ ቀንነት የተመረጠበት ምክንያት የዊልያም ሼክስፒር እና ስፔናዊው የታሪክ ጸሐፊ ኢንካ ጋርሲላሶ ዴ ላ ቬጋ የሞቱበት ቀን በመሆኑ እንደመታሰቢያ እንዲሆን ነው።

በእዚህ ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ በተለይ ወላጆች ለልጆቻቸው መጻሕፍትን በስጦታ መልክ በመስጠት ያከብሩታል።

የቀኑም ትልቁ ዓላማ የንባብ በዓል ማዳበረ ነው።

#Worldbookday!

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
📌"ቍናማት" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ

በገጣሚ ሐዋዝ የሻነህ የተዘጋጀው "ቍናማት" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል።

መጽሐፉ የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ205 ገፆች ተቀንብቦ በ400 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።

ገጣሚና ደራሲ ሐዋዝ የሻነህ ከዚህ መጽሐፍ አስቀድሞ "ኢካቦድ"የግጥም ስብስብ)፣ "የአዳም ፊርማ" እና "ሰውነት" የተሰኘ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌የአርብ ምሽቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!

በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ

የአርትስ ስፔሻል መረጃዎች ዋና ዋና ጉዳዮች:

1. የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ካደረሰ ሃያ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት መለሠ እና ሚካኤል በላይነህ የተጣመሩበት የሙዚቃ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው።

2.ጦቢያ የኪነጥበብና የሀሳብ መሰናዶ በዘጠኝ የአውሮፓ ሃገራት በ16 የአውሮፓ ትልልቅ ከተሞች ትርዒቱን ሊያቀረብ ነው።

3.ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ከፍተኛ ወጪ አውጥቼበታለሁ ያለውን የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች እንደሚያቀርብ ተናገረ።

4.የደራሲ አድኃኖም ምትኩ ሁለተኛ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።

5.'የተሸመኑ ትውስታዎች' የሥዕል አውደርዕይ ነገ ይከፈታል።

6.ኮሜዲያን እሸቱ መለሠ የኮሜዲ ዝግጅቱን ነገ በለንደን ከተማ ያቀርባል።

እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:

https://youtu.be/XBpZW2u7i3M?si=jPI7dBJ4hx5gLsrd

📌መልካም ምሽት

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
📌"ጦቢያ" በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት

"ጦቢያ" የኪነጥበብ ዝግጅት በ9 የአውሮፓ ሃገራት ትርዒቱን ሊያቀርብ እንደሆነ ተሰምቷል።

ይህም የአውሮፓ ጉዞ ጦቢያ ከሆፕ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው ተብሏል።ከወርሐ ሰኔ እስከ ነሐሴ ለሁለት ወራት ገደማ የሚካሄደው ዝግጅቱ የኢትዮጵያዊያንን ባህል ለማስተዋወቅ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም ተገልጿል።

ጦቢያ በዚህ ጉዞው በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት እና በ16 የአውሮፖ ትላልቅ ከተሞች  ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
4 የኢቤኤስ ሰራተኞች በዋስትና እንዲለቀቁ ተወሰነ

በሽብር ወንጀል ጉዳይ ተጠረጥረው በእስር ላይ የሚገኙ አራት የኢቤኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች፤ ዋስትና በማስያዝ እንዲለቀቁ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ።

ሁለት የጣቢያው ሰራተኞችን ጨምሮ 16 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት አስታውቋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌 የነገረ መጻሕፍት አዘጋጆችና ታደሚያን ቅዳሜ "አበሻው " በተሰኘ መጽሐፍ ላይ ይወያያሉ

በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ነገ ቅዳሜ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።በዚህ ሳምንት የተመረጠው መጽሐፍ "አበሻው " የተሰኘ መጽሐፍ ሲሆን በክብር እንግዳነት አያሌው ምትኩ ብሩ ይገኛሉ ተብሏል። የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1‌‌
📌"ለጋስ አድማስ" መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው

በገጣሚ ወልደገብርኤል ደሳለኝ(ወገደ) የተዘጋጀው "ለጋስ አድማስ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ በቅርቡ ንባብ ይበቃል ተብሏል።

"ለጋስ አድማስ" የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ350 ብር በቅደመ ሽያጭ ለአንባቢያን ይቀርባል።

መጽሐፉን መግዛት ለሚፈልጉ የባንክ ቁጥር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦ 1000530618661
ወልደገብርኤል ደሳለኝ
ቴሌ ብር ፦0992269755

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌የድምጻዊት ዘቢባ ግርማ "እንደምንም" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነው

አንጋፋውና ወጣት የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት “እንደምንም" የሙዚቃ አልበም 13 ሙዚቃዎችን በውስጡ የያዘ  ሲሆን አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ዓመት እንዲወሰድባትም ተነግሯል።

ለአልበሙ ላይ የሦስት የሙዚቃ ቪዲዮዎች ተሰርቶ የተጠናቀቁ ሲሆን ይህ አልበም ሙሉ በሙሉ በድምጻዊት ዘቢባ ግርማ ፕሮዲዩስ ተደርጓል፡፡

የሙዚቃ አልበሙ ስለ ፍቅር፤ ስለ ምስጋና እና ስለ እናት እና የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮችን ይዳስሳል።

የድምጻዊት ዘቢባ ግርሓጨ"እንደምንም" የተሰኘው አልበም የፊታችን አርብ ግንቦት አንድ በዘቢባ ግርማ ዩቲዩብ ቻናል እና በሁሉም ዓለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለአድማጮች ይቀርባል።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
26.04.202506:14
📌የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በአዲስ አበባ ኮንሰርቶች

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በሀገሪቱ ውስጥ የመዝናኛ እና የዕድል ፍላጎትን ለማጣጣም በሚያስችል አዲስ እና ትኩረት የሚስብ አካሄድ ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር በነገው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄዱ ሶስት ታዋቂ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ተከትሎ  የፊታችን ግንቦት ወር የሚወጣውን 50 ሚሊዮን ሎተሪ እንደሚያስተዋውቅ ገለጸ።

በሙዚቃ ኮንሰርት ታዳሚዎች  በመዝናናታቸው ጎን ለጎን የ50 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ሎተሪ የመቁረጥ ዕድል ይኖራቸዋል ተብሏል።

ዛሬ በሚደረጉ ሶስቱም ኮንሰርቶች ላይ ለሚሳተፋ በነፃ ለሚመዘገቡ ባለዕድለኞች የ50,000 (የሃምሳ ሺህ ብር) ሽልማትም ቀርቧል።

ይህ ልዩ ዕድል ሽልማት ዛሬ በሚካሄዱት በሚሊኒየም አዳራሽ ሽርጉድ ኮንሰርት ፣ በግዮን ሆቴል  ልዑል ኮንሰርት እና በማርዮት ሆቴል በሚካሄደው  ኤሌጋንስ ኮንሰርቶች ላይ የሚሳተፉትን ተሳታፊዎች ሎተሪ በመቁረጥ በEthiolottery.et ድረ ገጽ ላይ በመመዝገብ በቀላሉ እድለኛ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
📌 የሪፖርተር ጋዜጠኛ ታሰረ

የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ ጋዜጠኛ አበበ ፍቅር ታሰረ፡፡ ጋዜጠኛ አበበ የታሰረው ትናንት ሚያዚያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት አካባቢ ነው፡፡

ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው ከልደታ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች መረጃ በማሰባሰብ ላይ እያለ ሲሆን፣ የታሰረበት ምክንያት እስካሁን ግልጽ አልሆነም፡፡ ጋዜጠኛ አበበ በዕለቱ በፖሊሶች ተይዞ ከመወሰዱ በስተቀር በወቅቱ ወዴት እንደተወሰደና እንደታሰረ ባለመታወቁ፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሪፖርት በማድረግ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ባደረገው ትብብር ጋዜጠኛው በልደታ ክፍል ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጌጃ ሰፈር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩ ታውቋል፡፡

ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው እየሠራው ለነበረው ዘገባ ሚዛኑን ለመጠበቅ፣ የክፍለ ከተማውን ኃላፊዎች ለማነጋገር በሥፍራው በተገኘበት ወቅት ነበር፡፡

ዘገባው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
登录以解锁更多功能。