
Анатолий Шарий

Лёха в Short’ах Long’ует

Реальний Київ | Украина

Мир сегодня с "Юрий Подоляка"

Труха⚡️Україна

Николаевский Ванёк

Инсайдер UA

Реальна Війна | Україна | Новини

Лачен пише

Анатолий Шарий

Лёха в Short’ах Long’ует

Реальний Київ | Украина

Мир сегодня с "Юрий Подоляка"

Труха⚡️Україна

Николаевский Ванёк

Инсайдер UA

Реальна Війна | Україна | Новини

Лачен пише

Анатолий Шарий

Лёха в Short’ах Long’ует

Реальний Київ | Украина

Event Addis Media
Connect with Addis Ababa's artistic community! Find out about art exhibitions, music events, workshops, and cultural experiences. Contact: @Tmanaye
Website:https://eventaddis.com/
Website:https://eventaddis.com/
关联群组
EA
EVENT ADDIS FAMILY'S !
129
记录
11.05.202523:59
9.3K订阅者26.04.202523:59
200引用指数24.03.202514:33
2.4K每帖平均覆盖率17.04.202512:42
2.4K广告帖子的平均覆盖率03.05.202513:27
2.88%ER23.04.202512:42
25.79%ERR

02.05.202510:42
📌የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ አውደርዕይ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ 17ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውስጥ ያካሂዳል።
በነዚህ ቀናት በዩኒቨርሲቲው በመገኘት አውደርዕዩን ጎብኙ፣መጽሐፍት ግዙ፣ስለ ንባብ ተወያዩ ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ 17ኛውን ዓመታዊ የመጽሐፍ አውደ-ርዕይ ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ስድስት ኪሎ በሚገኘው በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ውስጥ ያካሂዳል።
በነዚህ ቀናት በዩኒቨርሲቲው በመገኘት አውደርዕዩን ጎብኙ፣መጽሐፍት ግዙ፣ስለ ንባብ ተወያዩ ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1


12.05.202507:32
📌"በመኖር በኩል" መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል
የደራሲ አድኃኖም ምትኩ "በመኖር በኩል" መጽሐፍ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ተመርቆ ለንባብ ይበቃል ተብሏል።
"በመኖር በኩል" መጽሐፍ አስራ ሰባት አጫጭር እና የተያያዙ ታሪኮች ያሉበትን የልብወለድ መጽሀፍ ነው።
ደራሲ አድኃኖም ምትኩ የበኩር ስራው የሆነውን "አዎ እሱ ጋ ያመኛል" የተሰኘ የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ መፅሃፍ በግንቦት ወር 2015 ዓ.ም ለአንባብያን ያደረሰ ሲሆን መጽሀፉ ተወዳጅነትን በማትረፍ በአጭር ግዜ ውስጥ አምስተኛ ህትመት ደርሶ ከአስራ ስምንት ሺ ኮፒ በላይ መሸጥ እንደተቻለ ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የደራሲ አድኃኖም ምትኩ "በመኖር በኩል" መጽሐፍ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ተመርቆ ለንባብ ይበቃል ተብሏል።
"በመኖር በኩል" መጽሐፍ አስራ ሰባት አጫጭር እና የተያያዙ ታሪኮች ያሉበትን የልብወለድ መጽሀፍ ነው።
ደራሲ አድኃኖም ምትኩ የበኩር ስራው የሆነውን "አዎ እሱ ጋ ያመኛል" የተሰኘ የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ መፅሃፍ በግንቦት ወር 2015 ዓ.ም ለአንባብያን ያደረሰ ሲሆን መጽሀፉ ተወዳጅነትን በማትረፍ በአጭር ግዜ ውስጥ አምስተኛ ህትመት ደርሶ ከአስራ ስምንት ሺ ኮፒ በላይ መሸጥ እንደተቻለ ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


01.05.202510:43
📌ድምጻዊ ልዑል ሲሳይ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል
(መግቢያው በነፃ ነው)
የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር ልዑል ሲሳይን ጋብዟል::
የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች"ከልዑል ጋር በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 28, 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ ገለጸዋል።
በዕለቱ ከድምጻዊ ልዑል ሲሳይ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::
ፕሪስቴጅ አዲስ ከልዑል ሲሳይ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ማክሰኞ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
📎 በ ዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱
https://jazzio.land/register
መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
(መግቢያው በነፃ ነው)
የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር ልዑል ሲሳይን ጋብዟል::
የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች"ከልዑል ጋር በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 28, 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ ገለጸዋል።
በዕለቱ ከድምጻዊ ልዑል ሲሳይ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::
ፕሪስቴጅ አዲስ ከልዑል ሲሳይ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ማክሰኞ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
📎 በ ዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ ፡፡👇🖱
https://jazzio.land/register
መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1


28.04.202512:52
📌የአይዳ ሙሉነህ የፎቶግራፍ ዓውደርዕይ
በአይዳ ሙሉነህ ተዘጋጅቶ በ ዘ-ኢንድ ፈንድ አዘጋጅነት እና በሪቺንግ ዘ-ላስት ማይል ድጋፍ ለህዝብ የቀረበው ሪፍሬሚንግ ኔግሌክት የተሰኘ የፎቶ ዓውደ-ርዕይ ተከፈተ፡፡
በዓውደ-ርዕዩ አይዳ ሙሉነህን ጨምሮ የሰባት አፍሪካዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ስራ ስብስብ የቀረበ ሲሆን በዋነኝነትም ደሀ ከሚባሉ አገራት ውስጥ ከሚከሰቱ በሽታዎች ያላቸውን ማህበራዊ እና ኢኮሚያዊ ጫና ለተመልካች ለማቅረብና የአፍሪካዊያንን ድምፅ ለአለም ለማሰማት የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በስራዎቻቸው ጠንካራ ታሪክን በፎቶ የማስቀረት እና ማህረሰቡ የሚያልፍበትን እውነታ የማንፀባረቅ ድንቅ ችሎታ ያላቸው የስድስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች 54 የስነጥበብ ስራዎችና ዘጋቢ‐ፎቶዎች የተካተተበት ዓውደ-ርዕይ ስነ-ጥበብ ምን ያህል ወሳኝ ጉዳዮችን የማጉላት ትልቅ አቅም እንዳለው ያሳያሉ ተብሏል፡፡
እ.ኤ.አ በ2022 ተጀምሮ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በአፍሪካ 2.8 ሚሊዮን ሰዎችን ተደራሽ ያደረገው ይሄው ዓውደ-ርዕይ በታላቅ ክብረበአል ሚያዚያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰአት ጀምሮ እስከ ግንቦት 19 2017ዓ.ም በገብረክርስቶስ ደስታ ማዕከል ለተመልካች ክፍት ይሆናል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በአይዳ ሙሉነህ ተዘጋጅቶ በ ዘ-ኢንድ ፈንድ አዘጋጅነት እና በሪቺንግ ዘ-ላስት ማይል ድጋፍ ለህዝብ የቀረበው ሪፍሬሚንግ ኔግሌክት የተሰኘ የፎቶ ዓውደ-ርዕይ ተከፈተ፡፡
በዓውደ-ርዕዩ አይዳ ሙሉነህን ጨምሮ የሰባት አፍሪካዊ የፎቶግራፍ ባለሙያዎች ስራ ስብስብ የቀረበ ሲሆን በዋነኝነትም ደሀ ከሚባሉ አገራት ውስጥ ከሚከሰቱ በሽታዎች ያላቸውን ማህበራዊ እና ኢኮሚያዊ ጫና ለተመልካች ለማቅረብና የአፍሪካዊያንን ድምፅ ለአለም ለማሰማት የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በስራዎቻቸው ጠንካራ ታሪክን በፎቶ የማስቀረት እና ማህረሰቡ የሚያልፍበትን እውነታ የማንፀባረቅ ድንቅ ችሎታ ያላቸው የስድስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች 54 የስነጥበብ ስራዎችና ዘጋቢ‐ፎቶዎች የተካተተበት ዓውደ-ርዕይ ስነ-ጥበብ ምን ያህል ወሳኝ ጉዳዮችን የማጉላት ትልቅ አቅም እንዳለው ያሳያሉ ተብሏል፡፡
እ.ኤ.አ በ2022 ተጀምሮ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በአፍሪካ 2.8 ሚሊዮን ሰዎችን ተደራሽ ያደረገው ይሄው ዓውደ-ርዕይ በታላቅ ክብረበአል ሚያዚያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12 ሰአት ጀምሮ እስከ ግንቦት 19 2017ዓ.ም በገብረክርስቶስ ደስታ ማዕከል ለተመልካች ክፍት ይሆናል፡፡
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


28.04.202512:52
📌"በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም"
የሠዓሊ አሸናፊ ማስቲካ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም" የተሰኘ የሥዕል አውደርዕይ ባሳፍነው ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኘው አርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ድርስ እንደሚቆይ አዘጋጆቹ ተናግረዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የሠዓሊ አሸናፊ ማስቲካ የሥዕል ስራዎች የቀረቡበት "በይው ተቀየረ እንጂ ትሪው አልተነሳም" የተሰኘ የሥዕል አውደርዕይ ባሳፍነው ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኘው አርታዊ የሥዕል ማሳያ ውስጥ ለእይታ በቅቷል።
ይህ የሥዕል አውደርዕይ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ድርስ እንደሚቆይ አዘጋጆቹ ተናግረዋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


23.04.202504:07
📌ዛሬ ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ቀን ነው!
የዓለም መጽሐፍ ቀን በየዓመቱ ሚያዝያ 15 ይከበራል
ሚያዝያ 15 ለዓለምአቀፍ የመጽሐፍ ቀንነት የተመረጠበት ምክንያት የዊልያም ሼክስፒር እና ስፔናዊው የታሪክ ጸሐፊ ኢንካ ጋርሲላሶ ዴ ላ ቬጋ የሞቱበት ቀን በመሆኑ እንደመታሰቢያ እንዲሆን ነው።
በእዚህ ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ በተለይ ወላጆች ለልጆቻቸው መጻሕፍትን በስጦታ መልክ በመስጠት ያከብሩታል።
የቀኑም ትልቁ ዓላማ የንባብ በዓል ማዳበረ ነው።
#Worldbookday!
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የዓለም መጽሐፍ ቀን በየዓመቱ ሚያዝያ 15 ይከበራል
ሚያዝያ 15 ለዓለምአቀፍ የመጽሐፍ ቀንነት የተመረጠበት ምክንያት የዊልያም ሼክስፒር እና ስፔናዊው የታሪክ ጸሐፊ ኢንካ ጋርሲላሶ ዴ ላ ቬጋ የሞቱበት ቀን በመሆኑ እንደመታሰቢያ እንዲሆን ነው።
በእዚህ ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ በተለይ ወላጆች ለልጆቻቸው መጻሕፍትን በስጦታ መልክ በመስጠት ያከብሩታል።
የቀኑም ትልቁ ዓላማ የንባብ በዓል ማዳበረ ነው።
#Worldbookday!
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1


03.05.202513:28
📌"ቍናማት" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
በገጣሚ ሐዋዝ የሻነህ የተዘጋጀው "ቍናማት" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል።
መጽሐፉ የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ205 ገፆች ተቀንብቦ በ400 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚና ደራሲ ሐዋዝ የሻነህ ከዚህ መጽሐፍ አስቀድሞ "ኢካቦድ"የግጥም ስብስብ)፣ "የአዳም ፊርማ" እና "ሰውነት" የተሰኘ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በገጣሚ ሐዋዝ የሻነህ የተዘጋጀው "ቍናማት" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ መጽሐፍ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል።
መጽሐፉ የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ205 ገፆች ተቀንብቦ በ400 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚና ደራሲ ሐዋዝ የሻነህ ከዚህ መጽሐፍ አስቀድሞ "ኢካቦድ"የግጥም ስብስብ)፣ "የአዳም ፊርማ" እና "ሰውነት" የተሰኘ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


09.05.202515:38
📌የአርብ ምሽቱ አርትስ ስፔሻል በትኩሱ ደርሷል !!
በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ
የአርትስ ስፔሻል መረጃዎች ዋና ዋና ጉዳዮች:
1. የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ካደረሰ ሃያ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት መለሠ እና ሚካኤል በላይነህ የተጣመሩበት የሙዚቃ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው።
2.ጦቢያ የኪነጥበብና የሀሳብ መሰናዶ በዘጠኝ የአውሮፓ ሃገራት በ16 የአውሮፓ ትልልቅ ከተሞች ትርዒቱን ሊያቀረብ ነው።
3.ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ከፍተኛ ወጪ አውጥቼበታለሁ ያለውን የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች እንደሚያቀርብ ተናገረ።
4.የደራሲ አድኃኖም ምትኩ ሁለተኛ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።
5.'የተሸመኑ ትውስታዎች' የሥዕል አውደርዕይ ነገ ይከፈታል።
6.ኮሜዲያን እሸቱ መለሠ የኮሜዲ ዝግጅቱን ነገ በለንደን ከተማ ያቀርባል።
እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።
"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:
https://youtu.be/XBpZW2u7i3M?si=jPI7dBJ4hx5gLsrd
📌መልካም ምሽት
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዚህ ሳምንት እነዚህን ጉዳዮች ታገኛላችሁ
የአርትስ ስፔሻል መረጃዎች ዋና ዋና ጉዳዮች:
1. የሙዚቃ አልበሙን ለአድማጮች ካደረሰ ሃያ ሁለት ዓመታት ያስቆጠረው አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት መለሠ እና ሚካኤል በላይነህ የተጣመሩበት የሙዚቃ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው።
2.ጦቢያ የኪነጥበብና የሀሳብ መሰናዶ በዘጠኝ የአውሮፓ ሃገራት በ16 የአውሮፓ ትልልቅ ከተሞች ትርዒቱን ሊያቀረብ ነው።
3.ድምጻዊ አስቻለው ፈጠነ ከፍተኛ ወጪ አውጥቼበታለሁ ያለውን የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች እንደሚያቀርብ ተናገረ።
4.የደራሲ አድኃኖም ምትኩ ሁለተኛ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።
5.'የተሸመኑ ትውስታዎች' የሥዕል አውደርዕይ ነገ ይከፈታል።
6.ኮሜዲያን እሸቱ መለሠ የኮሜዲ ዝግጅቱን ነገ በለንደን ከተማ ያቀርባል።
እነዚህንና ሌሎችንም የአርትስ ስፔሻል የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።
"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:
https://youtu.be/XBpZW2u7i3M?si=jPI7dBJ4hx5gLsrd
📌መልካም ምሽት
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


12.05.202507:32
📌"ጦቢያ" በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት
"ጦቢያ" የኪነጥበብ ዝግጅት በ9 የአውሮፓ ሃገራት ትርዒቱን ሊያቀርብ እንደሆነ ተሰምቷል።
ይህም የአውሮፓ ጉዞ ጦቢያ ከሆፕ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው ተብሏል።ከወርሐ ሰኔ እስከ ነሐሴ ለሁለት ወራት ገደማ የሚካሄደው ዝግጅቱ የኢትዮጵያዊያንን ባህል ለማስተዋወቅ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም ተገልጿል።
ጦቢያ በዚህ ጉዞው በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት እና በ16 የአውሮፖ ትላልቅ ከተሞች ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
"ጦቢያ" የኪነጥበብ ዝግጅት በ9 የአውሮፓ ሃገራት ትርዒቱን ሊያቀርብ እንደሆነ ተሰምቷል።
ይህም የአውሮፓ ጉዞ ጦቢያ ከሆፕ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው ተብሏል።ከወርሐ ሰኔ እስከ ነሐሴ ለሁለት ወራት ገደማ የሚካሄደው ዝግጅቱ የኢትዮጵያዊያንን ባህል ለማስተዋወቅ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም ተገልጿል።
ጦቢያ በዚህ ጉዞው በዘጠኝ የአውሮፓ ሀገራት እና በ16 የአውሮፖ ትላልቅ ከተሞች ዝግጅቱን ያቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


06.05.202508:55
4 የኢቤኤስ ሰራተኞች በዋስትና እንዲለቀቁ ተወሰነ
በሽብር ወንጀል ጉዳይ ተጠረጥረው በእስር ላይ የሚገኙ አራት የኢቤኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች፤ ዋስትና በማስያዝ እንዲለቀቁ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ።
ሁለት የጣቢያው ሰራተኞችን ጨምሮ 16 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት አስታውቋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በሽብር ወንጀል ጉዳይ ተጠረጥረው በእስር ላይ የሚገኙ አራት የኢቤኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች፤ ዋስትና በማስያዝ እንዲለቀቁ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ።
ሁለት የጣቢያው ሰራተኞችን ጨምሮ 16 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት አስታውቋል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


09.05.202513:41
📌 የነገረ መጻሕፍት አዘጋጆችና ታደሚያን ቅዳሜ "አበሻው " በተሰኘ መጽሐፍ ላይ ይወያያሉ
በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ነገ ቅዳሜ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።በዚህ ሳምንት የተመረጠው መጽሐፍ "አበሻው " የተሰኘ መጽሐፍ ሲሆን በክብር እንግዳነት አያሌው ምትኩ ብሩ ይገኛሉ ተብሏል። የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በዛጎል የመጻህፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጻህፍት ውይይት ነገ ቅዳሜ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።በዚህ ሳምንት የተመረጠው መጽሐፍ "አበሻው " የተሰኘ መጽሐፍ ሲሆን በክብር እንግዳነት አያሌው ምትኩ ብሩ ይገኛሉ ተብሏል። የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


03.05.202513:28
📌"ለጋስ አድማስ" መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው
በገጣሚ ወልደገብርኤል ደሳለኝ(ወገደ) የተዘጋጀው "ለጋስ አድማስ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ በቅርቡ ንባብ ይበቃል ተብሏል።
"ለጋስ አድማስ" የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ350 ብር በቅደመ ሽያጭ ለአንባቢያን ይቀርባል።
መጽሐፉን መግዛት ለሚፈልጉ የባንክ ቁጥር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦ 1000530618661
ወልደገብርኤል ደሳለኝ
ቴሌ ብር ፦0992269755
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
በገጣሚ ወልደገብርኤል ደሳለኝ(ወገደ) የተዘጋጀው "ለጋስ አድማስ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው አዲስ በቅርቡ ንባብ ይበቃል ተብሏል።
"ለጋስ አድማስ" የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ሲሆን በ350 ብር በቅደመ ሽያጭ ለአንባቢያን ይቀርባል።
መጽሐፉን መግዛት ለሚፈልጉ የባንክ ቁጥር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፦ 1000530618661
ወልደገብርኤል ደሳለኝ
ቴሌ ብር ፦0992269755
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


02.05.202510:10
📌የድምጻዊት ዘቢባ ግርማ "እንደምንም" የተሰኘ የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነው
አንጋፋውና ወጣት የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት “እንደምንም" የሙዚቃ አልበም 13 ሙዚቃዎችን በውስጡ የያዘ ሲሆን አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ዓመት እንዲወሰድባትም ተነግሯል።
ለአልበሙ ላይ የሦስት የሙዚቃ ቪዲዮዎች ተሰርቶ የተጠናቀቁ ሲሆን ይህ አልበም ሙሉ በሙሉ በድምጻዊት ዘቢባ ግርማ ፕሮዲዩስ ተደርጓል፡፡
የሙዚቃ አልበሙ ስለ ፍቅር፤ ስለ ምስጋና እና ስለ እናት እና የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮችን ይዳስሳል።
የድምጻዊት ዘቢባ ግርሓጨ"እንደምንም" የተሰኘው አልበም የፊታችን አርብ ግንቦት አንድ በዘቢባ ግርማ ዩቲዩብ ቻናል እና በሁሉም ዓለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለአድማጮች ይቀርባል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
አንጋፋውና ወጣት የሙዚቃ ባለሞያዎች የተሳተፉበት “እንደምንም" የሙዚቃ አልበም 13 ሙዚቃዎችን በውስጡ የያዘ ሲሆን አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ዓመት እንዲወሰድባትም ተነግሯል።
ለአልበሙ ላይ የሦስት የሙዚቃ ቪዲዮዎች ተሰርቶ የተጠናቀቁ ሲሆን ይህ አልበም ሙሉ በሙሉ በድምጻዊት ዘቢባ ግርማ ፕሮዲዩስ ተደርጓል፡፡
የሙዚቃ አልበሙ ስለ ፍቅር፤ ስለ ምስጋና እና ስለ እናት እና የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮችን ይዳስሳል።
የድምጻዊት ዘቢባ ግርሓጨ"እንደምንም" የተሰኘው አልበም የፊታችን አርብ ግንቦት አንድ በዘቢባ ግርማ ዩቲዩብ ቻናል እና በሁሉም ዓለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች አማካኝነት ለአድማጮች ይቀርባል።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
26.04.202506:14
📌የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በአዲስ አበባ ኮንሰርቶች
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በሀገሪቱ ውስጥ የመዝናኛ እና የዕድል ፍላጎትን ለማጣጣም በሚያስችል አዲስ እና ትኩረት የሚስብ አካሄድ ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር በነገው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄዱ ሶስት ታዋቂ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ተከትሎ የፊታችን ግንቦት ወር የሚወጣውን 50 ሚሊዮን ሎተሪ እንደሚያስተዋውቅ ገለጸ።
በሙዚቃ ኮንሰርት ታዳሚዎች በመዝናናታቸው ጎን ለጎን የ50 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ሎተሪ የመቁረጥ ዕድል ይኖራቸዋል ተብሏል።
ዛሬ በሚደረጉ ሶስቱም ኮንሰርቶች ላይ ለሚሳተፋ በነፃ ለሚመዘገቡ ባለዕድለኞች የ50,000 (የሃምሳ ሺህ ብር) ሽልማትም ቀርቧል።
ይህ ልዩ ዕድል ሽልማት ዛሬ በሚካሄዱት በሚሊኒየም አዳራሽ ሽርጉድ ኮንሰርት ፣ በግዮን ሆቴል ልዑል ኮንሰርት እና በማርዮት ሆቴል በሚካሄደው ኤሌጋንስ ኮንሰርቶች ላይ የሚሳተፉትን ተሳታፊዎች ሎተሪ በመቁረጥ በEthiolottery.et ድረ ገጽ ላይ በመመዝገብ በቀላሉ እድለኛ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በሀገሪቱ ውስጥ የመዝናኛ እና የዕድል ፍላጎትን ለማጣጣም በሚያስችል አዲስ እና ትኩረት የሚስብ አካሄድ ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር በነገው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄዱ ሶስት ታዋቂ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ተከትሎ የፊታችን ግንቦት ወር የሚወጣውን 50 ሚሊዮን ሎተሪ እንደሚያስተዋውቅ ገለጸ።
በሙዚቃ ኮንሰርት ታዳሚዎች በመዝናናታቸው ጎን ለጎን የ50 ሚሊዮን ብር ግዙፍ ሎተሪ የመቁረጥ ዕድል ይኖራቸዋል ተብሏል።
ዛሬ በሚደረጉ ሶስቱም ኮንሰርቶች ላይ ለሚሳተፋ በነፃ ለሚመዘገቡ ባለዕድለኞች የ50,000 (የሃምሳ ሺህ ብር) ሽልማትም ቀርቧል።
ይህ ልዩ ዕድል ሽልማት ዛሬ በሚካሄዱት በሚሊኒየም አዳራሽ ሽርጉድ ኮንሰርት ፣ በግዮን ሆቴል ልዑል ኮንሰርት እና በማርዮት ሆቴል በሚካሄደው ኤሌጋንስ ኮንሰርቶች ላይ የሚሳተፉትን ተሳታፊዎች ሎተሪ በመቁረጥ በEthiolottery.et ድረ ገጽ ላይ በመመዝገብ በቀላሉ እድለኛ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።
ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1


24.04.202513:21
📌 የሪፖርተር ጋዜጠኛ ታሰረ
የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ ጋዜጠኛ አበበ ፍቅር ታሰረ፡፡ ጋዜጠኛ አበበ የታሰረው ትናንት ሚያዚያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት አካባቢ ነው፡፡
ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው ከልደታ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች መረጃ በማሰባሰብ ላይ እያለ ሲሆን፣ የታሰረበት ምክንያት እስካሁን ግልጽ አልሆነም፡፡ ጋዜጠኛ አበበ በዕለቱ በፖሊሶች ተይዞ ከመወሰዱ በስተቀር በወቅቱ ወዴት እንደተወሰደና እንደታሰረ ባለመታወቁ፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሪፖርት በማድረግ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ባደረገው ትብብር ጋዜጠኛው በልደታ ክፍል ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጌጃ ሰፈር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩ ታውቋል፡፡
ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው እየሠራው ለነበረው ዘገባ ሚዛኑን ለመጠበቅ፣ የክፍለ ከተማውን ኃላፊዎች ለማነጋገር በሥፍራው በተገኘበት ወቅት ነበር፡፡
ዘገባው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
የሪፖርተር ጋዜጣ ዘጋቢ ጋዜጠኛ አበበ ፍቅር ታሰረ፡፡ ጋዜጠኛ አበበ የታሰረው ትናንት ሚያዚያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት አካባቢ ነው፡፡
ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው ከልደታ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች መረጃ በማሰባሰብ ላይ እያለ ሲሆን፣ የታሰረበት ምክንያት እስካሁን ግልጽ አልሆነም፡፡ ጋዜጠኛ አበበ በዕለቱ በፖሊሶች ተይዞ ከመወሰዱ በስተቀር በወቅቱ ወዴት እንደተወሰደና እንደታሰረ ባለመታወቁ፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሪፖርት በማድረግ የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ባደረገው ትብብር ጋዜጠኛው በልደታ ክፍል ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጌጃ ሰፈር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩ ታውቋል፡፡
ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገው እየሠራው ለነበረው ዘገባ ሚዛኑን ለመጠበቅ፣ የክፍለ ከተማውን ኃላፊዎች ለማነጋገር በሥፍራው በተገኘበት ወቅት ነበር፡፡
ዘገባው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
ለተጨማሪው:https://t.me/EventAddis1
登录以解锁更多功能。