Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
TIKVAH-SPORT avatar
TIKVAH-SPORT
体育
TIKVAH-SPORT avatar
TIKVAH-SPORT
体育
“ ዩሮፓ ሊግ አሸናፊ ሻምፒየንስ ሊግ መግባት የለበትም “ ቬንገር

የቀድሞ የአርሰናል አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር የዩሮፓ ሊግ አሸናፊ ወደ አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ማምራት የለበትም ሲሉ ገልጸዋል።

“ ዩሮፓ ሊግ የሚያሸንፈው ክለብ በቀጥታ በዩሮፓ ሊግ በድጋሜ እንዲሳተፍ ነው ሊደረግ የሚገባው “ ሲሉ አርሴን ቬንገር ተናግረዋል።

“ በተለይ ክለቡ በሻምፒየንስ ሊግ አምስት ክለቦች ከሚያሳትፍ ሊግ ከመጣ መሳተፍ የለበትም “ ሲሉ ነው የተናገሩት።

አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር አክለውም ዩኤፋ ህጉን በድጋሜ ተመልክቶ እንዲያሻሽል ጥሪ አቅርበዋል።

አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር ይህንን የተናገሩት ማንችስተር ዩናይትድ ዩሮፓ ሊግ አሸንፎ ሻምፒየንስ ሊግ መግባት የሚችልበት እድል ስለመኖሩ ሲነጋገሩ ነው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የፒኤስጂ እና አርሰናልን ጨዋታ ማን ይመራዋል ?

የፊታችን ረቡዕ በፒኤስጂ እና አርሰናል መካከል የሚደረገውን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ታውቀዋል።

ፓርክ ዴ ፕሪንስ ስታዲየም ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የመልስ ጨዋታ ጀርመናዊው ዳኛ ፍሊክስ ዝዋየር በመሐል ዳኝነት እንዲመሩት ተመርጠዋል።

ዋና ዳኛው ከዚህ በፊት ሁለት ጊዜ የፒኤስጂን ጨዋታዎች ሲመሩ አንዱን አሸንፎ በአንዱ አቻ ተለያይቷል።

በመጀመሪያው ዙር ፒኤስጂ 1ለ0 ማሸነፉ አይዘነጋውም።

ጨዋታውን ማን ያሸንፋል ?

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe
አርኖልድ ሊቨርፑል እንደሚለቅ አሳወቀ !

የሊቨርፑሉ የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ አሳውቋል።

አሌክሳንደር አርኖልድ በቀጣይ የስፔን ላሊጋውን ክለብ ሪያል ማድሪድ እንደሚቀላቀል ዘ አትሌቲክ አረጋግጧል።

አርኖልድ በሪያል ማድሪድ የስድስት አመታት ውል እንደቀረበለት ሲገለፅ ከሐምሌ ወር መጀመሪያ ቀን ጀምሮ ሎስ ብላንኮዎቹን እንደሚቀላቀል ተነግሯል።

እንግሊዛዊው የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ ሪያል ማድሪድን በነፃ ዝውውር ይቀላቀላል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ለቼልሲ ብሩህ ጊዜ እየመጣ ነው “ ማሬስካ

የሰማያዊዎቹ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ቀጣይ አመታት ለቼልሲ ብሩህ ናቸው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

“ አሁን ባሉን ተጨዋቾች ምክንያት መጪው ጊዜ ለቼልሲ ብሩህ ነው የሚሆነው “ ሲሉ ኢንዞ ማሬስካ ተናግረዋል።

ቼልሲ አሁን ላይ ለሻምፒየንስ ሊግ ቦታ ቢፋለምም ለወደፊት ለትልቅ ነገሮች ይፎካከራል የሚል እምነት አለኝ ብለዋል።

" አሁን ሙሉ ትኩረታችን ለኮንፈረንስ ሊግ ፍፃሜ መድረስ እና የሻምፒየንስ ሊግ ቦታ ይዘን ማጠናቀቅ ነው “ ማሬስካ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የቼልሲ የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ሆነ !

የ 2024/25 የውድድር ዘመን የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት የመሐል ሜዳ ተጨዋቹ ሞይሰስ ካይሴዴ የቼልሲ የተጨዋቾች የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ መመረጥ ችሏል።

በተጨማሪም ሞይሰስ ካይሴዶ የቼልሲ የደጋፊዎች የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ሽልማትን ማሸነፍ ችሏል።

ሞይሰስ ካይሴዶ በተጨዋቾች እና ደጋፊዎች በሁለቱም የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ የተመረጠ አራተኛው የቼልሲ ተጨዋች ሆኗል።

ከዚህ በፊት
- ኤደን ሀዛርድ
- ቲያጎ ሲልቫ እና
- ኮል ፓልመር ባለፈው አመት ሁለቱንም ሽልማት በጋር ያሸነፉ የቼልሲ ተጨዋቾች ናቸው።

@Tikvahethsport   @kidusyoftahe
“ ማህበራዊ ሚዲያ በማይሆን ሰው ተሞልቷል “ ፓልመር

ከአስራ ስምንት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ግብ አግቢነቱ የተመለሰው ኮል ፓልመር በማህበራዊ ሚዲያ ለሚቀርቡ ትችቶች ቦታ እንደማይሰጥ ገልጿል።

“ ማህበራዊ ሚዲያው በማይሆኑ ሰዎች ተሞልቷል “ ያለው ፓልመር እኔ ለእንደዚህ አይነት ነገሮች ቦታ አልሰጥም የሚያሳድርብኝ ተፅዕኖም የለም ብሏል።

“ አንዳንድ ጊዜ ግብ ያለማስቆጠር ችግር በእግርኳስ ሊገጥም ይችላል “ ሲል ፓልመር ተናግሯል።

አክሎም “ ዛሬ ግብ በማስቆጠሬ ደስተኛ ነኝ ነገርግን አንድ ጎል ነው በግብ አግቢነት መቀጠል እና የተሻለ ደረጃ ላይ መድረስ አለብኝ “ ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የመልሱን ጨዋታ እናሸንፋለን “ ሜሪኖ

የመድፈኞቹ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሚኬል ሜሪኖ ቡድናቸው ምንም ማድረግ እንደሚችል ያሳየ መሆኑን ገልጿል።

“ እኛ ከየትኛው የአለም ክለብ ጋር መፎካከር እና ማሸነፍ እንደምንችል አረጋግጠናል “ ሲል ሚኬል ሜሪኖ ተናግሯል።

አክሎም “ የመልሱን የፒኤሴጂ ጨዋታ እንደምናሸንፍ አልጠራጠርም “ ሲል ጥሩ ዝግጅት መደረጉን ተናግሯል።

አርሰናል እስካሁን በታሪኩ ዕለተ ረቡዕ ወደ ሀገረ ፈረንሳይ አቅንቶ ያደረጋቸውን ጨዋታዎች አልተሸነፈም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሊቨርፑል ለአርኖልድ ከፍተኛ ደሞዝ አቅርቦ ነበር !

ሊቨርፑል አሌክሳንደር አርኖልድን በክለቡ ለማቆየት በፕርሚየር ሊጉ ከፍተኛ ተከፋይ የመስመር ተጨዋች የሚያደርገውን ክፍያ አቅርበው እንደነበር ተገልጿል።

በተጨማሪም አርኖልድ ከአለም ከፍተኛ ተከፋይ እግርኳስ ተጨዋቾች አንዱ የሚያደርገው ደሞዝ ቀርቦለት ሳይቀበል መቅረቱ ተነግሯል።

አርኖልድ ለምን ሊቨርፑልን መልቀቅ ፈለገ ?

አሌክሳንደር አርኖልድ ሊቨርፑልን ለመልቀቅ የወሰነው ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ጉዳይ #አለመሆኑን ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።

አርኖልድ አዲስ ፈተና መጋፈጥ እንደፈለገ ሲገለፅ ራሱን በተለየ ቦታ ለመፈተሽ በማሰብ ውሳኔውን እንደወሰነ ተነግሯል።

አርኖልድ አዲስ ክለብ መቀላቀል ያለውን ሙሉ አቅም አውጥቶ እንዲጠቀም እገዛ እንደሚያደርግለት እንደሚያምን ተዘግቧል።

አሌክሳንደር አርኖልድ በሪያል ማድሪድ መጫወት እና ራሱን በድጋሜ ማሳየት እንደሚፈልግ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባርሴሎና ስብስቡን አሳውቋል !

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በነገው የኢንተር ሚላን ጨዋታ የሚጠቀመውን ስብስብ አሳውቋል።

በስብስቡ የፊት መስመር አጥቂው ሮበርት ሌዋንዶውስኪ ተካቷል።

በሌላ በኩል ጁሌስ ኩንዴ እና አሌሀንድሮ ባልዴ በጉዳት ምክንያት ከስብስቡ ውጪ ሆነዋል።

ሙሉ የቡድን ስብስቡ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የኢንተር ሚላን ደጋፊ ነኝ " ጂያኒ ኢንፋንቲኖ

የፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በነገ ምሽቱ የሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የኢንተር ሚላን ደጋፊ መሆናቸውን ገልጸዋል።

“ እኔ የኢንተር ሚላን ደጋፊ እንደሆንኩ ሁሉም ሰው ያውቀዋል “ ሲሉ ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ለማን ድጋፍ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።

በመጀመሪያው ዙር 3ለ3 የተለያዩት ባርሴሎና ኢንተር ሚላን ነገ ምሽት የመልስ ጨዋታቸውን ሳንሲሮ ላይ ያደርጋሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጁቬንቱስ ነጥብ ተጋርቷል !

በሰላሳ አምስተኛ ሳምንት የጣሊያን ሴርያ መርሐ ግብር ጁቬንቱስ ከቦሎኛ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የጁቬንቱስን ግብ ቱራም ኡሌን ከመረብ ሲያሳርፍ ለቦሎኛ ፍሬውለር አስቆጥሯል።

የደረጃ ሰንጠረዡ ምን ይመስላል ?

4️⃣ ጁቬንቱስ - 63 ነጥብ
7️⃣ ቦሎኛ   - 62 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታ ?

ቅዳሜ - ላዝዮ ከ ጁቬንቱስ

አርብ - ኤሲ ሚላን ከ ቦሎኛ

@Tikvahethsport   @kidusyoftahe
The Candlestick Trading Bible is the ultimate guide for traders of all levels, from beginners to experienced professionals. This comprehensive book simplifies the art of candlestick trading, making it easier than ever to understand and apply technical analysis effectively. Whether you are new to trading or looking to refine your strategies, this book provides powerful insights into price action, chart patterns, and trading psychology to help you navigate the financial markets with confidence.

በወርክሾፖቼ ላይ ለተሳታፊዎች ከማቀርባቸው ጥያቄዎች አንዱ አንድ ትሬደር በአንድ ጊዜ ግትርና ተለዋዋጭ ሊሆን የሚገባው እንዴት ነው? የሚለው ነው። መልሱም፦ በሕጎቻችን ላይ ግትር መሆን ሲገባን በጥበቃችን ላይ ደግሞ ተለዋዋጭ መሆን ይጠበቅብናል። በየትኛውም ከፍታና ዝቅታ እንዲሁም የገበያ መዋዠቅ ውስጥ ሊጠብቀን የሚችል ወጥነት ያለው ሕግ የሚያስፈልገን ሲሆን የምንጠብቅው ውጤት ግን በይሆንታ ማሰብ ላይ የተመሰረተና ተለዋዋጭነቱ የሚጠበቅ መሆን አለበት። በሚያሳዝን ሁኔታ ግን አብዛኛው ትሬደር የዚህን ተቃራኒ ነው  የሚከተለው። ሕጎቹ ተለዋዋጭና ደጋግሞ የሚጥሳቸው ሲሆኑ በሚጠብቀው ውጤት ላይ ደግሞ ግትር ነው። "Trading in the zone"

የትኛውም ትሬደር እጅ ላይ ሊኖሩ የሚገባቸው ሁለት መጽሐፍት!!! በሁሉም የመጽሐፍ መደብሮች ያገኟቸዋል።
@Guramaylebooks   0912319263
የአርሰናልን ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ማን ናቸው ?

አርሰናል ከቀናት በኋላ ከፒኤስጂ የሚያደርገውን ጨዋታ ጀርመናዊው ዳኛ ፌሊክስ ዝዋየር በመሀል ዳኝነት እንዲመሩት ተመርጠዋል።

ዋና ዳኛው ፌሊክስ ዝዋየር ከዚህ በፊት በጨዋታ ማጭበርበር ተከሰው ለስድስት ወራት ከዳኝነት ታግደውም እንደነበር ተገልጿል።

ዳኛው በወቅቱ 300 ዩሮ ጉቦ መቀበላቸውን አምነው እንደነበር ተነግሯል።

ጁድ ቤሊንግሀም ዶርትመንድ እያለ ከባየር ሙኒክ በነበረ ጨዋታ ወቅት " ጨዋታ አጭበርባሪ " ሲል ጠርቷቸው እንደነበር አይዘነጋም።

ይሁን እንጂ ፌሊክስ ዝዋየር በዳኝነት ስራቸው መጀመሪያ አካባቢ የተፈጠረው ሁነት ሳያግዳቸው አሁን ላይ በጀርመን ካሉ ጥሩ ዳኞች መካከል አንዱ ናቸው።

ፌሊክስ ዝዋየር ረቡዕ የሚመሩት ሰላሳ ሰባተኛ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታቸውን ሲሆን ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ ይዳኛሉ።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe
ሊቨርፑል ከሪያል ማድሪድ ክፍያ ይቀበላል ?

አሌክሳንደር አርኖልድ በሊቨርፑል ያለው ውል ሲጠናቀቅ ክለቡን በነፃ እንደሚለቅ በዛሬው ዕለት ማሳወቁ ይታወቃል።

ሊቨርፑል አሁን ላይ ከውሉ ማብቂያ ቀደም ብለው የአርኖልድን ኮንትራት ማቋረጥ እንደማይፈልጉ ተገልጿል።

ሪያል ማድሪድ አሌክሳንደር አርኖልድ በአለም ክለቦች ዋንጫ ውድድር እንዲሳተፍላቸው እንደሚፈልጉ ተዘግቧል።

ይሁን እንጂ ሪያል ማድሪድ አርኖልድን ለውድድሩ አንድ ወር ቀድሞ ለመውሰድ ክፍያ መፈፀም እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

ሪያል ማድሪድ 500,000 ፓውንድ ለመክፈል ፍቃደኛ መሆኑ ሲገለፅ ሊቨርፑል ግን ተጨማሪ ክፍያ እንደሚፈልግ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ለጣልያን ለመጫወት ተቃርቤ ነበር " ራፊና

የባርሴሎናው የፊት መስመር ተጨዋች ራፊንሀ ከጣልያን ብሔራዊ ቡድን የቀረበለትን ጥሪ ለመቀበል ተቃርቦ እንደነበር ገልጿል።

“ በ 2020 ከጣልያን ብሔራዊ ቡድን የቀረበልኝን ጥሪ ለመቀበል ተቃርቤ ነበር " ሲል ራፊንሀ አስተያየቱን ሰጥቷል።

“  በአውሮፓ ዋንጫ ልሳተፍ ነበር ነገርግን እንደ እድል ፓስፖርቴ በሰዓቱ ሳይመጣ ቀረ “ ሲል ስላልተሳካበት ምክንያት አስረድቷል።

በወቅቱ ጆርጂንሆን ጨምሮ የጣልያን ተጨዋቾች እና አሰልጣኝ አባላት እሱን ለማሳመን ጥረት ማድረጋቸውን ያነሳው ራፊንሀ የቀረበልኝ እቅድ ትኩረቴን ስቦት ነበር ብሏል።

" ነገርግን በዛን ሰዓት በውስጤ የብራዚል ብሔራዊ ቡድንን ማልያ የመልበስ ተስፋ ነበረኝ “ ራፊና

ብራዚል የተወለደው ራፊንሀ የአባቱ የዘር ሀረግ ከጣልያን የሚመዘዝ እንደሆነ ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Can PlayStation

PlayStation 4  ከ5 Game ጋር በ 32,000ብር ብቻ

2  jestic
500GB
Fc25 + 4game የተጫነበት
Dubai Used
Full accessories
6 month warranty without Power supply

CAN TV
Television ከኛ ጋር በፈለጉት አይነት በቅናሽ እኛ ዘንድ ያገኛሉ

ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል
ብዛት አቅርበናል
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ

🤝Tanks for choice

አድራሻ፡፦
ቁጥር 1  መገናኛ መተባበር ህንፃ

ቁጥር  2 መገናኛ 22 Taxi መያጃ ጡር ህንፃ 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር  F14

ቁጥር 3   ቦሌ ብራስ Celavi burger አጠገብ ዘንባባ ህንፃ  ምድር ላይ

ስልክ፦ 0910529770 ወይም                  0977349492
0914646972  ይደውሉ

ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://t.me/CanPlaystation

                       👍Update Your Life

    Can PlayStation እና Tv Market
“ ለባየር ሙኒክ እንኳን ደስ አላችሁ “ ዣቢ አሎንሶ

የባየር ሌቨርኩሰኑ አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ባየር ሙኒክ በዚህ አመት ቡንደስሊጋውን ማሸነፍ ይገባዋል ብለዋል።

“ ለባየር ሙኒክ እንኳን ደስ አላችሁ “ ያሉት ዣቢ አሎንሶ ባየር ሙኒክ በአመቱ ውስጥ ምርጥ እና ወጥ አቋም አሳይቷል ብለዋል።

አክለውም “ በዚህ አመት ባየር ሙኒክ ዋንጫውን ማሸነፍ ይገባቸዋል “ ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሰማያዊዎቹ ወሳኝ ድል አሳክተዋል !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ሰላሳ አምስተኛ ሳምንት መርሐግብር ቼልሲ ከሊቨርፑል ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

የሰማያዊዎቹን የማሸነፊያ ግቦች ኢንዞ ፈርናንዴዝ ፣ ፓልመር እና ኳንሳህ በራሱ መረብ ላይ ሲያስቆጥሩ ለሊቨርፑል ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።

ኮል ፓልመር ከአስራ ስምንት ጨዋታዎች በኋላ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

1️⃣ ሊቨርፑል :- 82 ነጥብ
5️⃣ ቼልሲ :- 63 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

እሁድ - ኒውካስል ዩናይትድ ከ ቼልሲ

እሁድ - ሊቨርፑል ከ አርሰናል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች ዩኤፋን ሊከሱ ነው !

የአትሌቲኮ ማድሪድ አለምአቀፍ ደጋፊዎች ማህበር የአውሮፓ እግርኳስ ማህበርን ለመክሰስ ገንዘብ ማሰባሰብ መጀመሩን አሳውቋል።

ማህበሩ ዩኤፋን ለመክሰስ የሚያስችለውን ህጋዊ ሂደት ለማስኬድ የሚረዳውን ገንዘብ ለማሰባሰብ ቲሸርቶችን እየሸጠ መሆኑን ይፋ አድርጓል።

የደጋፊዎች ማህበሩ ዩኤፋን የሚከሰው ከወር በፊት በሪያል ማድሪድ ጨዋታ የተፈጠረውን ክስተት ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።

በጨዋታው በነበረ መለያ ምት ጁሊያን አልቫሬዝ ኳስ ሁለት ጊዜ ነክቷል በሚል ያስቆጠረው መለያ ምት በቫር ተሽሮበት እንደነበር ይታወሳል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe
“ ለሊቨርፑል ያለኝ ፍቅር መቼም አይጠፋም “ አርኖልድ

እንግሊዛዊው የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ ሊቨርፑልን ለመልቀቅ ያሳለፈው ውሳኔ ከባድ እንደነበር ገልጿል።

አሌክሳንደር አርኖልድ ስሜታዊ ሆኖ በታየበት የቪዲዮ የስንብት መልዕክቱ ሊቨርፑልን ከሀያ አመታት በኋላ መልቀቁ እርግጥ መሆኑን አሳውቋል።

አርኖልድ ለደጋፊው ባስተላለፈው የስንብት መልዕክትም “ ይህ በህይወቴ የወሰንኩት ከባድ ውሳኔ ነው “ ሲል ገልጿል።

አክሎም “ ሊቨርፑል ሙሉ ህይወቴ ነበር ለክለቡ ያለኝ ፍቅር በጭራሽ አይጠፋም በጣም አመሰግናለሁ “ ሲል ተደምጧል።

አርኖልድ በመልዕክቱ በቀጣይ ወዴት እንደሚያቀና ያልገለፀ ቢሆንም መዳረሻው ሪያል ማድሪድ ስለመሆኑ ታማኝ የመረጃ ምንጮች ማረጋገጣቸው ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አሸናፊዎች ተለይተዋል።

ትክክለኛ ምላሽ ቀድመው የሰጡት ከስር የተገለፁት የቤተሰባችን አባላት ናቸው።

ትክክለኛ ምላሽ የሰጡትን በመፈለጉ ሂደት የተዘለለ እና ያልታየ ካለ ማሳወቅ ይቻላል። Edit የተደረገ መልስ ተቀባይነት አይኖረውም።

ስጦታ የሚበረከትላቸው ቀድመው የመለሱ ሶስት አሸናፊዎች ብቻ ናቸው።

⏩ የአርሰናል እና በርንማውዝ

1ኛ. @Mom_6940
2ኛ. @usernamemother
3ኛ. @A2121Z

⏩ የባርሴሎና እና ሪያል ቫላዶሊድ

1ኛ. @Miku03_26
2ኛ.@MarMa2
3ኛ. @Adulala247

⏩ የሪያል ማድሪድ እና ሴልታቪጎ

1ኛ. @Copy_past_12
2ኛ. @Matomiyasu1
3ኛ. Eba

⏩ የማንችስተር ዩናይትድ እና ብሬንትፎርድ

1ኛ. Esmael
2ኛ. YISAK T

⏩ የቼልሲ እና ሊቨርፑል

1ኛ. @beki697
2ኛ. @Eyobe2
3ኛ. @Yoniyo05

🔴 አሸናፊዎች @Kidusyoftahe ስልክ ቁጥር በማስቀመጥ ሽልማታቸውን መውሰድ ይችላል።

@tikvahethsport
አስተማማኝ እና የኦሪጅናል ጫማዎች  መገኛ ወደሆነው 
Zuqe Mens የቴሌግራም ቻናል በመቀላቀል 
የሚፈልጉትን ጫማ ይዘዙን 
 
📍አድራሻችን-ቦሌ መድኃኒአለም በብርሃኔ አደሬ 50 ሜትር ገባ ብሎ Milkomi Complex 1ኛ ፎቅ

📬inbox @CHATZUQE
🚘ይዘዙ ያሉበት  እናደርሳለን   
     ☎️ 0944201111   

ለመቀላቀል👇 
https://t.me/zuqemen 
https://t.me/joinchat/TtPEOGcPi5YrQSSl
“ ጨዋታውን ማሸነፍ ይገባናል “ ማሬስካ

የሰማያዊዎቹ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ቡድናቸው ሊቨርፑልን በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ መውሰዱን ገልጸዋል።

“ ትልቅ ሶስት ነጥብ ነው ያሳካነው “ ያሉት ማሬስካ በዚህ ሰዓት ጨዋታ ማሸነፍ ያስፈልገን ነበር በማለት ተናግረዋል ።

“ በተለይ የሊጉን አሸናፊ ማሸነፍ ትልቅ ነገር ነው ቀላል አልነበረም ፤ ጨዋታውን ማሸነፍ ይገባናል “ ሲሉ ኢንዞ ማሬስካ ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ አያይዘውም ክርስቶፈር ንኩንኩ በጉዳት ምክንያት እስከ ሁለት ሳምንታት ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🏆🏆🏆 CHAMPION 🇩🇪 🔴

በአሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ የሚመራው ባየር ሙኒክ የ 2024/25 የውድድር አመት የጀርመን ቡንደስሊጋ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።

ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ባየር ሌቨርኩሰን አቻ መለያየቱን ተከትሎ ባየር ሙኒክ የሊጉን አሸናፊነት ማረጋገጥ ችለዋል።

ባየር ሙኒክ የጀርመን ቡንደስሊጋ ዋንጫን ለሰላሳ አራተኛ ጊዜ ማሸነፍ ችለዋል።

እንግሊዛዊው ተጨዋች ሀሪ ኬን በእግርኳስ ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫ ማሸነፍ ችሏል።

ቶማስ ሙለር አስራ ሶስት የቡንደስሊጋ ዋንጫዎችን ያሸነፈ በሊጉ ታሪክ የመጀመሪያው ተጨዋች ሆኗል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
显示 1 - 24 2 858
登录以解锁更多功能。