
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
TGlist рейтинг
0
0
ТипАчык
Текшерүү
ТекшерилбегенИшенимдүүлүк
ИшенимсизОрду
ТилиБашка
Канал түзүлгөн датаSep 24, 2017
TGlistке кошулган дата
Dec 25, 2024Тиркелген топ
"ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ" тобундагы акыркы жазуулар
16.05.202518:16
ተወዳጆች ''በእንተ ስማ ለማርያም'' ይህቺን ጎደሎ ሙሉልን
እስከ አሁን ወደ አካውንቱ 40,000 ብር ገብቶልናል ከታሰበው 52,000 ብር ውስጥ 12,000 ይቀራል። በጎ አድራጊዎች "በእንተ ስማ ለማርያም" ብለን ፊታችሁ ቆመናልና በተጠቀሰው አካውንት እንደ አቅማችሁ ተሳተፉ...
የወልድያ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት በቶች አንድነት ጉባኤ
2071111 0880 89 013
ዓባይ ባንክ
ለተጨማሪ መረጃ ➛ +251 92195 8461
➛ +251 95 327 5024
ገቢ ያደረጋችሁበትን ለመላክ ወይም ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ @natansolo ይጠቀሙ
እስከ አሁን ወደ አካውንቱ 40,000 ብር ገብቶልናል ከታሰበው 52,000 ብር ውስጥ 12,000 ይቀራል። በጎ አድራጊዎች "በእንተ ስማ ለማርያም" ብለን ፊታችሁ ቆመናልና በተጠቀሰው አካውንት እንደ አቅማችሁ ተሳተፉ...
የወልድያ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት በቶች አንድነት ጉባኤ
2071111 0880 89 013
ዓባይ ባንክ
ለተጨማሪ መረጃ ➛ +251 92195 8461
➛ +251 95 327 5024
ገቢ ያደረጋችሁበትን ለመላክ ወይም ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ @natansolo ይጠቀሙ
16.05.202512:38
ተወዳጆች ሆይ! ማለፍ መለወጥ በሌለባት በመንግሥተ ሰማያት ጸጋንና ክብርን እናገኝ ዘንድ በምግባር በትሩፋት እናጊጥ፡፡ በዚህ ዓለም የሚኖረን ውበትና ጌጥ ድንገት ታይቶ የሚጠፋ ነው፡፡ የማይቻል ቢኾንም ምንም በሽታ፣ ኀዘን፣ ብስጭት፣ ይህም የመሳሰለ ኹሉ ባያገኘን እንኳን የዚህ ዓለም ውበትና ጌጥ ሃያ ዓመት ነው፡፡ በወዲያኛው ዓለም የሚሰጠው የሚገኘው ክብር ግን በዝቶ ሲሰጥ ይኖራል እንጂ መቼም ቢኾን መች አያልፍም፡፡ አይለወጥም፡፡ እርጅና የለምና ቆዳው አይጨማደድም፡፡ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስ አያገኘውም፡፡ ኀዘን አያወይበውም፡፡ በዚያ የምናገኘው ክብር፣ ውበት፣ ጌጥ ከዚህ ኹሉ የተለየ ነው፡፡ በዚህ ዓለም የምናገኘው ክብርና ውበት ግን የሚጠፋው ገና ከመምጣቱ ነው፡፡ ቢመጣ እንኳን አድናቂዎቹ ብዙ አይደሉም፡፡ ትሩፋትን ጌጥ ያደረጉ ሰዎች አያደንቁትም፡፡ የሚያደንቁት አመንዝሮች ናቸው፡፡
ስለዚህ ከዚህ ዓለም ከኾነው ክብር ልንለይ ይገባናል፡፡ መንግሥተ ሰማያትን እንወርስ ዘንድ ልንፈልገው የሚገባን ትሩፋትን ነው፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
ስለዚህ ከዚህ ዓለም ከኾነው ክብር ልንለይ ይገባናል፡፡ መንግሥተ ሰማያትን እንወርስ ዘንድ ልንፈልገው የሚገባን ትሩፋትን ነው፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
15.05.202518:06
የፍቅር ሥራ ይህች ናት
ባልንጀራውን የሚረዳውን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ይረዳዋል፡፡ ለወንድሙ የሚነቀፍበትን ስም የሚያወጣውን ፈታሒ በርትዕ እግዚአብሔር እንዲሰደብ ያደርገዋል፡፡ ክፉ ስለ ሠራ ወንድሙን በቤቱ ለብቻው ሆኖ የሚመክረው ሰው ግን በምክሩ ዐዋቂ ይሆናል፡፡ ወንድሙን በዐደባባይ የነቀፈ ግን ኀዘን ያጸናበታል፡፡ ከሰው ተለይቶ ወንድሙን የሚመክር ሰው እነሆ የፍቅሩን ብዛት ያስረዳል፤ በባልንጀሮቹ ፊት የሚነቅፈው ግን የቅናቱን ጽናት ያስረዳል፣ የምቀኝነቱን ጽናት አስረዳ፡፡
ወዳጁን ተሠውሮ የሚመክር ሰው ብልህ ባለመድኃኒት ነው:: ያ እንዳዳነው መክሮ አስተምሮ ያድነዋልና፡፡ ወንድሙን በብዙ ሰው ፊት የሚያመሰግነው ሰው እሱ እውነተኛ ጠላቱ ነው፣ በውዳሴ ከንቱ ይጎዳ ብሎ ነውና።
ኀዘን ያለበት የርሕራሄ ምልክቱ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ማለት ነው። የጠማማ ምልክቱ ጸብ ክርክር ነው፡፡ ወደ ክብር የሚያደርስ ረብህ ጥቅም ያግኝ ብሎ የሚመክር፣ የሚያስተምር በፍቅር ይመክረዋል፣ ያስተምረዋል፡፡ ቂም በቀል የሚሻ ሰው ፍቅር የለውም፡፡ አንድም እበቀለዋለሁ ብሎ የሚመክር ከፍቅር የተለየ ነው፡፡
ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር በፍቅር ይመክራል፣ ያስተምራል፣ እበቀላለሁ ብሎ ያይደል፡፡ እሱስ በምሳሌው የተፈጠረው ሰውን ለማዳን ይገሥጻል፡፡ አንድ ጊዜስ እንኳን ቂም አይዝም፣ መዓትን አያዘጋጅም፡፡ የፍቅር ሥራ ይህች ናት፣ በቅንነት ትገኛለች፡፡ ቂም ለመያዝ እበቀላለሁ አትልም፣ በፍቅር ሰውን መናገር ነው።
ብልህ የሚሆን ቅን ሰው ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይመስለዋል፡፡ ሰውን ክፉ ስላደረገ እበቀለዋለሁ ብሎ አይገሥጸውም፣ ሊመክረው ወዶ ነው እንጂ ሌሎችንም ለማስፈራት ነው እንጂ። ተግሣጽስ በፍቅር ካልሆነ ተግሣጽ አይባልም፡፡ በጎ ነገር ያደርግልኛል ብሎ በጎ የሚሠራ ኋላ ፈጥኖ ይተዋል፡፡
(ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ - በዲ/ን ሞገስ)
ባልንጀራውን የሚረዳውን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ይረዳዋል፡፡ ለወንድሙ የሚነቀፍበትን ስም የሚያወጣውን ፈታሒ በርትዕ እግዚአብሔር እንዲሰደብ ያደርገዋል፡፡ ክፉ ስለ ሠራ ወንድሙን በቤቱ ለብቻው ሆኖ የሚመክረው ሰው ግን በምክሩ ዐዋቂ ይሆናል፡፡ ወንድሙን በዐደባባይ የነቀፈ ግን ኀዘን ያጸናበታል፡፡ ከሰው ተለይቶ ወንድሙን የሚመክር ሰው እነሆ የፍቅሩን ብዛት ያስረዳል፤ በባልንጀሮቹ ፊት የሚነቅፈው ግን የቅናቱን ጽናት ያስረዳል፣ የምቀኝነቱን ጽናት አስረዳ፡፡
ወዳጁን ተሠውሮ የሚመክር ሰው ብልህ ባለመድኃኒት ነው:: ያ እንዳዳነው መክሮ አስተምሮ ያድነዋልና፡፡ ወንድሙን በብዙ ሰው ፊት የሚያመሰግነው ሰው እሱ እውነተኛ ጠላቱ ነው፣ በውዳሴ ከንቱ ይጎዳ ብሎ ነውና።
ኀዘን ያለበት የርሕራሄ ምልክቱ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ማለት ነው። የጠማማ ምልክቱ ጸብ ክርክር ነው፡፡ ወደ ክብር የሚያደርስ ረብህ ጥቅም ያግኝ ብሎ የሚመክር፣ የሚያስተምር በፍቅር ይመክረዋል፣ ያስተምረዋል፡፡ ቂም በቀል የሚሻ ሰው ፍቅር የለውም፡፡ አንድም እበቀለዋለሁ ብሎ የሚመክር ከፍቅር የተለየ ነው፡፡
ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር በፍቅር ይመክራል፣ ያስተምራል፣ እበቀላለሁ ብሎ ያይደል፡፡ እሱስ በምሳሌው የተፈጠረው ሰውን ለማዳን ይገሥጻል፡፡ አንድ ጊዜስ እንኳን ቂም አይዝም፣ መዓትን አያዘጋጅም፡፡ የፍቅር ሥራ ይህች ናት፣ በቅንነት ትገኛለች፡፡ ቂም ለመያዝ እበቀላለሁ አትልም፣ በፍቅር ሰውን መናገር ነው።
ብልህ የሚሆን ቅን ሰው ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይመስለዋል፡፡ ሰውን ክፉ ስላደረገ እበቀለዋለሁ ብሎ አይገሥጸውም፣ ሊመክረው ወዶ ነው እንጂ ሌሎችንም ለማስፈራት ነው እንጂ። ተግሣጽስ በፍቅር ካልሆነ ተግሣጽ አይባልም፡፡ በጎ ነገር ያደርግልኛል ብሎ በጎ የሚሠራ ኋላ ፈጥኖ ይተዋል፡፡
(ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ - በዲ/ን ሞገስ)
15.05.202509:58
የመረሻውን ግብ እያሰቡ ልጆችን ማሳደግ ማለት እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብ የዋሃን፣ ክፉውን ሳይኾን በጎውን ለማወቅ ትጉሃን፣ የዲያብሎስን ሽንገላ ለማስተዋል ጠቢባን፣ የቅዱሳንን ፋና ለመከተል የቃሉን ወተት የሚጠጡ ንጹሐን አድርጎ ማሳደግ ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን እኛ አየናቸውም አላየናቸውም በሕሊናቸው ጓዳ በልቡናቸው ሰሌዳ ላይ መንግሥተ እግዚአብሔርን መቅረፅ ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ስንጠራቸው አቤት ስናዛቸው ወዴት የሚሉንን ሳይኾን ትዕግሥትን፣ ቸርነትን፣ በጎነትን፣ እምነትን፣ የውሃትን ራስን መግዛትን፥ በአጭር ቃል የመንፈስ ፍሬዎችን ገንዘብ ያደረጉ ልጆችን ማሳደግ ነው። (ገላ.5፥22-24)
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን የገዛ ክብራቸውን እንዲያውቁና በዚያ መሠረት እንዲያድጉ - ይኸውም የእግዚእብሔር ልጆች ክርስቶስን የሚመስሉ በእግዚእብሔር አርአያና አምሳል ቅዱሳን እንዲኾኑ አድርጎ ማሳደግ ነው። (ዘፍ. 1፥26)
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን የእኛ ንብረት እንዲኾኑ ሳይኾን የእዚአብሔር ልጆች እንዲኾኑ አድርጎ ማሳደግ ው። መጥምቁ ዮሐንስ እስራኤላውያንን ለክርስቶስ ያዘጋጃቸው እንደ ነበረ፥ እኛም በዚያ መንገድ ልጆቻችን የእግዚአብሔር ልጆቸ እንዲኾኑ ማዘጋጀት ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት የልጆቻችንን መጥፎ ጠባይ ከማራቅና እንዲታዙን ከማድረግ በላይ፡ እግዚአብሔርን በፍጹም ኃይላቸው እንዲወድዱ ማድረግ ነው። ቅዱሳንን እንዲያፈቅሩ በቃል ኪዳናቸው ታምነው እርሱን እንዲመስሉ ማድረግ ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት እስተዳደግ ማለት ልጆቻችን እንዳይጣሉ ስናደርጋቸው መንፈሳዊ ሕይወትና የቅድስና መንገድ ምን እንደ ኾነ በሚያሳይ መልኩ ማሳደግ ነው። መጀመሪያ ላይ ባነሣሁት ምሳሌ ላይ ለምሳሌ "ዮሐንስ! መጫወቻውን አቀብለኝ" ብለውና እያንገራገረም ቢኾን ቢሰጠኝ፥ እኔም ቀጥዬ "መጫወቻውን እዚህ አስቀምጠዋለሁ፤ ከእራት በኋላም እንዴት በየተራ እንደምትጫወቱ ስትነግሩኝ ልሰጣችሁ እችላለሁ" ብለው ለጊዜው ኹለቱም መፍትሔ ባያመጡም እንደ አሁኑ እንዳልወስድባቸው ለሌላ ጊዜ እንዴት መጫወት እንዳለባቸው ከማሰብ ዝም አሉም።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን ከላይ ያነሣናቸውን ምግባራት በአንድ ቀን ሊይዙልን እንደማይችሉ ዐውቆ እነዚህን ቀሰ በቀስ እስኪይዟቸው ድረስ ሊማሩ የሚችሉበትን ኸኔታ እያመቻቸን ጊዜ ልንሰጣቸው እንደሚገባን ተረድቶ መታተር ነው። ልጅ ማሳደግ የአጭር ጊዜ ሳይኾን የረጅም ጊዜ ኃላፊነት ነውና። ልጆቻችን በኹለት ሳምንት ወይም በአንድ ወር እንዲያውቁትና እንዲይዙት የምንፈልገው አንድ ነገር አልያዙም ማለት ሙከራችን ስለማይሠራ ነው ማለት ላይኾን ይችላል፤ ጊዜ የሚፈልግ ይኾናል እንጂ። ልጅ ማሳደግ ትዕግሥት ይጠይቃል። ልጆቻችን እንዲይዙት የምንፈልገው ነገር ለመዝ እየጣሩ እንደ ኾነ ርግጠኛ እስከ ኾንን ድረስ ዕድል በመስጠት ልንታገሣቸው ይገባናል።"
(#ትንሿ_ቤተ_ክርስቲያን ገጽ 444-445
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ )
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን እኛ አየናቸውም አላየናቸውም በሕሊናቸው ጓዳ በልቡናቸው ሰሌዳ ላይ መንግሥተ እግዚአብሔርን መቅረፅ ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ስንጠራቸው አቤት ስናዛቸው ወዴት የሚሉንን ሳይኾን ትዕግሥትን፣ ቸርነትን፣ በጎነትን፣ እምነትን፣ የውሃትን ራስን መግዛትን፥ በአጭር ቃል የመንፈስ ፍሬዎችን ገንዘብ ያደረጉ ልጆችን ማሳደግ ነው። (ገላ.5፥22-24)
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን የገዛ ክብራቸውን እንዲያውቁና በዚያ መሠረት እንዲያድጉ - ይኸውም የእግዚእብሔር ልጆች ክርስቶስን የሚመስሉ በእግዚእብሔር አርአያና አምሳል ቅዱሳን እንዲኾኑ አድርጎ ማሳደግ ነው። (ዘፍ. 1፥26)
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን የእኛ ንብረት እንዲኾኑ ሳይኾን የእዚአብሔር ልጆች እንዲኾኑ አድርጎ ማሳደግ ው። መጥምቁ ዮሐንስ እስራኤላውያንን ለክርስቶስ ያዘጋጃቸው እንደ ነበረ፥ እኛም በዚያ መንገድ ልጆቻችን የእግዚአብሔር ልጆቸ እንዲኾኑ ማዘጋጀት ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት የልጆቻችንን መጥፎ ጠባይ ከማራቅና እንዲታዙን ከማድረግ በላይ፡ እግዚአብሔርን በፍጹም ኃይላቸው እንዲወድዱ ማድረግ ነው። ቅዱሳንን እንዲያፈቅሩ በቃል ኪዳናቸው ታምነው እርሱን እንዲመስሉ ማድረግ ነው።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት እስተዳደግ ማለት ልጆቻችን እንዳይጣሉ ስናደርጋቸው መንፈሳዊ ሕይወትና የቅድስና መንገድ ምን እንደ ኾነ በሚያሳይ መልኩ ማሳደግ ነው። መጀመሪያ ላይ ባነሣሁት ምሳሌ ላይ ለምሳሌ "ዮሐንስ! መጫወቻውን አቀብለኝ" ብለውና እያንገራገረም ቢኾን ቢሰጠኝ፥ እኔም ቀጥዬ "መጫወቻውን እዚህ አስቀምጠዋለሁ፤ ከእራት በኋላም እንዴት በየተራ እንደምትጫወቱ ስትነግሩኝ ልሰጣችሁ እችላለሁ" ብለው ለጊዜው ኹለቱም መፍትሔ ባያመጡም እንደ አሁኑ እንዳልወስድባቸው ለሌላ ጊዜ እንዴት መጫወት እንዳለባቸው ከማሰብ ዝም አሉም።
ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን ከላይ ያነሣናቸውን ምግባራት በአንድ ቀን ሊይዙልን እንደማይችሉ ዐውቆ እነዚህን ቀሰ በቀስ እስኪይዟቸው ድረስ ሊማሩ የሚችሉበትን ኸኔታ እያመቻቸን ጊዜ ልንሰጣቸው እንደሚገባን ተረድቶ መታተር ነው። ልጅ ማሳደግ የአጭር ጊዜ ሳይኾን የረጅም ጊዜ ኃላፊነት ነውና። ልጆቻችን በኹለት ሳምንት ወይም በአንድ ወር እንዲያውቁትና እንዲይዙት የምንፈልገው አንድ ነገር አልያዙም ማለት ሙከራችን ስለማይሠራ ነው ማለት ላይኾን ይችላል፤ ጊዜ የሚፈልግ ይኾናል እንጂ። ልጅ ማሳደግ ትዕግሥት ይጠይቃል። ልጆቻችን እንዲይዙት የምንፈልገው ነገር ለመዝ እየጣሩ እንደ ኾነ ርግጠኛ እስከ ኾንን ድረስ ዕድል በመስጠት ልንታገሣቸው ይገባናል።"
(#ትንሿ_ቤተ_ክርስቲያን ገጽ 444-445
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ )
15.05.202507:24
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አዲስ አበባ ገቡ!
ወደ ሀገር እንዲገቡ ፈቃድ የተሰጣቸው ሦስቱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገቡ
ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ የገቡት አባቶች
* ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣
* ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ እና
* ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ሲሆኑ፤
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዓን አባቶች ተገኝተው አቀባበል እንዳደረጉላቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ሚዲያ ዘግበዋል።
ወደ ሀገር እንዲገቡ ፈቃድ የተሰጣቸው ሦስቱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገቡ
ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ የገቡት አባቶች
* ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣
* ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ እና
* ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ሲሆኑ፤
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዓን አባቶች ተገኝተው አቀባበል እንዳደረጉላቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ሚዲያ ዘግበዋል።
15.05.202503:24
''በእንተ ስማ ለማርያም''
እስከ አሁን ወደ አካውንቱ 40,000 ብር ገብቶልናል ከታሰበው 52,000 ብር ውስጥ 12,000 ይቀራል። በጎ አድራጊዎች "በእንተ ስማ ለማርያም" ብለን ፊታችሁ ቆመናልና በተጠቀሰው አካውንት እንደ አቅማችሁ ተሳተፉ...
የወልድያ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት በቶች አንድነት ጉባኤ
2071111 0880 89 013
ዓባይ ባንክ
ለተጨማሪ መረጃ ➛ +251 92195 8461
➛ +251 95 327 5024
ገቢ ያደረጋችሁበትን ለመላክ ወይም ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ @natansolo ይጠቀሙ
እስከ አሁን ወደ አካውንቱ 40,000 ብር ገብቶልናል ከታሰበው 52,000 ብር ውስጥ 12,000 ይቀራል። በጎ አድራጊዎች "በእንተ ስማ ለማርያም" ብለን ፊታችሁ ቆመናልና በተጠቀሰው አካውንት እንደ አቅማችሁ ተሳተፉ...
የወልድያ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት በቶች አንድነት ጉባኤ
2071111 0880 89 013
ዓባይ ባንክ
ለተጨማሪ መረጃ ➛ +251 92195 8461
➛ +251 95 327 5024
ገቢ ያደረጋችሁበትን ለመላክ ወይም ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ @natansolo ይጠቀሙ
14.05.202519:58
"ልጆቻችንን ቸር እንዲሆኑ፣ ገር እንዲሆኑ፣ ይቅር ባይ እንዲሆኑ፣ ለጋስ እንዲሆኑ፣ ባልንጀሮቻቸውን እንዲወዱ ስናስተምር፣ በዘመኑ እንዳይወሰዱ እናደርጋለን። በጎነትን በነፍሳቸው ውስጥ እናሰርጻለን፤ የእግዚአብሔርንም መልክ በእነርሱ ውስጥ እንገልጣለን። ምንም እንኳ ሺህ በጎነቶችን ብናደርግም፣ መልካምነታችን በእግዚአብሔር ፍቅር ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት።"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)


14.05.202517:11
14.05.202517:11
በመጨረሻም
የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ አፈጻጸማችን በመገምገም ለቀጣዩ ጊዜ የሥራ አቅጣጫን የሚያስቀምጠው የርክበ ካህናቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለኦርቶዶክሳውያን ሕዝበ ክርስቲያን እናበስራለን፤
እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
(ምንጭ EOTC)
የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ አፈጻጸማችን በመገምገም ለቀጣዩ ጊዜ የሥራ አቅጣጫን የሚያስቀምጠው የርክበ ካህናቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለኦርቶዶክሳውያን ሕዝበ ክርስቲያን እናበስራለን፤
እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
(ምንጭ EOTC)
14.05.202517:11
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ ያስተላለፉት መልእክት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
* ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
* ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
*ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሐዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም አክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው አባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለርክበ ካህናት ጉባኤ አደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሐዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለኣሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤ይህ ሐዋርያዊ አስተምህሮ የኛን ተልእኮና ተልእኮው ያስፈለገበትን ምክንያት አጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሐዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚአብሔር መታዘዝ አቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤
ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገላት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቧል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነ መሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሐዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር አገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በአውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልዕኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሐዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማእከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ሊያሰማራ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ሥራ በመሥራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ የምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ አሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መሥራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን ዓቅምና ብቃት በአግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን አለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሐቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና አባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሠራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም አይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ስብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ አለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው አገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው አገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ አንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ አገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና አንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና አርአያ ሆነን መሥራት ይገባናል፤
በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መሥራት አለብን፤እንዳጋጣሚ ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንግልት የተላቀቀበት ጊዜ ብዙ እንዳልሆነ ይታወቃል፤ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው፤ እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት አካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ፤ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ፤ በዚህ አማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ አድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ አድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
* ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
* ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
*ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሐዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም አክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው አባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለርክበ ካህናት ጉባኤ አደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሐዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለኣሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤ይህ ሐዋርያዊ አስተምህሮ የኛን ተልእኮና ተልእኮው ያስፈለገበትን ምክንያት አጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሐዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚአብሔር መታዘዝ አቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤
ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገላት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቧል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነ መሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሐዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር አገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በአውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልዕኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሐዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማእከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ሊያሰማራ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ሥራ በመሥራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ የምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ አሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መሥራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን ዓቅምና ብቃት በአግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን አለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሐቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና አባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሠራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም አይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ስብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ አለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው አገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው አገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ አንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ አገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና አንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና አርአያ ሆነን መሥራት ይገባናል፤
በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መሥራት አለብን፤እንዳጋጣሚ ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንግልት የተላቀቀበት ጊዜ ብዙ እንዳልሆነ ይታወቃል፤ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው፤ እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት አካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ፤ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ፤ በዚህ አማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ አድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ አድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው፤
13.05.202517:00
ልዩ ፍርድ ቤት
ብዙዎቻችን ወንድሞቻችንን ለማማት የፈጠንን ነን፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተን የሰውን ጉድፍ ለማውጣት የምንቻኮል ነን፡፡ በወንድሞቻችን ላይ ለመፍረድ፥ እኅቶቻችንን ለመኰነን የምንጣደፍ ነን፡፡
ወዳጄ ሆይ! መፍረድ የእግዚአብሔር እንጂ ያንተ ሥልጣን አይደለምና ተጠንቀቅ፡፡ እህቴ ሆይ! በአምላክ ዙፋን ላይ ለመቀመጥ አታስቢ፡፡
ወዳጄ ሆይ! መፍረድ አማረኽን? እንኪያስ ምንም ወቀሳ የሌለበት፣ ይልቁንም ብዙ ጥቅም የሚያስገኝ የፍርድ ችሎት አለልህ፡፡ በራስህ ላይ መፍረድ ትችላለህና ተቀመጥ፡፡ ከኹሉም አስቀድመህ የበደልህን መዝገብ በፊትህ አኑረው፡፡ ነፍስህ የሠራችውንም ወንጀል በሙሉ በጥንቃቄ መርምር፡፡ ከዚያም “ነፍሴ ሆይ! ይኽንና ያንን በደል የፈጸምሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ የበደለችበትን ምክንያት ትታ በሌሎች ላይ ለማሳበብና በሌሎች ላይ ለመፍረድ ከዠመረችም “የተከሰስሽው በራስሽ ወንጀል እንጂ በሌላ ሰው ወንጀል አይደለም፡፡ እዚኽ ፍርድ ቤት የመጣሽው ስለእነዚያ ሰዎች ለመመስከር አይደለም፡፡ ስለዚኸ ንገሪኝ! ይኽን ያኽል በደል የፈጸምሽው፣ ይኽን ያንን ኹሉ ጥፋት ያጠፋሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ ዘወትር ይኽን የመሰለ አስጨናቂ ጥያቄ ጠይቃት፡፡ አፍራ የምትመልሰው ከሌላትም አስፈላጊውን ፍርድ (ቀኖና) ወስንባት፡፡ ይኽን ልዩ ፍርድ ቤት ዘወትር የምትቀመጥ ከኾነ ያንን የእሳት ባሕር፣ ያ እሳቱ የማይጠፋው ትሉ የማያንቀላፋው ስቃይ በልቡናህ ይቀረጻል፡፡
“ወደ እኔ መጥቶ ነው፤ እርሱ አታልሎኝ ነው፤ እርሱ ፈትኖኝ ነው" እያለች በዲያብሎስ እንድታመካኝም አትፍቀድላት፡፡ ይልቁንም፡- "አንቺ ባትፈቅጂ ነው እንጂ እነዚኸ ኹሉ በአንቺ ላይ ሥልጣን የላቸውም" ብለህ ንገራት፡፡ "እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፤ የምኖረውም በዚኽ ኃጢአት በሞላበት ዓለም ነው" ካለችህም "ይኽ ኹሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ ለብሰው በዚኽ ዓለም ኑረው ጻድቃንና ሰማዕታት ኾነዋል፡፡ አንቺ ራስሽ አንዳንድ ጊዜ መልካም ምግባራትን ስታደርጊ ይኸ አኹን የምታሳብቢበትን ሥጋ ለብሰሽ ነው" በላት፡፡ ይኽን ስትላት ቢያማትም እጅህን አታንሳባት፡፡ ምክንያቱም ቀኖናው ከሞት የሚታደጋት መንፈሳዊ ልምምድ እንጂ የሚገድላት ቅጣት አይደለምና፡፡ ስለዚኽ ምክንያት የምታበዛብህ ከኾነ “እባብ አሳተኝ" ብላ ከተጠያቂነት ያለመለጠችውን ሔዋንን አስታውሳት፡፡
ይኽን ኹሉ ስታደርግም ከአጠገብህ ማንም አይኑር፡፡ የሚረብሽህ ሰው ከአጠገብህ አይገኝ፡፡ ይልቁንም ዳኛ በፍርድ ወንበር ላይ እንደሚቀመጥ አንተም በፍርድ ወንበር ፈንታ በምቹ ጊዜና ቦታ በጽሞና ተቀመጥ፡፡ ነቢዩ “በመኝታችሁ ሳላችሁ በልባችሁ የምታስቡት ይታወቃችሁ" እንዳለው /መዝ.4፥4/ ይኽ ቦታና ጊዜ ከኹሉም ይልቅ ተስማሚ ነውና እራትህን ከበላህ በኋላ ዘወትር ይኽን የፍርድ ወንበር ወደ መኝታ ክፍልህ ይዘኸው ሒድ፡፡ ዕለት ዕለት ይኸን የምታደርግ ከኾነ ሐዋርያው “እኛ በራሳችን ብንፈርድ ኖሮ ባልተፈረደብንም ነበር" እንዲል (1ኛ ቆሮ.1፥31) በዚያ አስፈሪው የፍርድ ወንበር ፊት ያለ ፍርሐት ትቆማለህ፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች ገጽ 42-42 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
ብዙዎቻችን ወንድሞቻችንን ለማማት የፈጠንን ነን፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተን የሰውን ጉድፍ ለማውጣት የምንቻኮል ነን፡፡ በወንድሞቻችን ላይ ለመፍረድ፥ እኅቶቻችንን ለመኰነን የምንጣደፍ ነን፡፡
ወዳጄ ሆይ! መፍረድ የእግዚአብሔር እንጂ ያንተ ሥልጣን አይደለምና ተጠንቀቅ፡፡ እህቴ ሆይ! በአምላክ ዙፋን ላይ ለመቀመጥ አታስቢ፡፡
ወዳጄ ሆይ! መፍረድ አማረኽን? እንኪያስ ምንም ወቀሳ የሌለበት፣ ይልቁንም ብዙ ጥቅም የሚያስገኝ የፍርድ ችሎት አለልህ፡፡ በራስህ ላይ መፍረድ ትችላለህና ተቀመጥ፡፡ ከኹሉም አስቀድመህ የበደልህን መዝገብ በፊትህ አኑረው፡፡ ነፍስህ የሠራችውንም ወንጀል በሙሉ በጥንቃቄ መርምር፡፡ ከዚያም “ነፍሴ ሆይ! ይኽንና ያንን በደል የፈጸምሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ የበደለችበትን ምክንያት ትታ በሌሎች ላይ ለማሳበብና በሌሎች ላይ ለመፍረድ ከዠመረችም “የተከሰስሽው በራስሽ ወንጀል እንጂ በሌላ ሰው ወንጀል አይደለም፡፡ እዚኽ ፍርድ ቤት የመጣሽው ስለእነዚያ ሰዎች ለመመስከር አይደለም፡፡ ስለዚኸ ንገሪኝ! ይኽን ያኽል በደል የፈጸምሽው፣ ይኽን ያንን ኹሉ ጥፋት ያጠፋሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ ዘወትር ይኽን የመሰለ አስጨናቂ ጥያቄ ጠይቃት፡፡ አፍራ የምትመልሰው ከሌላትም አስፈላጊውን ፍርድ (ቀኖና) ወስንባት፡፡ ይኽን ልዩ ፍርድ ቤት ዘወትር የምትቀመጥ ከኾነ ያንን የእሳት ባሕር፣ ያ እሳቱ የማይጠፋው ትሉ የማያንቀላፋው ስቃይ በልቡናህ ይቀረጻል፡፡
“ወደ እኔ መጥቶ ነው፤ እርሱ አታልሎኝ ነው፤ እርሱ ፈትኖኝ ነው" እያለች በዲያብሎስ እንድታመካኝም አትፍቀድላት፡፡ ይልቁንም፡- "አንቺ ባትፈቅጂ ነው እንጂ እነዚኸ ኹሉ በአንቺ ላይ ሥልጣን የላቸውም" ብለህ ንገራት፡፡ "እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፤ የምኖረውም በዚኽ ኃጢአት በሞላበት ዓለም ነው" ካለችህም "ይኽ ኹሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ ለብሰው በዚኽ ዓለም ኑረው ጻድቃንና ሰማዕታት ኾነዋል፡፡ አንቺ ራስሽ አንዳንድ ጊዜ መልካም ምግባራትን ስታደርጊ ይኸ አኹን የምታሳብቢበትን ሥጋ ለብሰሽ ነው" በላት፡፡ ይኽን ስትላት ቢያማትም እጅህን አታንሳባት፡፡ ምክንያቱም ቀኖናው ከሞት የሚታደጋት መንፈሳዊ ልምምድ እንጂ የሚገድላት ቅጣት አይደለምና፡፡ ስለዚኽ ምክንያት የምታበዛብህ ከኾነ “እባብ አሳተኝ" ብላ ከተጠያቂነት ያለመለጠችውን ሔዋንን አስታውሳት፡፡
ይኽን ኹሉ ስታደርግም ከአጠገብህ ማንም አይኑር፡፡ የሚረብሽህ ሰው ከአጠገብህ አይገኝ፡፡ ይልቁንም ዳኛ በፍርድ ወንበር ላይ እንደሚቀመጥ አንተም በፍርድ ወንበር ፈንታ በምቹ ጊዜና ቦታ በጽሞና ተቀመጥ፡፡ ነቢዩ “በመኝታችሁ ሳላችሁ በልባችሁ የምታስቡት ይታወቃችሁ" እንዳለው /መዝ.4፥4/ ይኽ ቦታና ጊዜ ከኹሉም ይልቅ ተስማሚ ነውና እራትህን ከበላህ በኋላ ዘወትር ይኽን የፍርድ ወንበር ወደ መኝታ ክፍልህ ይዘኸው ሒድ፡፡ ዕለት ዕለት ይኸን የምታደርግ ከኾነ ሐዋርያው “እኛ በራሳችን ብንፈርድ ኖሮ ባልተፈረደብንም ነበር" እንዲል (1ኛ ቆሮ.1፥31) በዚያ አስፈሪው የፍርድ ወንበር ፊት ያለ ፍርሐት ትቆማለህ፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች ገጽ 42-42 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
13.05.202512:58
“ደጋግመህ ኃጢአት ብትሠራም ደጋግመህ ንስሐ ግባ፡፡ ቤተክርስቲያን ሐኪም ቤት እንጂ ፍርድ ቤት አይደለችምና፡፡”
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
13.05.202507:45
''በእንተ ስማ ለማርያም''
እስከ አሁን ወደ አካውንቱ 40,000 ብር ገብቶልናል ከታሰበው 52,000 ብር ውስጥ 12,000 ይቀራል። በጎ አድራጊዎች "በእንተ ስማ ለማርያም" ብለን ፊታችሁ ቆመናልና በተጠቀሰው አካውንት እንደ አቅማችሁ ተሳተፉ...
የወልድያ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት በቶች አንድነት ጉባኤ
2071111 0880 89 013
ዓባይ ባንክ
ለተጨማሪ መረጃ ➛ +251 92195 8461
➛ +251 95 327 5024
ገቢ ያደረጋችሁበትን ለመላክ ወይም ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ @natansolo ይጠቀሙ
እስከ አሁን ወደ አካውንቱ 40,000 ብር ገብቶልናል ከታሰበው 52,000 ብር ውስጥ 12,000 ይቀራል። በጎ አድራጊዎች "በእንተ ስማ ለማርያም" ብለን ፊታችሁ ቆመናልና በተጠቀሰው አካውንት እንደ አቅማችሁ ተሳተፉ...
የወልድያ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት በቶች አንድነት ጉባኤ
2071111 0880 89 013
ዓባይ ባንክ
ለተጨማሪ መረጃ ➛ +251 92195 8461
➛ +251 95 327 5024
ገቢ ያደረጋችሁበትን ለመላክ ወይም ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ @natansolo ይጠቀሙ
Рекорддор
16.05.202523:59
45.3KКатталгандар13.04.202519:14
200Цитация индекси21.03.202505:44
5.7K1 посттун көрүүлөрү14.05.202513:51
4.8K1 жарнама посттун көрүүлөрү02.05.202523:59
13.21%ER21.03.202505:44
13.13%ERRӨнүгүү
Катталуучулар
Citation индекси
Бир посттун көрүүсү
Жарнамалык посттун көрүүсү
ER
ERR
Көбүрөөк функцияларды ачуу үчүн кириңиз.