
ቅዳጅ ገፆች🫀📝
እነዛ የኖርናቸው መኖሮች ምንኛ ነበሩ🗒
.
We're gonna share our life lessons like a friend like a soul mate 🖊
Dm @Kal_awit fyi‼️
.
We're gonna share our life lessons like a friend like a soul mate 🖊
Dm @Kal_awit fyi‼️
TGlist рейтингі
0
0
ТүріҚоғамдық
Растау
РасталмағанСенімділік
СенімсізОрналасқан жері
ТілБасқа
Канал құрылған күніЖовт 09, 2024
TGlist-ке қосылған күні
Лист 11, 2024Қосылған топ
"ቅዳጅ ገፆች🫀📝" тобындағы соңғы жазбалар
03.05.202520:02
መኖር በእናንተ ዕይታ ምንድነው?
Қайта жіберілді:
የራስ ገፅ📖

29.03.202516:02
የአይሁድ ዘር በሙሉ ገዳይ ነው ተባለ ፣
ሞትን የገደለ ክርስቶስ እያለ ።
ሎሚ ተራተራ
https://t.me/yarso21
https://t.me/yarso21
ሞትን የገደለ ክርስቶስ እያለ ።
ሎሚ ተራተራ
https://t.me/yarso21
https://t.me/yarso21


29.03.202511:35
Guys lets be friends on ig🫶🏼
Follow , i will follow back📌
https://www.instagram.com/classy__kal?igsh=MWNycmhjN3plMWFscQ==
Follow , i will follow back📌
https://www.instagram.com/classy__kal?igsh=MWNycmhjN3plMWFscQ==
24.03.202519:14
ርዕስ አልተገኘለትም(ርዕሱ ነው)
ነጭ ግድግዳ የተባለ ነገር እያስጠላት መጥቷል።ሞት ሞት የሚሸት ክፍል መታጎሯ ለማን ጥቅም እንደሆነ አይገባትም ፤ለእርሷ ወይስ ለእነሱ?ሁሌ ወደ ክፍሏ ሱክ ሱክ እያሉ ወጣ ገባ የሚሉት ሰዎች ነጭ የለበሱ አውሬዎች ይመስሏታል፤ልክ እንደዛች ሴት...
ዛሬም እንደ ትናንቱ ሁሉ አንድ ነጭ ለባሽ ፍጥረት ፊት ለፊቷ ተቀምጧል።
"እስኪ ስለቀንሽ ነገሪኝ።" መነፅሩን ገፋ እያደረገ ጠየቃት።
"ቀኔ...ቀኔ...ቆንጆ ስጋ በስሱ የተቆረጠ..." ለራሷ በሚመስል ድምፅ ዝም ብላ ታወራለች።ዶክተሩ አንዳች ነገር ቸከቸከ እና በድጋሚ ቀና አለ
"አሌክሳንድራ! እባክሽ ከእኔ ጋር ሁኝ" ትዕዛዝ ይሁን ልምምጥ ባልገባው ድምፅ ተናገረ።እርሷም ቀና ብላ አየችው።ጭንቅላቷን በእሺታ አወዛውዛ ዞር ልትል ስትል መልክ አየች፤የሰው ሊያውም የሴት፤ሌላ የትም አደለም እዚያው መነፅሩ ውስጥ።የት እንደምታውቃት ለማስታወስ ሞከረች።ፀጉሯ ሊተኮስ እንደተሰየመ ደረቅ ሳር ቆም ቆም ያለ፤ፊቷ ከአዲስ ወረቀት የነጣ ሴት ፊት።የት ነበር ምታውቃት...?ዶክተሩ በፅሞና ሲያያት ቆየና
"ምን እያሰብሽ ነው?"ብሎ ጠየቃት፤የምርም ጓግቶ ነበር።
"መነፅርህ ውስጥ ሴት አየሁ።ማን ናት እያልኩ ነበር።ድክተርዬ አቃታለሁ መሰል..."ምታስብ መስላ ዝም አለች።ከአፍታ በኋላ ፍለጋው ቀንቷት ይሆን አድክሟት ቀና ብላ እርሱኑ ማየት ጀመረች።እርሱም ምናልባት ከወራት በኋላ የተለወጠ ነገር ያለ ስለመሰለው መናገር ቀጠለ።
"እርሷ አሌክሳንድራ ስቲቨንስ ትባላለች።ሀርላንድ የሚባል ባል እና ክርስቲ ምትባል ቆንጅዬ ልጅ ነበረቻት።ባሏ የሚሰራው በቤት ሽያጭ ጉዳዮች ነበር።እርሷ ደግሞ አራሷን ክርስቲን ይዛ የቤት እመቤት፤ውብ ወይዘሮ ነበረች። እጅግ ደስተኞች ነበሩ።ከአመት አመት በፍቅር እንደ አዲስ እፍ የሚሉ ቤተሰቦች..."ፊቷን አስተዋላት።ጉንጯን እጆቿ ላይ አስደግፋ በተመስጦ ነበር ምታዳምጠው።ቀልቡ ጥሩ ነጥብ ላይ እንደደረሰ ሹክ አለው።ቀጠለ
"...የሆነ ቀን ላይ ተነስታ ማንም ያላሰበውን አደረገች።ባሏን፤ የልጀነት ምኞቷን፤ስለ ፍቅሩ የመነነችለትን አዳሟን...ገደለችው።ቆራርጣ ማቀዝቀዣ ውስጥ አስቀመጠችው።...ትንሿ ክርስቲ ነገሩ ሳይገባት ከማልቀስ በቀር ምንም አላለችም።አሌክሳንድራም ልጇን አንስታ..."ይሄን እንዳለ አቆመና ለደቂቃዎች ሁኔታዋን አጤነ።ፊቷ ከበፊቱም ይባስ ነጥቶ እና ገርጥቶ ነበር።ጥርሷን ምታኝከው ይመስል አስሬ ሰቅጣጭ ድምፅ ያወጣል።ከእግሯ እንቅጥቃጤና ከክፍሉ ዝምታ ጋር ተዳምሮ ክፍሉ አንዳች ደመናን ያረገዘ መሰለ።ያቋረጠውን አስታውሳ ቀዝቃዛ ንግግር ከፈተች።
"...ካሪን አንስታ አይዞሽ የስጋ መረቅ ልሰራልሽ ነው አለቻት።...ፖሊሶች ከሰዓታት በኋላ ስለ ባሏ መሰወር ከጎረቤት ሰምተው ለፍለጋ በራቸውን አንኳኩ..."ማልቀስ ጀመረች።ከእምባዋ ጋር የፀፀት፤የብቸኝነት፤የበደል ስሜቷን አብራ አነባችው።ዶክተሩ ወራት የለፋበትን ውጤት በማግኘቱ ውስጥ ውስጡን ደስ ቢለውም የአሌክሳንድራ ሁኔታ ግን ወደ ጥልቅ ሀዘን ልቡን ለመክተት ብዙ አልፈጀበትም።ስለማፅናናት ቢያስብም ከግል ስሜቱ ስራውን አስቀደመ።
"ምክንያቷ ምን ነበር ብለሽ ታስቢያለሽ አሌክሳንድራ? ጥርጣሬ፣ጥላቻ፣ቅናት፣ቂም ወይስ ንዴት ነበር በአንዲያ ፍቅሯ ላይ ጨክና ቢላ እንድታሳርፍ ያረጋት?"
ምንም አላለችም ከልቧ አነባች ልቧ ደምን አነባ።የምድር ጫፍ ላይ ብቻዋን ያለች መሰላት።በድኗ ቀረ።ልቧ ሞተ።
ለሰዓታት ተንሰቀሰቀች።ዶክተሩ ከነበረበት ሳይነሳ እስከምትጨርስ አብሯት ነበር።ከጎኗ መለየት አልቻለም ነበር።ድንገት"ወደ ክፍሌ እንዲወስዱኝ ንገራቸው"
ለመቃወም ድፍረት አልነበረውም።ነርሷ እና አንዲት ፖሊስ መጥተው ወሰዷት።
ከቀናት በኋላ ራሷን ማጥፍቷን ሰማ።የአልጋዋን ብረት ነቃቅላ ራሷን ልክ እንደ ባሏ ቆራርጣ ተገኘች።በባሏ ያረፉት እጆቿ ለእራሷም መጥፊያ አረገቻቸው።
ከአመታት በኋላ ዲያሪዋ ተገኘ።ሙሉ ህይወቷ ነበር የተተየበበት።ከባሏ ሞት በፊት ከባድ ድብርት ውስጥ መግባቷን ፅፋ ነበር።ስለ መሞት ማስቧም ተገልጿል።የገደለችው ለት የፃፈችው ገፅ አጭር ነበር።
"ውድ ማስታወሻዬ
ዛሬ በስሱ የተቆራረጠ የስጋ መረቅ አምሮኝ ነበር።ሀርሊ እንዲገዛልኝ ስጠይቀው ስለ ገንዘብ ችግር አውርቶ ተጣላን እና መታኝ።እኔም ጭንቅላቱን በጠርሙስ ብዬው ወደቀ።ከዛም ያማረኝን ስጋ
በላሁ።ካሪም ጠጥታለች ግን አልወደደችውም መሰል ካጠጣኋት በኋላ ተኛች፤አልተነፍስ አለች ደግሞ.....ሰው እያንኳኳ ነው መጣሁ..."
ይል ነበር ልጇንም የገደለቻት እርሷ ነበረች?
ለዚ ርዕስ ይሰጣል?ምንስ ተብሎ?
✍️🏼ቃል
https://t.me/Piece_of_pages
https://t.me/Piece_of_pages
ነጭ ግድግዳ የተባለ ነገር እያስጠላት መጥቷል።ሞት ሞት የሚሸት ክፍል መታጎሯ ለማን ጥቅም እንደሆነ አይገባትም ፤ለእርሷ ወይስ ለእነሱ?ሁሌ ወደ ክፍሏ ሱክ ሱክ እያሉ ወጣ ገባ የሚሉት ሰዎች ነጭ የለበሱ አውሬዎች ይመስሏታል፤ልክ እንደዛች ሴት...
ዛሬም እንደ ትናንቱ ሁሉ አንድ ነጭ ለባሽ ፍጥረት ፊት ለፊቷ ተቀምጧል።
"እስኪ ስለቀንሽ ነገሪኝ።" መነፅሩን ገፋ እያደረገ ጠየቃት።
"ቀኔ...ቀኔ...ቆንጆ ስጋ በስሱ የተቆረጠ..." ለራሷ በሚመስል ድምፅ ዝም ብላ ታወራለች።ዶክተሩ አንዳች ነገር ቸከቸከ እና በድጋሚ ቀና አለ
"አሌክሳንድራ! እባክሽ ከእኔ ጋር ሁኝ" ትዕዛዝ ይሁን ልምምጥ ባልገባው ድምፅ ተናገረ።እርሷም ቀና ብላ አየችው።ጭንቅላቷን በእሺታ አወዛውዛ ዞር ልትል ስትል መልክ አየች፤የሰው ሊያውም የሴት፤ሌላ የትም አደለም እዚያው መነፅሩ ውስጥ።የት እንደምታውቃት ለማስታወስ ሞከረች።ፀጉሯ ሊተኮስ እንደተሰየመ ደረቅ ሳር ቆም ቆም ያለ፤ፊቷ ከአዲስ ወረቀት የነጣ ሴት ፊት።የት ነበር ምታውቃት...?ዶክተሩ በፅሞና ሲያያት ቆየና
"ምን እያሰብሽ ነው?"ብሎ ጠየቃት፤የምርም ጓግቶ ነበር።
"መነፅርህ ውስጥ ሴት አየሁ።ማን ናት እያልኩ ነበር።ድክተርዬ አቃታለሁ መሰል..."ምታስብ መስላ ዝም አለች።ከአፍታ በኋላ ፍለጋው ቀንቷት ይሆን አድክሟት ቀና ብላ እርሱኑ ማየት ጀመረች።እርሱም ምናልባት ከወራት በኋላ የተለወጠ ነገር ያለ ስለመሰለው መናገር ቀጠለ።
"እርሷ አሌክሳንድራ ስቲቨንስ ትባላለች።ሀርላንድ የሚባል ባል እና ክርስቲ ምትባል ቆንጅዬ ልጅ ነበረቻት።ባሏ የሚሰራው በቤት ሽያጭ ጉዳዮች ነበር።እርሷ ደግሞ አራሷን ክርስቲን ይዛ የቤት እመቤት፤ውብ ወይዘሮ ነበረች። እጅግ ደስተኞች ነበሩ።ከአመት አመት በፍቅር እንደ አዲስ እፍ የሚሉ ቤተሰቦች..."ፊቷን አስተዋላት።ጉንጯን እጆቿ ላይ አስደግፋ በተመስጦ ነበር ምታዳምጠው።ቀልቡ ጥሩ ነጥብ ላይ እንደደረሰ ሹክ አለው።ቀጠለ
"...የሆነ ቀን ላይ ተነስታ ማንም ያላሰበውን አደረገች።ባሏን፤ የልጀነት ምኞቷን፤ስለ ፍቅሩ የመነነችለትን አዳሟን...ገደለችው።ቆራርጣ ማቀዝቀዣ ውስጥ አስቀመጠችው።...ትንሿ ክርስቲ ነገሩ ሳይገባት ከማልቀስ በቀር ምንም አላለችም።አሌክሳንድራም ልጇን አንስታ..."ይሄን እንዳለ አቆመና ለደቂቃዎች ሁኔታዋን አጤነ።ፊቷ ከበፊቱም ይባስ ነጥቶ እና ገርጥቶ ነበር።ጥርሷን ምታኝከው ይመስል አስሬ ሰቅጣጭ ድምፅ ያወጣል።ከእግሯ እንቅጥቃጤና ከክፍሉ ዝምታ ጋር ተዳምሮ ክፍሉ አንዳች ደመናን ያረገዘ መሰለ።ያቋረጠውን አስታውሳ ቀዝቃዛ ንግግር ከፈተች።
"...ካሪን አንስታ አይዞሽ የስጋ መረቅ ልሰራልሽ ነው አለቻት።...ፖሊሶች ከሰዓታት በኋላ ስለ ባሏ መሰወር ከጎረቤት ሰምተው ለፍለጋ በራቸውን አንኳኩ..."ማልቀስ ጀመረች።ከእምባዋ ጋር የፀፀት፤የብቸኝነት፤የበደል ስሜቷን አብራ አነባችው።ዶክተሩ ወራት የለፋበትን ውጤት በማግኘቱ ውስጥ ውስጡን ደስ ቢለውም የአሌክሳንድራ ሁኔታ ግን ወደ ጥልቅ ሀዘን ልቡን ለመክተት ብዙ አልፈጀበትም።ስለማፅናናት ቢያስብም ከግል ስሜቱ ስራውን አስቀደመ።
"ምክንያቷ ምን ነበር ብለሽ ታስቢያለሽ አሌክሳንድራ? ጥርጣሬ፣ጥላቻ፣ቅናት፣ቂም ወይስ ንዴት ነበር በአንዲያ ፍቅሯ ላይ ጨክና ቢላ እንድታሳርፍ ያረጋት?"
ምንም አላለችም ከልቧ አነባች ልቧ ደምን አነባ።የምድር ጫፍ ላይ ብቻዋን ያለች መሰላት።በድኗ ቀረ።ልቧ ሞተ።
ለሰዓታት ተንሰቀሰቀች።ዶክተሩ ከነበረበት ሳይነሳ እስከምትጨርስ አብሯት ነበር።ከጎኗ መለየት አልቻለም ነበር።ድንገት"ወደ ክፍሌ እንዲወስዱኝ ንገራቸው"
ለመቃወም ድፍረት አልነበረውም።ነርሷ እና አንዲት ፖሊስ መጥተው ወሰዷት።
ከቀናት በኋላ ራሷን ማጥፍቷን ሰማ።የአልጋዋን ብረት ነቃቅላ ራሷን ልክ እንደ ባሏ ቆራርጣ ተገኘች።በባሏ ያረፉት እጆቿ ለእራሷም መጥፊያ አረገቻቸው።
ከአመታት በኋላ ዲያሪዋ ተገኘ።ሙሉ ህይወቷ ነበር የተተየበበት።ከባሏ ሞት በፊት ከባድ ድብርት ውስጥ መግባቷን ፅፋ ነበር።ስለ መሞት ማስቧም ተገልጿል።የገደለችው ለት የፃፈችው ገፅ አጭር ነበር።
"ውድ ማስታወሻዬ
ዛሬ በስሱ የተቆራረጠ የስጋ መረቅ አምሮኝ ነበር።ሀርሊ እንዲገዛልኝ ስጠይቀው ስለ ገንዘብ ችግር አውርቶ ተጣላን እና መታኝ።እኔም ጭንቅላቱን በጠርሙስ ብዬው ወደቀ።ከዛም ያማረኝን ስጋ
በላሁ።ካሪም ጠጥታለች ግን አልወደደችውም መሰል ካጠጣኋት በኋላ ተኛች፤አልተነፍስ አለች ደግሞ.....ሰው እያንኳኳ ነው መጣሁ..."
ይል ነበር ልጇንም የገደለቻት እርሷ ነበረች?
ለዚ ርዕስ ይሰጣል?ምንስ ተብሎ?
✍️🏼ቃል
https://t.me/Piece_of_pages
https://t.me/Piece_of_pages
Қайта жіберілді:
ምስለ እኔነት🤩

11.02.202520:40
መልኬን ባጣው የጣልኩትን
በሰው ትንፋሽ የፃፍኩትን
የሄደ እለት እኔም ተነንኩ
እንዳልኖርኩኝ ዳግም ባከንኩ...
ለዚህ አይደል የማርቀው
እንዳይፃፍ ገፄ ከርሱ የማጠፋው
ኩልል ብሎ የኔነት መልክ እንዲገለፅ
እንዳይጠፋ .....
የኔ ተስሎ የርሱ ጠፋ
ይህ ይሻላል የካድከኝ ለት እንዳልረሳው
ክህደትህ የኔኑ መልክ እንዳይክደው
......
አይሻልም?
@onelife21A
በሰው ትንፋሽ የፃፍኩትን
የሄደ እለት እኔም ተነንኩ
እንዳልኖርኩኝ ዳግም ባከንኩ...
ለዚህ አይደል የማርቀው
እንዳይፃፍ ገፄ ከርሱ የማጠፋው
ኩልል ብሎ የኔነት መልክ እንዲገለፅ
እንዳይጠፋ .....
የኔ ተስሎ የርሱ ጠፋ
ይህ ይሻላል የካድከኝ ለት እንዳልረሳው
ክህደትህ የኔኑ መልክ እንዳይክደው
......
አይሻልም?
@onelife21A


Медиа контентке
қол жеткізе алмадық
қол жеткізе алмадық
26.01.202510:57
11.11.202404:58
"ሁላችንም ታሪካችን እንደ ተረት ከእለታት አንድ ቀን ጀምሮ ከእለታት አንድ ቀን ያበቃል፣ ህይወት ግን በበርካታ ግማሽ ቀናት የተሞላች መንገድ ናት... መኖር ማለት ይሕችኑ ግማሽነት ለመሙላት የሚደረግ ትግል ነው።"
📚 ከእለታት ግማሽ ቀን
✍ አሌክስ አብርሀም
📚 ከእለታት ግማሽ ቀን
✍ አሌክስ አብርሀም
Рекордтар
16.05.202523:59
419Жазылушылар05.04.202523:59
500Дәйексөз индексі30.03.202515:38
3421 жазбаның қамтуы30.03.202515:38
342Жарнамалық жазбаның қамтуы01.02.202523:59
4.76%ER15.01.202520:56
112.00%ERRКөбірек мүмкіндіктерді ашу үшін кіріңіз.