Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Мир сегодня с "Юрий Подоляка"
Труха⚡️Україна
Труха⚡️Україна
Николаевский Ванёк
Николаевский Ванёк
TIKVAH-ETHIOPIA avatar
TIKVAH-ETHIOPIA
News and Media
TIKVAH-ETHIOPIA avatar
TIKVAH-ETHIOPIA
News and Media
21.04.202518:50
በመዲናዋ የትንሣኤ በዓል እንዴት አለፈ ?

በ2017 ዓ/ም የትንሣዔ በዓል የተለያዩ ደንቦችን በተላለፉ አሽከርካሪዎች እርምጃ መወሰዱን፣ የበዓል ዋዜማ አንድ ሰው በመኪና አደጋ መሞቱን የአዲስ አበባ ከተማ  ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?

“ ከወንጀል አንጻር ስንመለከት፥ በመደበኛነት ከሚፈጸሙ እንደሌብነት፣ ጸብ፣ ቅሚያና የመሳሰሉ ከመጠጥ ጋር የተገናኙ ድርጊቶች ካልሆኑ በስተቀር ከበዓሉ ጋር በተገናኘ ከባድ ወንጀል የተፈጸመበት ጊዜ አልነበረም።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ኮድ 2 64942 አውቶብስ የ50 ዓመት እድሜ ያላቸው ሰው በውስጥ ለውስጥ መንገድ ወጥተው ሲሻገሩ ገጭቷቸው ህይወታቸው እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል።

የትራፊክ አደጋ ላይ በአልኮል መጠጥ ፍተሻ ጭምር ቁጥጥር አድርገናል። በዚህም በአልኮል ጥሰት ወደ 1,072 አሽከርካሪዎችን ተፈትሽዋል። 33 አሽከርከሪዎች ከመጠን በላይ ጠጥተው ሺያሽከረክሩ ተገኝተው በደንብ መተላለፍ ቅጣት ተወስዶባቸዋል።

ከመጠን በታች የጠጡ ደግሞ ወደ 41 አሽከርካሪዎች አግኝተናል። አልኮል ጠጥተዋል፤ ግን መጠኑ ከ0.4 በላይ አይደለም። ከፍተኛ የሚባለው ከዚህ በላይ ሲሆን ነው። ግን ይሄም አደጋ የሚያደርስ ስለሆነ አስተምረን ለቀናቸዋል።

ሌሎች ልዩ ልዩ ደንቦችን የጣሱ አሽከርካሪዎች ላይ ቁጥጥር አድርገናል። ወደ 99 አሽከርካሪዎች ደንብ ሲተላለፉ ተገኝተው አስፈላጊው እርምጃ ተወስዶባቸዋል። በዓሉ በጣም ደማቅ ነበር፤ ከድምቀቱና ከሰው ብዛቱ አንፃር ሰላማዊ በዓል አሳልፈናል ማለት ይቻላል ” ብለዋል።

ሰዎች ወንጀል ሲፈጽሙ ብዙ ጊዜ በጥቅል “እርምጃ ተወስዶባቸዋል” ነው የሚባለውና በሾፌሮቹ የተወሰደው እርምጃስ ምንድን ነው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “ ከ70 በላይ ደንብ መተላለፎች ናቸው። 70ዎቹንም መጥቀስ አይቻልም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

በበዓሉ ህገ ወጥ የብር ኖት ማጭበርበር፣ በምግብና መጠጥ ላይ በዓድ ነገሮችን ቀላቅሎ ከመሸጥ አንፃር የተፈጸመ ወንጀል ካለ ስንጠይቃቸውም፣ እስካሁን የደረሳቸው የክስ ሁኔታ እንደሌለ፣ ካለ ግልጽ እንደሚያደርጉ አስረድተዋል።

ኮማንደር ባስተላለፉት መልዕክት ምን አሉ ?

“ ከዚህ በኋላም የሰርግ ወራት ነው፤ በተለይ የትራፊክ አደጋ ሥጋት አለብን ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ አለበት። አልኮል ጠጥተው የሚያሽከረክሩ ሹፌሮች እንደሚበዙ ይገመታል።

አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ሰው ስለሚበዛ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል፣ ሰውና እቃን አንድ ላይ መጫን እና የመሳሰሉ ደንብ መተላለፎች ሊበዙ ይችላሉ ተብሎ ስለሚገመት ጥብቅ ቁጥጥር እናደርጋለን።

የትራንስፓርት መጠበቂያ፣ በጥቅሉ ሰው በሚበዛባቸው ቦታዎች የኪስ ቀበኞች ሊኖሩ ስለሚችሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ አለበት ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
21.04.202505:15
#Tigray

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ እንደ አዲስ የተዋቀረው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ስራ እንደጀመረ ተነግሯል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ ሲመራ የነበረውን የካቢኔ ቁጥር ከ27 ወደ 21  ፤ ሁለት ምክትል ፕሬዜዳንት የነበረውን ወደ አንድ እንዲወርድ ያደረጉት ፕሬዜዳንቱ እስካሁን ምክትላቸው ማን እንደሆነ በይፋ አላስታወቁም።

ይሁን እንጂ ከደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የህወሓት ሃይል ሰፊ ቁጥር ያለው የካቢኔ አባል ያካተቱ ስለመሆኑ ተነግሯል።

ምክትላቸው  የህግ ምሁርና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ኣማኒኤል አሰፋ አደርገው መሾማቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ጨምሮ በርካቶች በመፃፍ ላይ ይገኛሉ።

አንዳንዶች  " አዲሱ የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት የወጣቱ የለውጥ ጥያቄ የሚመልስ አዲስ ካቢኔ አላዋቀሩም " በሚል ነቄፌታ እያቀረቡ ይገኛሉ።

ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ አዲሱ ካቢኔ ስራ መጀመሩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ " ትግራይ በአሸናፊና ተሸናፊ የፓለቲካ ቅኝት ከገባችበት አዘቅት መውጣት አትችልም " ብለዋል።

" ባለፉት ሁለት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዓመታት በርካታ ጥሩና መጥፎ ነገሮች ተፈፅመዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ጥሩውን ለራስ መጥፎውን ለሌላ መስጠት አይቻልም ድሉም ውድቀቱም የጋራ ነው ከእልህና ህዝብንና አገር ከሚጎዳ ፓለቲካዊ አካሄድ እንውጣ "  ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።  

" የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች የሚመሰገኑበት መድረክ ይዘጋጃል " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ጥሪውን ተቀብለው እንዲገኙ ከወዲሁ በይፋ የግብዣ ጥሪ አቅርበዋል።

የቀድሞ ፕሬዚዳንትና አመራሮች ይመሰገኑበታል የተባለው የምስጋና ስነስርዓት መቼ እና የት እንደሚዘጋጅ የተባለ ነገር የለም።

በሌላ በኩል ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ተፈናቃዮች የሚገኙበት ስቃይና ሰቆቃ ባወሳ ንግግራቸው " በዚሁ ዓመት ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ይሰራል ፤ በማቆያ ጣብያ የሚቆዩት ደግሞ አኗኗራቸው እንዲሻሻል ትኩረት ይደረጋል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

@tikvahethiopia
20.04.202519:52
19.04.202523:27
" አንዳችን በሌላችን ላይ ያስከተልነው ጉዳት ጥላቻን ከትውልድ ወደ ትውልድ ከማሸጋገር እና የህዝባችንን ሰቆቃ ከማራዘም በስተቀር አንዳችም መልካም ነገር አላስገኘልንም " - ቄስ ደረጀ ጀምበሩ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሀፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የ2017 ዓ/ም የትንሣኤ በዓልን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" የትንሣኤን መታሰቢያ በዓል ስናከብር እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን ታላቅ ፍቅርና ከዚህም የተነሳ አንድያ ልጁን ስለ እኛ ሃጥያት ለመስቀል ሞት አሳልፎ መስጠቱን እንድናስብ ግድ ይለናል። ይህም ከዘላለም ሞት ወደ ዘላለም ሕይወት መሸጋገራችንን ፤ ከሃጥያት ባርነት ነጻ መውጣታችንን በመገንዘብ እግዚአብሔርን ይበልጥ እንድናመሰግነውና ዕለት ዕለትም በቅድስና እንድናመልከው ሊያደርገን ይገባል።

ስለሆነም ፋሲካችን የሆነው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ከሃጥያታችን ስለዋጀን የመንግሥቱም ወራሽ በመሆን በጽኑ ተስፋ ተደላድለን እንድንቆም ስላደረገን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ብቻ ይሁን።

ትንሣኤ ጥላቻ በፍቅር ፤ መለያየት በአንድነት ፤ ሀዘን በደስታ የተቀየረበት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍቅር የተገለጠበት ስለሆነ ከሁሉ በፊት በእኛ በክርስቲያኖች መካከል እውነተኛ ፍቅር መታየት ይኖርበታል።

ትንሣኤ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተራራቁ የሚቀራረቡበት እንዲሁም በያለንበት ታርቀን በማስታረቅ መልካም ምሳሌነታችን ጎልቶ እንዲታይ ያስፈልጋል። ይህ ከሁሉም ምዕመናን የሚጠበቅ መልኮታዊ ትዕዛዝ ስለሆነ ቸል የምንለው ጉዳይ አይሆንም።

.
.

ሀገራችን ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የእርስ በእርስ ግጭቶች የተነሳ ብዙ ጎዳቶችን እንዳስተናገደች የሚካድ አይደለም። በዋናነት ለድህነታችን እና ወደኃላ ለመቅረታችን ምክንያቱ ልዩነቶችን በውይይት ከመፍታት ይልቅ መሳሪያ በማንሳት መጠፋፋት ላይ በማተኮራችን እንደሆነ ግልጽ ነው።

አንዳችን በሌላችን ላይ ያስከተልነው ጉዳት ጥላቻን ከትውልድ ወደ ትውልድ ከማሸጋገር እና የህዝባችንን ሰቆቃ ከማራዘም በስተቀር አንዳችም መልካም ነገር አላስገኘልንም። ይህ እየታወቀ አሁንም ከመጠፋፋት አዙሪት ለመውጣት የምናሳየው ፍቃደኝነት አለመኖር ወይም አዝጋሚ መሆን እጅግ ያሳዝናል።

የችግራችን መፍትሄ ያለው በእኛው እጅ ስለሆነ ችግሩ ተባብሶ የበለጠ ጉዳት ሳያስከትል ቆም ብለን ልናስብ ያስፈልጋል። በፍጹም ቅንነት መከባበር እና መደማመጥ በእርቅ የሀገራችንን ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ እና የህዝባችንንም አንድነት በፅኑ አለት ላይ ለማቆም መወያየት ግድ ይለናል።

ስለዚህ አሁንም ካውንስላችን የሰላም ጥሪውን በመደጋገም ሲያስተላልፍ በእግዚአብሔር ስም ነው። "

(የአባታችን ሙሉ መልዕክት በዚህ ተያይዟል ፦
https://youtu.be/WPX_OADik1Q?si=-raFopdEdxRCCpRa)

@tikvahethiopia
19.04.202517:39
" መሳሪያ አንሥታችሁ እርስ በርስ በመገዳደል የምትገኙ ወገኖቻችን እባካችሁ ቆም ብላችሁ ኣስቡና ሰላምና ዳቦ ኣጥቶ ለተቸገረው ሕዝባችሁ ስትሉ ለሰላማዊ መፍትሔ ዕድል ስጡ " - ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2017 ዓመተ ምሕረት የትንሣኤ በዓልን በማስመልከት  አባታዊ  ቃለ በረከት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ዘር ሳይኖር ፍሬ እንደማይገኝ ሁሉ ሕይወታዊ ትንሣኤም ያለ ሃይማኖትና ሥነ - ምግባር ሊገኝ ኣይችልም፡፡ ጌታችንም ይህንን ኣስመልክቶ ሲያስተምረን " መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ይነሣሉ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይነሣሉ " ብሎ ኣሳውቆናል፡፡

ከዚህ አኳያ የሕይወትን ትንሣኤ የሚያገኝ ያመነ፣ የተጠመቀና መልካም ስራን የሰራ እንጂ የተነሣው ሁሉ ኣለመሆኑ ግልጽ ነው፤ መነሣቱ ሁሉም የግድ ይነሣል፤ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ የሚጠብቀን ሕይወት በዚህ ዓለም በሕይወተ ሥጋ ሳለን በሰራነው ስራ የሚወሰን እንደሆነ ጌታችን በማያሻማ ሁኔታ ኣረጋግጦልናል፡፡

ስለሆነም የመጨረሻው ዕድላችን የተንጠለጠለው እምነትን ተከትለን በምንሰራው ስራ ላይ መሆኑን ለኣፍታ እንኳ መዘንጋት የለብንም፤ ዛሬ ከሰው ኣእምሮ በእጅጉ እየራቀ የሚገኘው ይኸው እምነትና ሥነ-ምግባር ነው፤ ሰዎች ከእምነትና መልካም ሥነ-ምግባር በራቁ ቊጥር ሕይወት መራራ እንድትሆን ትገደዳለች፡፡

እኛ ኢትዮጵውያን ከጥንት ጀምሮ በእምነትና ሥነ-ምግባር እየተመራን፣ በደልን በይቅርታ እየዘጋን፣ እስከ ጋብቻ በሚዘልቅ ባህለ-ዕርቅ ደምን እያደረቅን፣ በወንድማማችነት ፍቅር ተስማምተን በሺሕ ለሚቆጠሩ ዘመናት እንዳልኖርን፣ እነሆ ዛሬ ለታላቅነታችን በማይመጥን ሆናቴ መለያየትና መጣላት ብሎም እርስ በርስ መገዳደል ዕለታዊ ተግባራችን ኣድርገን እንገኛለን፡፡

ይህ በጣም ኣሳዛኝ ክሥተት ነው፤ ይህንን ሳናስተካክል የምናከብረው በዓለ ትንሣኤም እዚህ ግባ የሚባል ደስታ ሊያስገኝልን እንደማይችል የታወቀ ነው፡፡

እየሆነ ያለው ሁሉ ማንንም ኣይጠቅምም፤ በዕርቅ፣ በይቅርታና በውይይት የማይፈታ ችግር ያለ ይመስል ይህን ያህል መጨካከን እንዴት እንደ መፍትሔ ተደርጎ ይወሰዳል ? አሁንም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የምንማፀነው ፡- እባካችሁ እኛው ራሳችን ሸምጋይና ተሸምጋይ ሆነን ችግሮቻችንን ለመፍታት በብርቱ እንስራ፤ መፍትሔም እናምጣ፤ መሳሪያ ኣንሥታችሁ እርስ በርስ በመገዳደል የምትገኙ ወገኖቻችን እባካችሁ ቆም ብላችሁ ኣስቡና ሰላምና ዳቦ ኣጥቶ ለተቸገረው ሕዝባችሁ ስትሉ ለሰላማዊ መፍትሔ ዕድል ስጡ።

ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገር የሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆኗን በትክክል የሚያረጋግጥ ሰላማዊ መፍትሔ በማስቀመጥ ለአንድነትዋና ለዕድገትዋ አጥብቃችሁ ጣሩ ፤ ግጭትና መለያየት ከሚያጠፋን በቀር ምንም ዓይነት ጥቅም ሊሰጠን እንደማይችል ብዙ ማብራሪያ የሚያስፈልገው ኣይደለም፤ ስለሆነም ገዳዩን መሳሪያ ኣስቀምጡና በሃይማኖት፣ በኣንድነት፣ በስምምነትና በጭንቅላት ኃይል ሰላምን ኣምጡ፤ ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ጥሪ ነው።

በልዩ ልዩ ምክንያት ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው በየኣካባቢው በረኃብ ኣለንጋ እየተገረፉ የሚገኙት ወገኖቻችን በትንሣኤው በዓል ተጽናንተውና እፎይ ብለው በደስታ እንዲያሳልፉ ካለን ከፍለን በመመገብና በማልበስ እንድንደርስላቸው በእግዚአብሔር ስም ኣባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን። "


(የቅዱስነታቸው ሙሉ የትንሣኤ በዓል መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
19.04.202517:21
21.04.202511:34
#EOTC

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ፍራንሲስ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ለመላው የሮማ ካቶሊካዊ መሪዎች እና በመላው ዓለም ላሉ ምእመናን እንዲሁም በኢትዮጵያ ላሉ ካቶሊካውያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
21.04.202505:15
20.04.202519:52
#ሐኪሞች🙏

በጎ ፈቃደኛ ሐኪሞች የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ በሀዋሳ ከተማ ለህግ ታራሚዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት ሰጥተዋል።

የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ ጤና ተቋማት የተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በሀዋሳ ከተማ በሚገኘዉ የማረሚያ ተቋም በመገኘት ለህግ ታራሚዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት ሰጥተዋል።

በነፃ የህክምና አገልግሎቱ አጠቃላይ ሀኪሞች ፣የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች ፣ የቆዳ ህክምና ስፔሻሊስት ፣ የጥርስ ሀኪሞች እና የዓይን ህክምና ስፔሻሊስት ተሳትፈውበታል።

ባለሙያዎቹ በሀዋሳ ከተማ ማረሚያ ተቋም በመገኘት ከ358 ለሚሆኑ የህግ ታራሚዎች ነፃ የምርመራና የህክምና አገልግሎት ሰጥተዋል።

ባለሙያዎቹ ከአዲስ አበባ የመጡ ሲሆኑ የዘጠነኛዉ ሺ ሲትኮም ተከታታይ ድራማ ደራሲና ዳይሬክተር ዶክተር በዛብህ ብርሃኑ መረሃ ግብሩን መምራታቸውን ላለፉት ሶስት ቀናት የህክምና አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውን ለመስማት ችለናል።

@tikvahethiopia
19.04.202523:24
" በመስቀልና በትንሣኤው የተሰበረው ይጠገናል፤ የደከመው ይበረታል፤ የወደቀው ይነሣል፤ የተሸነፈው ያሸንፋል ይህንንም ለማክበር በትንሣኤው እንሰበሰባለን " - ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳሳት የ2017 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" የትንሣኤ በዓል የክርስቲያን ሕይወት መሠረትና ምሶሶ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው ትንሣኤ ባይኖር እምነታችን ከንቱ በሆነ ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ የሚታዘንልን ሰዎች በሆንን ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክቱን የጻፈው በቆሮንጦስ ክርስቲያኖች መካከል ትንሣኤን የሚጠራጠሩ ሰዎች ስለነበሩ ነው፤ በሌላ አነጋገር ትንሣኤን እየካዱ ወይንም እየተጠራጠሩ ክርስቲያን ነን ማለት ትርጉም እንደሌለው እያስተማረ ነበር ማለት ነው፡፡

ሰውን በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረ ጌታ አሁንም ሰውን በትንሣኤው አዲስ ፍጥረት አደረገው፡፡ ሰውን በመልኩና በአምሳሉ መፍጠሩ ብዙ ያስተምረናል፡፡ የተለየ ቦታና ሃላፊነት ለሰው እንደተሰጠ ያሳየናል፡፡ ትንሣኤው ደግሞ ሰውን በሙሉ በድጋሚ ወደ አንድ ማምጣቱን ያሳየናል። ትንሣኤ በሰው ውድቀት የተጨማደደውን መልክ ያስተካክላል፡፡ ትንሣኤ ሁሉንም ነገድ፤ ሁሉንም ቋንቋ፤ ሁሉንም ባህል ወደ አንድ ያመጣዋል፡፡ ትንሣኤ የጎደለውን ይሞላል፡፡ የተረሳውን ያስታውሳል፡፡ የሕይወትን ወሳኝ ጥሪ ወደ ትክክለኛው ቦታ ይመራዋል፡፡

የትንሣኤዉ የምሥራች ከምንም በላይ የምርምር ውጤት ሳይሆን የእምነት ፍሬ ነገር መሆኑንም ማስተዋል ያሻል፡፡ ትንሣኤን መስበክ የተቀበሉትን እምነት ማስተላለፍ ነውና፡፡

ቅዱሳት መጽሐፍ ስናነብና ስናሰላስል በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ብርሃን የምናይበት ወቅት ያስፈልገናል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የሰውን ልጅ ታሪክም ሆነ የራሳችንን ታሪክ እንዲሁም በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ብርሃን ልንቃኘው ያሻል፡፡ በዚያን ወቅት አዲስ መረዳትን እናገኛለን፡፡ ዘመናችንን በልዩ ብርሃን እንረዳለን፡፡ የታሪክ ትርጉማችንንም ይቀይራል፤ ለሕይወትም የምንሰጠው ትርጉም ሙላትና በረከት ይኖረዋል፡፡ ምናልባት መልስ ያጣንባቸው እንቆቅልሾች መልስ ያገኛሉ፡፡ ሐዋርያት ክርስቶስን እስከ ቀራንዮ ድረስ መከተል ከብዷቸው ሸሽተው ነበር፡፡ በድፍረት ወጥተው መመስከር የቻሉት በትንሣኤውና በጰራቅሊጦስ ምስጢር የተነሣ ነው፡፡ ቀራንዮና የመስቀል ሞት ያለትንሣኤ አሁን ያለውን ትርጉም ባላገኙ ነበር፡፡ የወንጌል የምሥራች የተገለጠው በክርቶስ ትንሣኤ ነው፡፡

ብዙ የሚያስጨንቁና የሚያሳዝኑ ነገሮች በዕለታዊ ሕይወታችን ውስጥ ያጋጥሙናል፡፡ የሰው ጥበብ እስከተወሰነ ድረስ ያደርሰን ይሆናል፡፡ ነገር ግን ጌታችንን በመከተል ብቻ የሚገኙ በረከቶች አሉ፡፡

የተፈጠርንበትን ዓላማ ስንስት ወደ መሠረታዊው ዓለም የሚመልሰን ፈጣሪ ብቻ ነው፡፡

መከፋፈል፤ መድሎ፤ ምቀኝነት፤ ጭካኔ የተፈጠርንበት ዓለም አይደሉም፡፡ አፍራሽ ሐሳብ፤ ጎጂ ንግግርና ተግባር ከተፈጠርንበት ዓላማ እጅግ የራቁ ነገሮች ናቸው፡፡ እውነተኛ መፍትሔዎች የሚመጡት ከእግዚአብሔር ነው፡፡ ወደ መስቀሉ ስንቀርብ ወደ ትንሣኤውም እንቀርባለን፡፡ መስቀል መሸሸጊያችን ሲሆን ትንሣኤም እንዲሁ አምባችን ይሆናል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር በመስቀልና በትንሣኤው አማካኝነት አዲስ ኪዳንን፤ አዲስ ፍጥረትን፤ እውነተኛ እርቅን አምጥቷልና ነው፡፡

በመስቀልና በትንሣኤው የተሰበረው ይጠገናል፤ የደከመው ይበረታል፤ የወደቀው ይነሣል፤ የተሸነፈው ያሸንፋል ይህንንም ለማክበር በትንሣኤው እንሰበሰባለን፡፡ የአምልኮ ሥርዓታችን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ላይ የተመሠረተ ነውና፡፡ "

(የአባታችን ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
19.04.202517:28
#Tigray

በቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሦስት ጀነራሎች ላይ የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድ በአዲሱ  ፕሬዜዳንት ተሽሯል።

በአራተኛው ጀነራል የተወሰነው ከሃላፊነት የማንሳት ውሳኔም ተሰርዟል።

የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፦
- በጀነራል ምግበይ ሃይለ
- በጀነራል ዮውሃንስ ወ/ጊዮርጊስ
- በጀነራል ማሾ በየነ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ ፈንታ በአቶ ጌታቸው ረዳ በተፃፈ ደብዳቤ ከስራ ገበታቸው እንዲነሱ መወሰኑ  ይታወሳል።

በቀድሞ ፕሬዜዳንት የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድና ከስራ የማሰናበት ውሳኔ በአዲሱ የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል።

አዲሱ ፕሬዜዳንት ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ጊዚያዊ እግዱና የስራ ስንብቱ ከመሰረዛቸው በተጨማሪ ፤ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊው በስራ ገበታቸው እንዲቀጥሉ የሚያፅና የሹመት ደብዳቤ ፅፈዋል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
የትንሳኤ ሎተሪ ወጣ።

የ2017 ዕጣ ዛሬ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በዕድል አዳራሽ መውጣቱን የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት አሳውቋል።

በዚህም ፦

1ኛ ዕጣ ቁጥር 0312160 ➡️ 10,000,000 ብር (አስር ሚሊዮን ብር)

2ኛ ዕጣ ቁጥር 0302606 ➡️ 5,000,000 ብር (አምስት ሚሊዮን ብር)

3ኛ ዕጣ ቁጥር 0269838 ➡️ 2,500,000 (ሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር)

4ኛ ዕጣ ቁጥር 1301182 ➡️ 1,500,000 ብር (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር)

(ሙሉ የዕጣ ማውጫ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
21.04.202505:21
20.04.202519:58
#ትንሣኤ

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ !

" በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደተናገረው ተነሥቷል "  

በማቴዎስ ወንጌል ፥ " እነሆ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወርዶአልና ፤ ቀርቦም በመቃብሩ አፍ ላይ ድንጋይዋን አንከባሎ በላይዋ ተቀመጠ፡፡

መልኩም እንደ መብረቅ ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበር፡፡

እርሱንም ከመፍራት የተነሣ መቃብሩን የሚጠብቁ ታወኩ ፤ እንደ በድንም ሆኑ፡፡

መልአኩ መልሶ ሴቶቹን እንዲህ አላቸው፥ ' እናንተስ አትፍሩ ፤ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንደምትሹ አውቃለሁና፡፡ በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደ ተናገረው ተነሥቶአል ' " ተብሎ እንደተጻፈው መድኃኒዓለም ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን በክብር ተነሥቶአል፡፡

መልካም የትንሣኤ በዓል !
በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሆን ዘንድ እንመኛለን !


ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
19.04.202523:24
19.04.202517:28
18.04.202517:44
" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
21.04.202505:21
" ህዝባችንን ከዚህ ኋላቀር ገዢ ሃይል ለማላቀቅ ሁሉንም ዓይነት ትግል እናካሂዳለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የህወሓት ኃይል

አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የህወሓት ኃይል " ሌሎችን ያገለለና አቃፊ ያልሆነ  ካቢኔ ተቋቁሟል " በሚል ተቃውሞውን ገለጸ።

አዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር ካቢኔ ወደ ስራ መግባቱን ፕሬዚዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ አሳውቀዋል።

" የአንዱን ህገ-ወጥ ቡድን ፍላጎት ብቻ በማድመጥ ሌሎች ያገለለ አቃፊ ያልሆነ ካቢኔ ማቋቋም ተቀባይነት  የለውም " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው የህወሓት ሃይል ተቃውሟል።

አዲሱ ካቢኔ በአስቸኳይ እንዲስተካከል ጠይቋል።

በይፋ ባሰራጨው መግለጫ " በባለፈው ጊዚያዊ አስተዳደር ላይ ወታደራዊ መፈንቅለ ስልጣን ተካሂደዋል "  የሚል አገላለፅ ተጠቅሟል።

" በትግራይ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በማካሄድ ስልጣን ከተያዘ 40 ቀናት ተቆጠረዋል " ያለው ይኸው የህወሓት ኃይል " የአቶ ጌታቸው አስተዳደር ህገ-ወጥ ተግባሩ ተጋግሎ ወደ ተባባሰ ግጭት እንዳያመራ ስልጣን ጭምር ለሰላም ሲል አሳልፎ ሰጥቷል " በማለት ገልጿል።

" አዲሱ ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግስትና በዓለም አቀፍ ተቋማት ወኪሎች ፊት የፈረሙት ሰነድ ሳይውል ሳያድር በመጣስ ወደ አንድ ወገን ያደላ ካቢኔ አቋቁመዋል " በማለትም ተችቷል።

በተግባር ያልተደገፈ ነው ሲል የገለጸው  " አሸናፊ እና ተሸናፊ የለም " የሚል ተደጋጋሚ ንግግራቸውን አብጠልጥሎታል። 

የተጀመረው ለውጥ የሚስቀጥል እንጂ ወደ ኋላ የሚመልስ አካሄድ ተቀባይነት እንደሌለው ገልጾ የተቋቋመው ካቢኔ በአስቸኳይ እንዲስተካከልና አቃፊ እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን ህዝቡን " ኋላቀር ገዢ " ካለው ሃይል ለማላቀቅ ሁሉም ዓይነት ትግል እንደሚያካሂድ አስጠንቅቋል።

ይህንን አቋሙንም " የፌደራል መንግስትና የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በግልፅ ይወቁልኝ " ብሏል።

የአዲሱ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ አዲሱ ካቢኒያቸው ወደ ስራ መግባቱ ይፋ ባደረጉበት ወቅት ለቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና በኋላፊነት ለሌሉ ሌሎች የካቢኔ አባላት ምስጋናና እውቅና ለመስጠት ያለመ ስነ-ስርዓት ይካሄዳል ብለው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

@tikvahethiopia
20.04.202519:58
#Ethiopia #Kenya

ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሞያሌ ድንበር የንግድ ልውውጥን በ1 ሺህ ዶላር ጣሪያ ለመጀመር ተስማሙ።

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለሁለት ዓመታት በዘለቀ ድርድር በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕቀፍ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥን ለማቀላጠፍ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

በዚህም መሰረት በሞያሌ ድንበር ላይ ለሚደረጉ የሸቀጦች ንግድ የመጀመሪያ ጣሪያ 1 ሺህ የአሜሪካ ዶላር እንዲሆን ተወስኗል።

በሞምባሳ የተጠናቀቀው ይህ ስምምነት የንግድ ሂደቶችን በማቅለል የድንበር ማህበረሰቦችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማሳደግ ያለመ ነው።

በስምምነቱ የኢትዮጵያ የድንበር ንግድ ዞን ከሞያሌ በ50 ኪሎ ሜትር እንዲሁም የኬንያ ደግሞ በ100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚወሰን ነው።

ነጋዴዎችም በጋራ በተስማሙበት የምርት ዝርዝር መሰረት እስከ 1 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የንግድ ልውውጥ በወር እስከ አራት ጊዜ ድረስ ማካሄድ ይችላሉ ተብሏል።

ይህ ስምምነት የንግድ ዋጋ ጣሪያዎችን፣ የጉዞ ድግግሞሽን እና የድንበር ንግድ ዞኖችን የመሳሰሉ ጉዳዮችን በመዳሰስ ለሁለት ዓመታት በዘለቀ ድርድር የተገኘ ውጤት ነው ተብሏል።

መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia
19.04.202523:27
19.04.202517:39
19.04.202517:21
#Update : በማይናማር ' ዲኬቢኤ ' ካምፕ የነበሩ 252 ኢትዮጵያውያን ትላንት ለታይላንድ የቀረበች በማይናማር በምትገኝ ማይዋዲ ወደምትባል ከተማ መሻገራቸውን፣ ይህም ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የሚያስችላቸው አንድ እርምጃ መሆኑን የወላጆች ኮሚቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በዚህም፣ ኢትዮጵያውያኑንና የሌሎች ሀገራት ዜጎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 276 ወጣቶችን የዲሞክራቲክ ካረን ጦር ወደ ማይዋዲ እንደላከ ኮሚቴው ነግሮናል።

ኢትዮጵያውኑ በማይናማር በሚገኘው የዲሞክራቲክ ካረን ጦር (ዲኬቢኤ) ሥር የነበሩ፣ በመጀመሪያ ወደ ታይላንድ እንዲያሻግራቸው፣ ከዚያ ወደ ሀገራቸው እንዲመልሳቸው የመንግስትን ምላሽ ደጋግመው ሲጠይቁ የነበሩ ናቸው።

ኮሚቴው " አሁንም ገና መንግስት ወደ ቦታው ወኪል መላክ አለበት። ‘ለኤንጂኦ ውክልና ሰጥተናል’ ነው ያሉት ግን በኤንጂኦ ውክልና ብቻ ተላልፈው ወደ ኢትዮጵያ መተላለፍ አይችሉም። ለዚህ ጉዳይ የመንግስት ደሊጌሽን ያስፈልጋል " ብሏል።

" በተጨማሪም፣ በማይናማር ቢጄኤፍ ካምፕ ስክሪን አውት ተደርገው፣ ፓስፓርት ተሰጥቷቸው የተቀመጡ ወደ 495 ኢትዮጵያውያን አሉ። እንዲሁም የመንግስትን ሰብዓዊ ድጋፍ የሚፈልጉ ሦስት ልጆች በስቃይ ናቸው የዛሬዎቹ ልጆቻቸን ከወጡበት አካባቢ ያሉ ማለት ነው " ሲል አክሏል።

" ከዚህ ቀደም ልጆቻችን በአንድ ወቅት ከካምፕ ባመለጡበት ወቅት በፓሊስ ታግተው የተመለሱ ወደ 26፣ በቢጂኤፍ ካምፕ አካባቢም ሌሎች 14 ልጆቻችን በስቃይ ላይ ናቸው። የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው ያሉት " ብለዋል።

" ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቀናል። ልጆቹን ከነሙሉ ስማቸውና ከነፓስፓርት ቁጥራቸው አስተላልፈናል። ‘ለሁለቱም ኤምባሲዎች እናሳውቃለን’ ብለውናል " ሲል ኮሚቴው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
18.04.202517:44
Shown 1 - 24 of 1687
Log in to unlock more functionality.