МОр сегПЎМя с "ЮрОй ППЎПляка"
МОр сегПЎМя с "ЮрОй ППЎПляка"
НОкПлаевскОй ВаМёк
НОкПлаевскОй ВаМёк
ЛачеМ пОше
ЛачеМ пОше
МОр сегПЎМя с "ЮрОй ППЎПляка"
МОр сегПЎМя с "ЮрОй ППЎПляка"
НОкПлаевскОй ВаМёк
НОкПлаевскОй ВаМёк
ЛачеМ пОше
ЛачеМ пОше
💞አውደ💞 ቃል 💞💖 avatar
💞አውደ💞 ቃል 💞💖
💞አውደ💞 ቃል 💞💖 avatar
💞አውደ💞 ቃል 💞💖
​
​
МөөМөт
КөрүүлөрЎүМ саМы

ЊОтаталар

ППсттПр
РепПсттПрЎу жашыруу
05.05.202520:46
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
ӚчүрүлгөМ04.05.202519:41
🔥👏 ተኹፈተ ተኹፈተ ተኹፈተ 👏🔥

🥳 አስደሳቜ ዜና 🥳

🔎ለአርሎናል እና ለማንቺስተር ዩናይትድ 🔎 ደጋፊዎቜ አዲስና ለዚት ያለ ቻናል ዚዘነላቜሁ መጥተናል በኢትዮጵያ ዚመጀመሪያው ዹአርሮናልና ዚማንቜስተር ዩናይትድ ቻናል ነው መሚጃዎቜን በአንድ ቊታ በአንድ ቻናል ለዚት ባለ ሁኔታ ዚዘነላቜሁ መጥተናል ኹናንተ ዹሚጠበቀው ቻናሉን join በማሹግ ቀተሰብ ማሆን ብቻ ነው ::
✞ ማክሰኞ- ቶማስ ይባላል፡-

በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑፀ "ጌታዬና አምላኬ" ብሎ መመስኚሩ ይዘኚራል፡፡ ዮሐ.፳፥፳፯-፳፱

                 🌹🌹
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
                 🌷🌷
Кайра бөлүшүлгөМ:
መዝሙር ቲዩብ™ avatar
መዝሙር ቲዩብ™
20.04.202506:07
#እንኳን ለብርሀነ ትንሳኀ አደሚሳቜሁ

            ✹ «ትንሣኀ» ✹
ዹሚለው ቃል ዚግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ ዹሚለው ግሥ ይሆናል፡፡
«ትንሣኀ» ማለት ታዲያ = መነሣት፣ አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡
«ትንሣኀ» በሊቃውንተ ቀተ ክርስቲያን በዚመልኩ፣ በዚዐይነቱ ሲተሚጐም ዐምስት ክፍል አለው፡፡
          አኹፋፈል
✹አንደኛው «ትንሣኀ» ኅሊና ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡

✹ሁለተኛውም «ትንሣኀ» ልቡና ነው፡፡ ዹዚህም ምስጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እዚታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡

✚ሊስተኛው «ትንሣኀ» ለጊዜው ዚሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይኚተለዋል፡፡

✚አራተኛው «ትንሣኀ» ዚክርስቶስ በገዛ ዚባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ ዚእርሰ ትምህርታቜንም መሠሚት ይኾው እንደሆነ ይታወሳል፡፡

✚አምስተኛውና ዚመጚሚሻው «ዚትንሣኀ» ደሹጃም ዚባሕርይ አምላክ ዚጌታቜን ዚመድኀኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስን «ትንሣኀ» መሠሚት ያደሚገ «ትንሣኀ ዘጉባኀ» ነው፡፡ ይህም ኹዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደዚሥራው ለክብርና ለውርደት፣ ለጜድቅና ለኩነኔ በአንድነት ዚሚነሣው ዹዘለዓለም ትንሣኀ ይሆናል፡፡

☊#ዚትንሣኀ በዓል በቃሉም ምስጢር በይዘቱም ስለሚመሳሰሉ ጥላው ምሳሌውም፣ ስለሆነ «ፋሲካ» ተብሎ ይጠራል፡፡ «ፋሲካ» ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ «ፌሳሕ» በጜርእ በግሪክኛው «ስኻ» ይባላል፡፡ ይህም ወደ እኛው ግእዝና ዐማርኛ ቋንቋቜን ሲመለስ ፍሥሕ ዕድወት = ማዕዶት፣ በዓለ ናእት = ዚቂጣ በዓል፣ እዚተ቞ኮለ ዹሚበላ #መሥዋዕት፣ #መሻገር #መሾጋገር ማለት ነው፡፡

☊#ታሪካዊ መልእክቱ በዘመነ ኊሪት ይኹበር ዹነበሹው በዓለ ፋሲካ እስራኀል ዘሥጋ ኚግብጜ ዚባርነት ቀንበር ወደነፃነት ዚተላለፉበት፣ ኚኚባድ ሐዘን ወደ ፍጹም ደሰታ፣ ዚተሞጋገሩበት በዓል ነበር፡፡ በዚህ ኊሪታዊ ምሳሌ በዓል አሁን አማናዊው በዓል «ትንሣኀ» ተተክቶበታል፡፡

☊#ፋሲካ፣ በዓለ ትንሣኀ በዘመነ ሐዲስ እስራኀል ዘነፍስ ዚሆኑት ምእመናነ ክርስቶስ ትንሣኀውን ዚሚያኚብሩበት ዕለት ሆኖ በእርሱ ትንሣኀ #ኚኀጢአት ወደ ጜድቅ፣ ኚኀሳር = ኚውርደት ወደክብር፣#ኚጠላት ሰይጣን አገዛዝ ወደ #ዘለዓለማዊ ነፃነት፣ #ኚአደፈ፣ #ኹጐሰቆለ አሮጌ ሕይወት ወደ ሐዲስ ሕይወት ዚተሻገሩበት ታላቅ መንፈሳዊ ዚነፃነት በዓል ነው፡፡

☊#ክርስቲያኖቜ ዚትንሣኀን በዓል በታላቅ ደስታና መንፈሳዊ ስሜት ያኚብሩታል፡፡ ስለዚህም ኚበዓላት ሁሉ ዹበለጠ ሆኖ ይታያል፡፡
          #ባህሉስ
ኚትንሣኀ እሑድ ጀምሮ እስኚ ዳግም ትንሣኀ ድሚስ ሕዝበ ክርስቲያኑ «እንኳን ጟመ ልጓሙን ፈታላቜሁ» እዚተባባለ በመጠራራት ዐብሮ ሲበላ ሲጠጣ ልዩ ልዩ ጚዋታ ሲጚዋወት ለንስሐ አባትና ለሜማግሌዎቜ ለወዳጅ ዘመድም ዹአክፋይ ዳቊ፣ ወይም ዚሥጋ ወጥ ግፍልፍል ሲወስድ ይሰነብታል፡

አገልግሎቱን መደገፍ መርዳት ለምትፈልጉ ሃሳብ አስተያዚት ጥያቄ ካላቜሁ  በዚህ በኩል ያናግሩን!


@emebtemariyam21bot

📲 @mezmurortodox21📱
📲 @mezmurortodox21📱
15.04.202518:46
ዹሰሙነ ሕማማት
ሊስተኛው ቀን
#ምክሹ አይሁድ
#ዚመልካም መዓዛ
#ዚእንባ ቀን




@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
Кайра бөлүшүлгөМ:
😍ዚጥበብ አለም ✍✍ avatar
😍ዚጥበብ አለም ✍✍
04.05.202519:03
ሰላም ቀተሰብ ዛሬ ኹ social media ላይ ያገኘውትን ታሪክ ላካፍላቜሁ ነው።ተኚታተሉ!!!!!!!!!!


አንድ ዘመኑን በሀጥያት ያሰለፈ ወጣት ንስሀ ለመግባት ይፈልግና ወደ ቀተክርስቲያን ሂዶ ዚንስሀ አባት ይዞ ንስሀ ይገባል።አባቱም ኹ ንስሀው በጚማሪ ሁሌም መፅሀፍ ቅዱስ እንዲያነብ እና ቶሎ ጚርሶ እንዲያስሚዱት ነግሹው ላኩት።ልጁም እያነበበ እያነበበ አልገባ አልሚዳህ ሲለው ወደ አባቱ ሂዶ አባ አቅቶኛል አላ቞ው።እሺ ልጄ ሌላ ልዘዝህ አሉና ዹኹሰል ማዳበሪያ ይዘው መተው በዚህ ማዳበሪያ ኹሀይቅ ውሀ እያመላለስክ ያንን በርሚል ሙላ ይሉታል።ልጁም ተቀብሎ ሲመላለስ ዋለ ነገር ግን ማዳበሪያ ውሀ አይዝምና ሳያደርሰው አፍሶ እዚለቀቀ መሙላት አልቻለም።አባቱንም አባ቎ ማዳበሪያው እኮ ውሀ አይዝም አላ቞ው።እሳ቞ውም አዹህ ልጄ ያላስተዋልኚው ነገር ማዳበሪያው በኹሰል ዹቆሾሾ ነበር አሁን ግን ፀድቷል አላ቞ው።ስለዚህ ልጄ መፅሀፍ ቅዱሱንም ስታነብ እግዚአብሔር እንደዚህ ውስጥህን ያፀዳዋል።።አላ቞ው ይባላል።።።።

እናም ሁልጊዜም መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ ይልመድብን ወደ እግዚአብሔር ያቀርበናልና።።።።

መልካም ምሜት😊😊

@tsedi12m

@yetbebaleme
@yetbebaleme
@yetbebaleme
እሚ join እያሚጋቜሁ አበሚታቱን❀
27.04.202518:32
እንኳን ለዳግም ትንሣኀ በሰላም አደሚሳቜሁ 🙏

               🌹🌹
@AWDEKALAT_2112
                 🌷🌷
25.04.202520:45
✞ ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡-

በዚህ ዕለት ለአዳም ዹተሰጠው ተስፋ እና ዚተገባለት ኪዳን እንደተፈጞመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡


@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
23.04.202522:20
✝ኚትንሳኀ በኋላ ያሉት ቀናት ስያሜ✝

ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡-

ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካቜን በክርስቶስ ትንሣኀ ኚድቅድቅ ጹለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ኚሞት ወደ ሕይወት፣ ኚሲኊል ወደ ገነት፣ ኚሃሳር ወደ ክብር መሻገራቜንን እናስባለን፡፡


                 🌹🌹
@AWDEKALAT_2112
                 🌷🌷
​​​​ ቅዳሜ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧



➊ ቀዳም ስዑር ትባላለቜ ፊ

ይህቜ እለት ኚድሮ በተለዹ መልኩ ዚጌታቜንን መኚራ በማሰብ በጟም ታስባ ስለምትውል ዚተሻሚቜ ቅዳሜ ይባላል።
➊ ለምለም ቅዳሜ ይባላል፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጀማ ዚሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጀማ እስኚ ትንሣኀ ለሊት በራሳ቞ው ላይ ያስሩታል።



➊ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡-

ቅዱስ ዹሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥሚታትን አኹናውኖ ያሚፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ዚማዳን ስራውን ሁሉ ፈጜሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኊል ወርዶ ሲኊልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ ዚነበሩትን ነፍሳት ዹዘላለም ዕሚፍትን ያወሚሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።



     ✚🌷 እንኳን አደሚሳቜሁ አደሹሰን 🌷✚
            ፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧



@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
15.04.202504:16
#ሰሙነ ሕማማት

ኹሰኞ እስኚ ቅዳሜ ሰሙነ ሕማማት ዚጟመ ሁዳዎ ዚመጚሚሻው ሳምንትፀ ዚጌታቜን ዚመድኃኒታቜን ዚኢዚሱስ ክርስቶስ ሕማም ዚሚታሰብበትፀ ካህናትና ምእመናን በአጾደ ቀተክርስቲያን ተሰብስበው ዹሕማሙን ነገር ዚሚያወሳውን ዜማ ዚሚያዜሙበትፀ ግብሚ ሕማም በመባል ዚሚታወቀውን መጜፍ ዚሚያነቡበትና ዚሚሰሙበትፀ በነግህ፣ በሠልስት፣ በስድስት፣ በተሰዓት /ዘጠኝ /ሰዓት፣ በሰርክ /በዐስራ አንድ/ ሰዓት እዚመላለሱ ዚሚሰግዱበትና ዚሚጞለዩበት ልዩ ሳምንት ነው ኚሆሳዕና ማግስት እስኚ ትንሳኀ።

በዚህ ሳምንት በተለይ ካህናት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ ምክንያቱም ጌታቜን ዚደሚሰበትን መኚራና ስቃይ እንዲሁም ዹሰው ልጅ ፭ ሺ ፭ መቶ ዘመን በጹለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘኹርም ጭምር ነው።
ዚጌታቜን ዚመድኃኒታቜን ዚኢዚሱስ ክርስቶስን መኚራና ሕማም በጜኑ እንድናስበው ያስተማሩን ሐዋርያት ና቞ው። ለእነርሱም ዚነገራ቞ው ደግሞ ራሱ ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ነው።
ሰሙነ ሕማማት ዚጌታቜንን ሕማማት ኚማሰብ ጋር በዚዕለቱ በርካታ ድርጊቶቜ መፈጾማቾውን ዚምናስታውስበት ሳምንት ነው፩

            📖ሰኞ

መርገመ በለስ ዚተፈጞመበት ሰኞ ይባላልፊ
በዚህ ዕለት ጌታቜን ኚቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ኹቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ኹአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለሚገማት መርገመ በለስ ዚተፈጞመበት ሰኞ ይባላል።

አንጜሖተ ቀተመቅደስ ይባላል፡-
ጌታ ወደ ቀተመቅደስ ሄዶ በቀተመቅደሱ ዚሚሞጡትን እና ዚሚለውጡትን “ቀ቎ ዚጞሎት ቀት ትባላለቜ” ማቮ ፳፩፥፲፫ በማለት ኚቀተመቅደስ ገርፎ አስወጥቷ቞ዋልና።

      📖ማክሰኞ

ዚጥያቄ ቀን ይባላልፊ
ሰኞ ዕለት በቀተመቅደስ ሲሞጡ እና ሲለውጡ ዚነበሩትን ሁሉ እዚገሚፈ በማባሚሩ ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን ዹሰጠ ጌታ “በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ?” ማቮ ፳፩፥ ፳፫ ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና ዚጥያቄ ቀን ይባላል።

ዚትምህርት ቀን ይባላል፡-
በዚህ ዕለት በቀተመቅደስ ሹጅም ትምህርት ስላስተማሚም ዚትምህርት ቀን ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪።

      📖ሚቡዕ

ምክሹ አይሁድ ይባላልፊ
ሚቡዕ እለት ዚአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጞሐፍት ጌታን እንዎት መያዝ እንዳለባ቞ው ዚመኚሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክሹ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ ዚፋሲካን በዓል ዚሚያኚብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይኹተለው ስለነበር ሁኚት እንዳይነሳ ስጋት ነበራ቞ው ። ነገር ግን ኚአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ዚአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣ቞ው ስለነገራ቞ው ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ጭንቀታ቞ው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል።

ዚመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፡-
ጌታቜን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቀት ተቀምጩ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር ዚነበሚቜው ማርያም እንተ እፍሚት/ባለሜቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ ዹሆነ ዚአልባጥሮስ ሜቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርኹፍኹፍ ስለቀባ቞ው ማቮ ፳፮፥፮-፯ ዹመዓዛ ቀን ይባላል።

ዚእንባ ቀን ይባላል፡-
ባለሜቱዋ ሎት (ማርያም እንተ እፍሚት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እዚለመነቜ በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለቜና ማር ፲፬፥፱ ዚእንባ ቀን ይባላል።

       📖ሐሙስ

ጾሎተ ሐሙስ ይባላልፊ
ጌታቜን ለአይሁድ ተላልፎ ኚመሰጠቱ በፊት በጌቮሮማኒ ዚአትክልት ስፍራ ሲጞልይ በማደሩ ማቮ ፳፮፥ፎ፮ ጾሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታቜን ዚደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጜበተ ሐሙስ ይባላል።

ዚምስጢር ቀን ይባላል፡-
ኚሰባቱ ምስጢራት አንዱ ዚቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማ቎፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጜሟልና ዚምስጢር ቀን ይባላል።

ዚሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡-
መሥዋዕተ ኊሪት /በእንስሳት ደም ዚሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድህነት ራሱን ያቀሚበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ ዚሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።

ዚነጻነት ሐሙስ ይባላል፡-
ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም ዹሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ ዚተሚጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ ዚነጻነት ሐሙስ ይባላል።

             📖ዓርብ

ዚስቅለት ዓርብ ይባላልፊ
ጌታቜን ዚመድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቀዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ዚዋለበት ዕለት ነውና ማቮ ፳፯፥ፎ፭ ዚስቅለት ዓርብ ይባላል።

መልካሙ ዓርብ ይባላል፡-
ኚጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ ዹወንጀለኛ መቅጫ ምልክት ዹነበሹውን መስቀል ጌታቜን በደሙ ቀድሶ ዚምህሚት፣ ዚሕይወት አርማ፣ ዚዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደሚገውፀ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።

          📖ቅዳሜ

ቀዳም ስዑር ትባላለቜ ፊ
ይህቜ እለት ኚድሮ በተለዹ መልኩ ዚጌታቜንን መኚራ በማሰብ በጟም ታስባ ስለምትውል ዚተሻሚቜ ቅዳሜ ይባላል።
ለምለም ቅዳሜ ይባላል፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጀማ ዚሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጀማ እስኚ ትንሣኀ ለሊት በራሳ቞ው ላይ ያስሩታል።

ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡-
ቅዱስ ዹሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥሚታትን አኹናውኖ ያሚፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ዚማዳን ስራውን ሁሉ ፈጜሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኊል ወርዶ ሲኊልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ ዚነበሩትን ነፍሳት ዹዘላለም ዕሚፍትን ያወሚሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።

    @AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
ӚчүрүлгөМ04.05.202519:41
Кайра бөлүшүлгөМ:
ማሩፍ ስፖርት™ avatar
ማሩፍ ስፖርት™
02.05.202506:16
📥 wave 📥  መግባት ዚምትፈልጉ 
      
◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩◩
➺ Above  ➣  1k subscribers
➺ Above  ➣  2k+ subscribers
➺ Above  ➣  3k+ subscribers


ኹዛም በታቜ ያላቹ እንዳትመጡ!!  ቊታው ሳይሞላ አፍጥኑት

🅘🅝🅑🅞🅧 @king_negn

FOLDER LINK https://t.me/addlist/_PHX8J2JOmBiYmVk
✞ ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡-

በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት ዚክርስቶስን አካል ሜቶ ለመቀባት ጹለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታ቞ውና ትንሣኀውንም ቀድመው ማዚታ቞ው ይሰበካል፡፡

@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112



🙏🙏🙏
24.04.202518:59
ምናልባት
ወ ደ ፊ ት!
<strike>~</strike>~~~
እኔም ትልቅ ሆኜ
እሄ ትንሜ ልቀ አድጎ ኹተገኘ
በ ትላልቅ ሀሳብ ቅኔ ኹተቀኘ
~~~~
ዛሬ አሰባስቀ
ያስቀመጥኳ቞ውን ዹበደል ጥሪቶቜ በደሜ መዝግቀ
- - - ነገ በተራዬ
አስሚክበዋለው ውስጀን ላቆሰለው ምስጋና ደርቀ

ለምን ቢባልማ

ክፉ ለቾሹኝ ሰው ክፋት አላወርስም
ቂም በቀል አልይዝም
ምክንያቱም
- - - **እንኳን እኔ ፍጡሯ
ፈጣሪም ራሱ ምህሚት ነው እንጅ ቅጣት አያውጅም!
             
𝕃𝕚𝕜𝕖❀  𝑆ℎ𝑒𝑟💌  𝗝𝗌𝗶𝗻📥 🙏
     

         @AWDEKALAT_2112   🥇
23.04.202512:16
ፍቅር ይሆን እንዎ ?
___

  አይንሜ
ለማዚት ዹምርበደበደው
ድምፅሜን ስሰማ ባንዎ ዹምርደው
ስምሜን ሲጠሩት ኚተቀምጥኩበት ዚምነሳው ባንዎ
እኔምን አውቃለሁ ወድጄሜ ነው እንዎ ?

ፍቅር አይመስለኝም ብቻ ናፍቀሺኛል
አብሚሺኝ ኚሌለሜ  ያቁነጠንጠኛል
ያመኛል ያመኛል
ስጚነቅ ያዚ ሰው ፍቅር ነው ይለኛል

ፍቅር ይሆን እንዎ
                ያኚሳኝ ሰሞኑን
እንዎት ነው ዹማውቀው
              አፍቅሬሜ መሆኑን

ስራመድ በድንገት አንቺን እያስታወስኩ
ምኑንም ሳላውቀው ይሀው ቀትሜ ደሚስኩ

ላንኳኳ ነበሹ እጄ ቊታው ጠፋኝ
ወደቀት ተመለስኩ እንዲያ እንደኚፋኝ
አፍቅሬሜ ኹሆነ  አልፈልግም በቃኝ 😫



👇🏟👇🏟👇🏟
@AWDEKALAT_2112


""""""""""""""""""""
15.04.202519:49
(...)

ዚምኞት መጹለም
ዚትዝታ መናድ
በወዳጅ መጠላት
ባመኑት ሰው መካድ
ሲኖሩት አይደለም
ሲያስቡት ነው ኚባድ ።


ኚወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ


@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
Кайра бөлүшүлгөМ:
ማኅደሹ ተዋህዶ avatar
ማኅደሹ ተዋህዶ
መርገመ በለስ

ዹሰሙነ ሕማማት ዚመጀመሪያው ዕለት ዕለተ ሰኑይ መርገመ በለስ ይባላል፡፡

ጌታቜን ዚሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግስቱ ኚቢታንያ ሲወጣ ተራበፀ በመንገድም ሲያልፍ ቅጠል ያላት በለስን ኚሩቁ ተመለኚተ፡፡ ወደ በለሲቱም በቀሹበ ጊዜ ኹቅጠል በቀር አንዳቜ ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ያንጊዜም ‹‹ኚእንግዲህ ወዲህ ለዘለዓለም ኚአንቺ ፍሬ ዹሚበላ አይኑር›› ሲል በለሲቱን ሚገማት፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ይህንን ሰሙት፡፡ በዚህም ምክንያት ይህቜ ዕለት በለሲቱ ዚተሚገመቜባት ቀን ናትና መርገመ በለስ ተብላ ትጠራለቜ፡፡ (ማር.፲፩፥፲፩-፲፬)

በዚህ አገላለጜ በለስ ዚተባለቜ ቀተ እስራኀል ስትሆን ፍሬ ዚተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባር ነው፡፡ መድኃኒታቜን ክርስቶስ ኚእስራኀል ፍቅርን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን ፈልጎ አላገኘባ቞ውም፡፡ እስራኀልፊ ሕዝበ እግዚአብሔር፣ ዚአብርሃም ዘር መባልን እንጂ ዚአብርሃምን ሥራ በመሥራት በምግባር በሃይማኖት ጾንተው መኖር አይፈልጉምና ደግ ሰው አልተገኘባ቞ውም፡፡

ኹዚህም ባሻገር በለስ ዚተባለቜ ኃጢአት ናት፡፡ ዚበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነቜ ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አግኝቷታል፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣልፀ ቆይቶ ግን ይመራልፀ ኃጢአትም ሲሠሩት ለጊዜው ደስ ያሰኛል ኋላ ግን ያሳዝናል፡፡ በአንቺ ፍሬ አይገኝ ዹሚለውም በአንቺ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ ዹሚቀር አይኑር ሲል ነው፡፡ በለሲቱ ስትሚገም ፈጥና መድሚቋም በአዳም ምክንያት ያገኘን በደል በእርሱ እንደጠፋልን ለመግለጜ ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
💚 @Mahdere_tewahedo 💚
💛  @Mahdere_tewahedo 💛
❀ @Mahdere_tewahedo ❀
01.05.202519:24
አንቺን አገኝ ብዬ
:
ሎትን ዹመማሹክ ቁልፍ ሚስጥራቶቜ
ሃያ አራቱ ድብቅ ዚመግባቢያ ስልቶቜ
ሰባቱ ታላላቅ ዹፍቅር መንገዶቜ
ዘጠና ዘጠኙ ግሩም አባባሎቜ
አራቱ ዚሎት ልጅ፣ ያልተቃኙ ቅፆቜ
ሁለቱ ዚፍቅር፣ ተለዋዋጭ ገፆቜ
:
:
ብለው ዹተፃፉ
ወ.ዘ.ተ  መፅሐፍትን እንደሞመደድኩት
ሳነብ ስታትር፣ ውዬ እንዳደርኩት!
አታውቂም!
¶
አንቺን አገኝ ብዬ
:
እንደሚያገባ ሰው ሜርክርክ ብዬ
ጀነን ኮራ እያልኩ ኚደጃፍሜ ውዬ
አመሻሜ መመለስ በብስጭት በቂም
ዚዘውትር ተግባሬ መሆኑን አታውቂም።
¶
አንቺን አገኝ ብዬ
:
ጓደኞቌን ልኬ፣ ገፍተው እንዲነኩሜ
እራሎው መጥቌ፣ ዚውሞት ያዳንኩሜ
ስታመሰግኝኝ በደስታ ስትስቂም
ለፍቅርሜ ውለታ መሆኑን አታውቂም።
:
አንቺ አገኝ ብዬ
ዚጥንዱን ቀት ሳይቀር እንደመሚመርኩኝ
ገፃቾውን ሁሉ ፎሎ እንዳሚኩኝ
አታውቂም!
:
አንቺን አገኝ ብዬ
ዚልቀን አርግቀ ናፍቆቮን ባልቆርጥም
ለፍቅርሜ ስጊታ ዚፃፍኩልሜ ግጥም
ዛሬ ካንቺ ጋራ በልቀ ውስጥ አድጎ
እዛው እንዳስቀሚኝ ገጣሚ አድርጎ
አታውቂም!
:
አንቺን አገኝ ብዬ
ፍልስፍናን ግቌ ስለፍቅር መንገድ
ጓዝ ጥቅልሉ ሳይቀር ቢኖሚው ብዬ ገድ
ሳነበው... ስፅፈው፣ ዘመን እንደፈጀው
ዹፍቅር ፈላስፋ ሆኜ እንዳሚጀው።
አታውቂም!




@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112



        ✹......✹......✹
         ✹......⭐........✹

  ——¯_✚—⭐—_—✚¯_
✞ አርብ- ቅድስት ቀተክርስቲያን ይባላል፡-

በዚህ ዕለት ቀተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኀ ስለመመስሚቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቀዛ ሆኖ በደሙ አንጜቶ በትንሣኀው ድል ሰጥቶ እንዳኚበራት ይነገራል፡፡



@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112

         🊋🊋🊋
✞ ሚቡዕ- አልአዛር ይባላል፡-

በዚህ ዕለት ትንሣኀና ሕይወት ዹሆነው ጌታቜን አምላካቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ኚሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ ዚሞትን ስልጣን ዚሻሚ ዚሕይወት ራስ ፀ ዚመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኀ፡ በድልም ያሚገ ንጉሥና ዚባህርይ አምላክ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡


                 🌹🌹
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
                 🌷🌷
""" ሕያዉን ኚሙታን መካኚል ስለ ምን ትፈልጋላቜሁ ?  ተነስቷል እንጂ በዚህ ዚለም።"""  ሉቃ ፪፬ ÷  ፭
"ክርስቶስ ተንሥአ እሙታንፀ
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣንፀ
አሰሮ ለሰይጣንፀ
አግዐዞ ለአዳምፀ
ሠላም ፀ
እምይዕዜሰ ፀ
ኮነፀ
ፍስሐ ወሠላም፡፡”
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኀ በአል በሰላም አደሚሳቹ😊

💙💙💙 መልካም በዓል 💙💙💙

@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
Кайра бөлүшүлгөМ:
💞አውደ💞 ቃል 💞💖 avatar
💞አውደ💞 ቃል 💞💖
15.04.202519:49
ዹሰሙነ ሕማማት
ሊስተኛው ቀን
#ምክሹ አይሁድ
#ዚመልካም መዓዛ
#ዚእንባ ቀን




@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
ሆሳዕና በአርያም 🌿🌿🌿🌿


እንኳን ለ ሆሳዕና በዓል በሰላም አደሚሳቜሁ አደሹሰን 🌿🌿🌿🌿

@AWDEKALAT_2112
@AWDEKALAT_2112
КөрсөтүлЎү 1 - 24 ОчОМЎе 38
Көбүрөөк фуМкцОяларЎы ачуу үчүМ кОрОңОз.